Category Archives: News

ሕዝባዊ መሰረቱን ያረጋገጠ ታላቅ ተቃውሞ!

ድምፃችን ይሰማ

አላሁ አክበር! የኢትዮጵያ ሙስሊም ዛሬም ጥያቄው ሳይመለስ ቤቱ እንደማይገባ፣ ተቃውሞውንም እንደማያቆም ዳግም ሲያረጋግጥ ዋለ! ለሳምንታዊው የጁምአ ሰላት ቀደም ብሎ በታላቁ አንዋር መስጊድ ቦታ ቦታውን የያዘው ጨዋ ህዝብ የዛሬው አመጣጡ ከቀድሞው የተለየ እንደነበር ያስታውቃል፡፡ ቀደም ባሉት ቀናት ኢቲቪ በመሪዎቻችን ላይ ህግ እና የፍርድ ቤት ትእዛዝ ጥሶ የፈጸመው በደል ውስጡ ድረስ ሰርጎ ተሰምቶታል፡፡ በሰዎች ፊት ላይ ቁጣ ይነበባል፡፡ሕዝባዊ መሰረቱን ያረጋገጠ ታላቅ ተቃውሞ!

አዎ! በዛሬዋ ቀን ሰዎች ወደ ጁሙአ የመጡት ተቃውሟቸውን ለማሰማት ብቻ አልነበረም፡፡ ይልቁንም የትኛውም አይነት የተንኮል ቢላዋ በእነሱና በመሪዎቻቸው መካከል ያለውን የፍቅር ገመድ ሊበጥስ እንደማይችል በማያወላውል ሁኔታ ለማረጋገጥም ጭምር ነበር፡፡ አልሀምዱሊላህ – ተቃውሟቸውንም ያላንዳች እንከን በሰላም ነበር ያጠናቀቁት፡፡ አመት ሙሉ ጨዋነቱን በተደጋጋሚ እያሳየ በተቃራኒው ግን የሚፈጸምበት በደል እየጨመረ እና ድንበር እየታለፈበት እንኳን ስሜቱ ትእግስቱን የማያሸንፍበት ህዝብ በእርግጥም ሊወደስ ይገባዋል!የሰዉ ብዛት እጅግ አስገራሚ ነበር፡፡ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ቦታው በሰዎች ተወርሮ ነበር፡፡ ከጎጃም በረንዳ መጠምዘዣ ጀምሮ ወደታች አሜሪካ ግቢን አልፎ ወደሱማሌ ተራ መውረጃ፣ በሴቶች በኩል ወደመርካቶ ዘልቆ ገብቶ ነበር፡፡ በሲኒማ ራስ በኩል የነበረው ቦታም እንዳለ በሰጋጆች ተይዞ ነበር፡፡ ከሌላው ጊዜ ለየት ባለ ሁኔታ መፈክሮች በባነር ጭምር ተዘጋጅተው ነበር፡፡ በሴቶች መስጊድ በኩል ጀግኖች እህቶቻችን የ28ቱ ጀግኖቻችን ፎቶ የታተመበትን ትልቅ ባነር ከፍ ድርገው ይዘው ሲያሳዩ የነበረ ሲሆን ፊልሙ ላይ በግድ ምስክርነት እንዲሰጡ የተደረጉት ኡስታዝ አቡበክርና ካሚል ሸምሱ፣ እንዲሁም የኡስታዝ በድሩ ሁሴን ፎቶዎች በትላልቁ ታትመው በወንዶች በኩል ሲውለበለቡ ታይተዋል፡፡

በዚህ ታላቅ ተቃውሞ የትግሉን መንፈስ የሚገልጹ በርካታ መፈክሮች ተስተጋብተዋል፡፡ በዚህ ታላቅ ተቃውሞ የትግሉን መንፈስ የሚገልጹ በርካታ መፈክሮች ተስተጋብተዋል፡፡ ‹‹አሃዱን አሃድ!››፣ ‹‹ህጉ ተጥሷል!››፣ ‹‹የሐሰት ክስ አይገዛንም!›› ‹‹ኮሚቴዎቻችን አሁንም ህጋዊ ወኪሎቻችን ናቸው!››፣ ‹‹እኛ አቡበክር ነን!››፣ ‹‹እኛ ያሲን ኑሩ ነን!››፣ ‹‹እኛ ካሚል ሸምሱ ነን!›› የሚሉ መፈክሮች ተሰምተዋል!

በዚህ ታላቅ ሰላማዊ ተቃውሞ ካሁን በፊት ሲሞከር እንደነበረው ሁሉ ሰዉን ወደስሜታዊነት ለማስገባት ሲባል 12፣ 13 እና 41 ቁጥር አንበሳ አውቶቡሶች ተቃውሞውን አቋርጠው እንዲያልፉ የተደረገ ሲሆን አላማውም ህዝበ ሙስሊሙ ንዴቱ ገንፍሎ ድንጋይ ሲወረውር ‹‹በህዝብ ንብረት ላይ ጉዳት አድርሰዋል!›› የሚል ፕፓጋንዳ ለመንዛት ነበር፡፡ ይርጋ ሀይሌ ህንጻ ላይ ተዘጋጅቶ ሲጠብቅ የነበረው የኢቲቪ ካሜራ ግን ከሰላማዊ ተቃውሞ እና ‹‹አንሰብርም! አንሰብርም!›› ከሚል መፈክር ውጭ አንዳችም የድንጋይ ውርወራ ሳይቀርጽ ወደመጣበት ለመመለስ ተገዷል፡፡ ብዙዎች ተንኮለኝነት የግለሰብ ሳይሆን የመንግስታት ባህሪ መሆኑ በጣም አሳዝኗቸዋል፡፡

በዛሬዋ ጁምአ ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ከተሞችም የተለያዩ ተቃውሞዎች ተደርገዋል፡፡ ካሁን ቀደም ከፍተኛ ተቃውሞ ሲደረግባት በቆየችው ሻሸመኔ ከተማ ዛሬም ታላቅ የተክቢራ ተቃውሞ ተደርጓል፡፡ በቦታው እጅግ በርካታ የፖሊስ እና ፌደራል ታጣቂ ሀይል የነበረ ቢሆንም ሰላማዊው የሻሸመኔ ሙስሊም ማህበረሰብ ሰላማዊ ተቃውሞውን አሰምቶ በሰላም ተመልሷል፡፡ በደዶላ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ መስጊዶችም ጊዜውን የጠበቀ እና የሞቀ ተቃውሞ ተደርጓል፡፡

መንግስትና አህባሽ መሳጂዶችን በመንጠቅ እና የቁርአን ማቅሪያዎችን በመዝጋት ቢዚ ሆነውባት በነበረችው የኮምቦልቻ ከተማም እንዲሁ ተቃውሞ ተደርጎ ውሏል፡፡ በባቲ ከተማም ቢሆን ከጁምአ ሰላት በኋላ በሴት እህቶች በኩል ጠንካራ የተቃውሞ ስነ ስርአት ተደርጓል፡፡

በሌላ በኩል በሀረርና በጂማ ከተማ ለየት ያሉ ተቃውሞዎች ተስተውለዋል፡፡ በሁለቱም ከተሞች በርካታ መስጊዶች የተሳተፉበት የዱአ ተቃውሞ ስነስርአት ተደርጓል፡፡ በአባ ጂፋሯ ጅማ ለወትሮው ጁምአ በሚሰገድባቸው 40 ያህል መስጊዶች ህዝበ ሙስሊሙ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል አላህ እንዲያነሳው እና ኮሚቴዎቻችንንም አላህ ከተንኮል እንዲጠብቃቸው ዱአ የተደረገ ሲሆን ከሳምንታት በፊት ልጆቿ ደም በጠማቸው ፌደራሎች የተገደሉባት ሀረር ከተማም እንዲሁ በበርካታ መስጊዶቿ የዱአ ተቃውሞ ስነ ስርአት አድርጋለች፡፡

የዛሬው ተቃውሞ ላይ የህዝበ ሙስሊሙ ቁጣም ሆነ ቁጥሩ ከወትሮው ጨምሮ የታየበት ምክንያት መንግስት በፈበረከው ድራማ ኮሚቴውን ለመወንጀል የተደረገው የከሸፈ ሙከራ ብቻ አልነበረም፡፡ አሳፋሪው የፕሮፓጋንዳ ፊልም በህዝቡ ዘንድ አንቱታን ያተረፉ ታላላቅ ዓሊሞችን ክብራቸውን እንኳን ባልጠበቀ መልኩ ‹‹ጂሃድ ሰባኪው›› እያለ ከማብጠልጠሉም በላይ ከሽብር ድርጊት ጋር ለማነካካት መድፈሩ በርካታ እናቶችና አባቶችን ክፉኛ አስቆጥቷል፡፡

ከዚህ ቀደም ‹‹መንግስት ትክክል ሊሆን ይችላል›› የሚል ጥርጣሬ የነበራቸው የህብረተሰብ ክፍሎችም በኢቲቪው ቅጥፈት እውነት ከማን ጋር እንዳለች ተገልፆላቸዋል፡፡ የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤት የዛሬውን ጁመዓ ከመቼውም በተለየ በህዝብ ጎርፍ እንዲጥለቀለቅ ያደረገ ሲሆን ትግሉም በምንም ሰውኛ ሃይል ላይነቀነቅ ግዙፍ ህዝባዊ መሰረት መጣሉን አረጋግጧል፡፡ በትናንትናው እለት በሪያድ ተደርጎ በነበረው የአባይ ግድብ የቦንድ ሽያጭ ስብሰባ ላይ የመንግስት ልኡካን የገጠማቸውን ተቃውሞ ስናስተውል ከዚህ በኋላ ለመንግስት ይህ ትግል የማይወክለውን የህብረተሰብ ክፍል ለማግኘት ለናሙናም እንኳ የሚከብደው ግዜ እንዳፈጠጠበት ለመረዳት እንገደዳለን፡፡ ታዲያ መንግስት ከህዝብ ጋር እንዲህ ተጣልቶ መዝለቁ ይበጀዋልን?
ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለም!

አላሁ አክበር!

ECADF.com

Indian investors are forcing Ethiopians off their land

Thousands of Ethiopians are being relocated or have already fled as their land is sold off to foreign investors without their consent

Ethiopia’s leasing of 600,000 hectares (1.5 acres) of prime farmland to Indian companies has led to intimidation, repression, detentions, rapes, beatings, environmental destruction, and the imprisonment of journalists and political objectors, according to a new report.

Research by the US-based Oakland Institute suggests many thousands of Ethiopians are in the process of being relocated or have fled to neighbouring countries after their traditional land has been handed to foreign investors without their consent. The situation is likely to deteriorate further as companies start to gear up their operations and the government persues plans to lease as much as 15% of the land in some regions, says Oakland.

In a flurry of new reports about global “landgrabbing” this week, Oxfam said on Thursday that investors were deliberately targeting the weakest-governed countries to buy cheap land. The 23 least-developed countries of the world account for more than half the thousands of recorded deals completed between 2000 and 2011, it said. Deals involving approximately 200m ha of land are believed to have been negotiated, mostly to the advantage of speculators and often to the detriment of communities, in the last few years.

In what is thought to be one of the first “south-south” demonstrations of concern over land deals, this week Ethiopian activists came to Delhi to urge Indian investors and corporations to stop buying land and to actively prevent human rights abuses being committed by the Ethiopian authorities.

“The Indian government and corporations cannot hide behind the Ethiopian government, which is clearly in violation of human rights laws,” said Anuradha Mittal, director of the Oakland Institute. “Foreign investors must conduct impact assessments to avoid the adverse impacts of their activities.”

Ethiopian activists based in UK and Canada warned Indian investors that their money was at risk. “Foreign investors cannot close their eyes. When people are pushed to the edge they will fight back. No group knows this better than the Indians”, said Obang Metho, head of grassroots social justice movement Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE), which claims 130,000 supporters in Ethiopia and elsewhere.

Speaking in Delhi, Metho said: “Working with African dictators who are stealing from the people is risky, unsustainable and wrong. We welcome Indian investment but not [this] daylight robbery. These companies should be accountable under Indian law.”

Nyikaw Ochalla, director of the London-based Anywaa Survival Organisation, said: “People are being turned into day labourers doing backbreaking work while living in extreme poverty. The government’s plans … depend on tactics of displacement, increased food insecurity, destitution and destruction of the environment.”

Ochall, who said he was in daily direct contact with communities affected by “landgrabbing” across Ethiopia, said that the relocations would only add to hunger and conflict.

“Communities that have survived by fishing and moving to higher ground to grow maize are being relocated and say they are now becoming dependent on government for food aid. They are saying they will never leave and that the government will have to kill them. I call on the Indian authorities and the public to stop this pillage.”

Karuturi Global, the Indian farm conglomerate and one of the world’s largest rose growers, which has leased 350,000 ha in Gambella province to grow palm oil, cereals maize and biofuel crops for under $1.10 per hectare a year, declined to comment. A spokesman said: “This has nothing to do with us.”

Ethiopia has leased an area the size of France to foreign investors since 2008. Of this, 600,000 ha has been handed on 99-year leases to 10 large Indian companoes. Many smaller companies are believed to have also taken long leases. Indian companies are said to be investing about $5bn in Ethiopian farmland, but little is expected to benefit Ethiopia directly. According to Oakland, the companies have been handed generous tax breaks and incentives as well as some of the cheapest land in the world.

The Ethiopian government defended its policies. “Ethiopia needs to develop to fight poverty, increase food supplies and improve livelihoods and is doing so in a sustainable way,” said a spokeswoman for the government in london. She pointed out that 45% of Ethiopia’s 1.14m sq miles of land is arable and only 15% is in use.

The phenomenon of Indian companies “grabbing” land in Africa is an extension of what has happened in the last 30 years in India itself, said Ashish Kothari, author of a new book on the growing reach of Indian businesses.

“In recent years the country has seen a massive transfer of land and natural resources from the rural poor to the wealthy. Around 60m people have been displaced in India by large scale industrial developments. Around 40% of the people affected have been indigenous peoples”, he said.

These include dams, mines, tourist developments, ports, steel plants and massive irrigation schemes.

According to Oakland, the Ethiopian “land rush” is part of a global phenomenon that has seen around 200m ha of land leased or sold to foreign investors in the last three years.

The sales in Africa, Latin America and Asia have been led by farm conglomerates, but are backed by western hedge and pension funds, speculators and universities. Many Middle Eastern governments have backed them with loans and guarantees.

Barbara Stocking, the chief executive of Oxfam, which is holding a day of action against landgrabs on Thursday, called on the World Bank to temporarily freeze all land investments in large scale agriculture to ensure its policies did not encourage landgrabs.

“Poor governance allows investors to secure land quickly and cheaply for profit. Investors seem to be cherry-picking countries with weak rules and regulations because they are easy targets. This can spell disaster for communities if these deals result in their homes and livelihoods being grabbed.”

Oxfam will be placing huge “Sold” signs on the Sydney harbour bridge, the Lincoln memorial in Washington and the Colosseum in Rome to mark its action day.

Ethio Media.Com

ይህ የወያኔ እንስሳዊ ባህሪ እንጂ ሌላ አይደለም !

ኮሚቴዎቻችን መርጠን 3 ጥያቄዎችን በአደራ አስይዘን ወደ መንግሰት አካላት ስንልካቸው ዛሬ እያየነው ያለው የጠነከረ ጭቆና እና ረገጣ ይፈጣራል ብለን አላሰብንም ነበር፡፡ ከአንድ ዓመት በላይ መብታችን ይከበር ድምጻችን ይሰማ እያልን ስንጮህ መንግስት መብታችን ረግጦ ድምጻችንን አፍኖ በተፋጠጥ እየተያየን እዚህ ደረሰናል፡፡ እኛ በቅን ልቦና መንግስት ከዛሬ ነገ ይገባው ይሆናል ጥያቄያችንንም ይመልስልናል በማለት በርካታ ሰላማዊ ተቃሞዎችን ስናደርግ ብንቆይም በመንግስት ስም የተደራጁ ሽፍታዎች ግን ሙስሊሙን ህረተሰብ ሲያምሱት እና ሲያሳቃዩት ቆይተዋል፡፡ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለማጥፋት ቆርጠው ተነስተዋል፡፡ለዚህም የጥፋት ዘመቻቸው ሙስሊሙን ለመምቻነት እንዲያግዛቸው “ኢስለማዊ መንግሰት” ሊመሰርቱ የሚል የውሸት ካባ በሙስሊሙ ላይ ጫኑበት፡፡ ይህን ቅዠት የሆን ፍልስፍና ይዘው ህዝቡ ላይ ሽብር መንዛት ጀመሩ ፡፡  በሀይማኖት ሽፋን ድብቅ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም የሚሞክሩ ጥቂት አክራሪዎች በማለት ህዝቡ እሰኪሰለች ድረስ ቀን በቀን በኢቲቪ አስተጋቡት፡፡ ይህን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ እውነት ለማስመሰል በስርቤት ያሉ ወንድሞች ላይ ከባድ ድብደባ በማድረግ ያልሰሩትን ሰርተናል ብለው እንዲሉ አስገድደዋቸዋል፡፡ የዚህም ግፋዊ ድብደባ የመጀመሪያዎቹ ሰለባዎች በፊርማችን አረጋግጠን ከሞቀቤታቸው አስወጥተን በአደራ የላክናቸው ኮሚቴዎቻችን ነበሩ፡፡

ወያኔ በሚሊዮኖች እውቅና የተሰጠውን ይህን ህጋዊ ኮሚቴ ይዳፈራል ብሎ ያሰበ ማንም አልነበረም፡፡ አይደለም መደብደብ እና ያስራቸዋል ተብሎ እንኳን አይታሰብም ነበር፡፡ ግን ወያኔ ዓላማ የሙስሊሙን ጥያቄ መመለስ ሳይሆን በተቃራኒው ሙስሊሙን ማዳከም እና ማትፋት ስለነበር ግፋዊ ድብደባውን በኮሚቴዎቻችን ላይ ጀመረ፡፡በዚህም ድርጊቱ ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ያለውን ጥላቻ እና ንቄት በግልጽ አሳይቷል፡፡መንግስት ይባስ ብሎ ኮሚቴዎችን ያልሰሩትን ሰርተናል ብለው እንዲናገሩ የስቃይ ማዕበል አውርዶባቸዋል፡፡ የራሱን እኩይ ዓላማ ለማሳካት በወኪሎቻችን ላይ የግፍ ውርጂብኝ አወረደባቸው፡፡ ኮሚቴዎቻችን ቀን ከሌሊት በስቃይ አለጋ ተገረፉ፤ አካላቸውም መንፈሳቸውም ደማ፡፡ ነፍሳቸው ልትወጣ እስክትቃረብ ድረስ ጭካኔ በተሞላበት ድብደባ ተሰቃዩ፡፡ ስቃዩ እጅግ የበረታ ስለነበር በሚደበደቡበት ሰዓት በዚያው ከሞትንም በማለት ሸሀዳ ይሉ ነበር፡፡ በኤሌክትሪክ ሾክ በመግረፍ፤ በፈላ ውሀ ውስጥ በመንከር፡ በኤሌክትሪክ ወንበር ላይ በማስቀመጥ፤ ለረዥም ሰዓታት እንዲቆሙ እና ቁጭ ብድግ እንዲሉ በማድረግ ፤ ከወገባቸው ላይ በተኙበት ከባድ ነገር በመጫን፤ እጅ እግራቸውን በካቴና አስረው በቦክስ እየተቀባበሉ በማሰቃየት መከራቸውን አሳይተዋቸዋል፡፡ የነበው ስቃይ ሞት ምን አለበት ያስብላል፡፡

እንዲህ የሚያሰቃዩቸው “ስንቀሳቀስ የነበረው ኢስላማዊ መንግሰት ለመመስረት ነው ብላቸሁ ተናገሩ በማለት ነበር”፡፡ኮሚቴዎቻችን በመጀመሪያው አካባቢ ይህን ስቃይ ተቋቁመው ቢቆዩም አካላቸው በጣም እየተጎዳ ሲመጣ ግን ስቃዩን ከሚቋቋሙት በላይ ሆነባቸው፡፡ከአካላዊ ስቃይ በተጨማሪ መንፈሳዊ ስቃይም ያደርጉባቸው ስለነበር ሰዉ ናቸውና አቅማቸው እየተዳከመ መጣ፡እንደዚህ እየተሰቃዩ መቆየቱም ለውጥ እንደሌለው ሲገነዘቡ ያልሰሩትን ስርተናል ብለው እንዲናገሩ ቀን ከሌሊት የሚወርድባቸው ስቃይ አስገደዳቸው፡፡ አይደለም በውናቸው በህልማቸው አስበውት የማያውቁትን ነገር ተናገሩ፡፡እነዚያ የስልጣን ግዜያቸውን ለማራዘም ብለው ኮሚቴዎቻችንን ሲሰቃዩ የነበሩት የሚፈለግትን ነገር አገኙ፡፡ይህን እኩይ ሴራ ለህዝብ አስመስሎ ለማቅረብም በቪዲዮ ካሜራ ቀረጹት፡፡ አሳፋሪው መንግስትም ይህን በድብቅ እና በግዳጅ የተቀረጸ ቪዲዮ በመቆራረጥ እና ከሌሎች ቪዲዮች ጋር በማገናኘት እጅግ አሳፋሪ የሆነና ከእውነት ፍጹም የራቀ የሆነ ዶክመንታሪ ፊልም በማሰራት ለህዝብ ለማቅረብ ወስኗል፡፡
እጅ እግር አስሮ በኤልክትሪክ ሾክ በመግረፍ እና የፈላ ውሀ ውስጥ እየነከሩ በመደብበድ ያልሰሩትን ሰርተናል እንዲሉ ማድረግ ወንድነት አይደለም፤ ጀግንነትም አይደል፤ ይህ የወያኔ እንስሳዊ ባህሪ እንጂ ሌላ አይደለም ፡፡ ማንኛውም ሰብዓዊነት የሚሰማው ሰውም ይሄን ድርጊት አያደርገውም፡፡ ይሁን እንጂ በመንግሰት ስም የተደራጁ ሽፍቶች በኮሚቴዎቻችን ላይ አሰቃቂ ድብደባ ፈጽመውባቸዋል፡፡ እኛ ኮሚቴዎቻችንን እና ወንድሞቻችንን ከማንም በላይ እናውቃቸዋለን፡፡ ስቃዩ ካቅማቸው በላይ ሆኖ ያልሰሩትን ሰርተናል ብለው ሲናገሩ ብንሰማቸው በነሱ ላይ ሲደረግ የነበረው የስቃይ መዓብል ምን ያክል ከባድ መሆኑን እንድንረዳ ደርገናል እንጂ ኮሚቴዎቻችንን በሌላ እንድናስባቸው አያደርገንም፡፡ ስቃዩ ምን ያክል ከባድ እንደነበር ከኮሚቴዎቻችን ፊት ገጽታ ላይ ይነበባል፡፡ በኮሚቴዎቻችን ላይ ይታይ የነበረው የፊታቸው ኑር ዛሬ ገርጥቶ እና ጠቁሮ ስናየው ውስጣችን ይቃጠላል፡፡

መንግሰት ያለ መስሎን ለሽፍቶች ሰጥተን አስደበደብናቸው ፡፡ አካላቸው ከስቶ እና ተጎሳቆሎ፤ ያዬ  በወኔ የተሞላ ንግግራቸው ዛሬ ከጆራችን ሲርቅ ልባችን በሀዘን ዓይናች በደም እንባ ይታጠባል፡፡

የወያኔ  መንግሰት ጠላትነቱን ከመቼም ግዜ በበለጠ አረጋግጦልናል፡፡ ገደለን፤ አሰረን ፤ አሰቃየን፤ አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ እጅግ አስናዋሪ የሆነ የሀሰት ፊልም በመስራ በአደባባይ ስማችንን ሊያጠፋ እና ክብራችንን ዝቅ ለማድረግ ተዘጋጅቷል፡፡ መንግሰት የኮሚቴዎቻችን እና የህዝበ ሙስሊሙን ክብር በሚያንቋሽሽ መልኩ የሀሰት ፊልም በማዘጋጀት ጠላትነቱን በግልጽ አረጋግጦልናል፡፡ ከዚህ በላይ ምንም ሊያደረገን አይችልም፡፡ ገድሎናል፤ አስሮናል አሰቃይቶናል፡፡ አሁን ግን ከግድያ በባሰ መልኩ ተወልደን በኖርንባት ሀገራችን ተዋርደን እና ተሸማቀን እንደንኖር ወይም ሀገር ለቀን እንድንሄድ እያስገደደን ይገኛል፡፡ ያለስማችን ስም በመለጠፍ ያለ ስራች ስራ በመስጠት ተሸማቀን እንደንኖር አድርጎናል፡፡ ይህንም ነገ ማክሰኞ በአደባባይ በማውጣት በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ ያለውን ንቄት ዳግም ሊያሰዩን ተዘጋጅቷል፡፡በአደባባይ ኮሚቴዎቻችን ሲያንቋሽሹ ማየቱ ምን ያህል ያሳምማል፡፡ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በአደባባይ ሲሰደብ መስማቱ ምን ያህል ልብ ያቆስላል፤ በጣም ልባችን ቆስሏል፤ ትዕግስታችንም እየተሟጠጠ መጥቷል፡፡

ስለሆነም ብዙ እየተባለለት ያለው ይህ አዲስ ፊልም ከመውጣቱ በፊትና በኋላ በመላው አገሪቱ ያሉ ሙስሊሞች ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ለክርስቲያን ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ፍቅር እንዲሰጡና ኢህአዴግ ሊፈጥረው ያሰበውን የጥርጣሬ አመለካከት መስበር እንደሚገባ ጠንቅቀን ማወቅ ይኖርብናል ። ከዚህ  በተጨማሪ መላው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አምባገነኑ የወያኔ  መንግሰት  የሚያደርግብንን እጅግ አስቀያሚ ሴራ ተረድተን ሁላችንም ከሌሎች  ወገኖቻችን ጋር በመተባበር በቁርጠኝነት ለመታገል ከልባችን ቆርጠን መነሳት ይኖርብናል፡፡ በእርግጠኝነት እስከ ህይወታችን ፍጻሜ እንፋለማቸዋለን !!! በትግላችን ላይ አሏህ (ሰ.ወ) ጽናቱን እና ብራታቱን እንዲሰጠን በመጨረሻም ድሉን እንዲያጎናጽፈን አጥብቀን እንለምንዋለን ፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

Maleda times

Federalism or Internal Colonialism-the Ethiopian situation.

By Yilma Bekele

“The tragic reality of today is reflected in the true plight of our spiritual existence. We are spineless and cannot stand straight.“  Ai Weiwei – Chinese dissident.

As a concept there is nothing wrong with Federalism as a system of government. There are plenty of examples of such arrangement like as in the USA, Canada, Germany, Mexico and India among others where it has shown to work. That is the system TPLF under Meles and company told the Ethiopian people that they are attempting to construct. It has been over twenty years now since the work has started and the question in front of us is, how is it going?

How is Federalism working in our country? I will tell you about a specific powerful institution in Ethiopian and you the reader, be the judge. The governmental body I have in mind is one of the most important and key sector of our economy and it is currently named Ethio Telecom. Here is a brief description of the history of the telephone in Ethiopia.

The first telegraph line was between Harar and Addis Abeba in 1889. Emperor Haile Sellasie established the Imperial Board of Telecommunications of Ethiopia in 1952. Derge reorganized it as Ethiopian Telecommunication Service and later on as Ethiopian Telecommunications Authority (ETA) in 1976 and 1981. In 1996 TPLF replaced that with Ethiopian Telecommunications Corporation. It was born again as Ethio Telecom in 1910. The Ethiopian Telecommunications Corporation is the oldest Public Telecommunications Operator (PTO) in Africa. (http://en.wikipedia.org/wiki/Telecommunications_in_Ethiopia)

In our country Ethiopia the Federal Government owns the country including resources, land and most of the vital economy. Communication tools such as television, radio, telephone and Internet are fully owned and operated by the Federal Government. The Ethiopian government is the number one employee in the country. Controlling all this assets give the Federal Government total power on every aspect of the people and country. For the Woyane regime Ethio Telecom is a weapon to amass large amount of money, spy, control, create anxiety and bully the citizen. How TPLF was able to control ETC is the story of what happened to our country. The group known to us as TPLF organized as an ethnic based party took over the political, economic, security sectors of the country called Ethiopia in a very systematic and deliberate way.  This assertion can be proved in more ways than one cares to count. Please read Ginbot7 publication on the domination of the military by Tigrean ethnic group. (http://www.ginbot7.org/the-ethiopian-military-leadership-under-haile-selassie-and-derg-regimes/)

Ethio Telecom is another key sector of the economy and a very powerful weapon that was targeted by TPLF for complete take over. How they were able to do that is the history of what happened to the rest of the country. Ethio Telecom encompasses the trial and tribulations of our country and people. In my opinion Ethio Telecom is where Weyane’s star shined.

It took TPLF for years (1991 -1995) to figure out the inner workings of such a large and old organization. In 1996 they restructured it as a Corporation and were able to get rid of ‘trouble makers’ and install their own people in key positions. Its importance did not manifest until around 2000 with the advent of the World Wide Web.  Before that TPLF was content collecting spare change. The Internet changed the whole ball game. Communication became the driving force of change. As a totalitarian regime highly motivated to control the flow of information the TPLF saw the dangers of unrestricted access to information and knowledge.

In 2010 Ethio Telecom emerged. The birth of Ethio Telecom was a painful moment in the history of our country. People were played upon, dangled around, set against each other and humiliated. Such a powerful and modern organization in the life of our country was made to look like a failed and useless outfit. The twelve thousand strong body was completely dismantled by the TPLF. Guess who was in charge of this tragedy. None other than current Deputy Prime Minister Dr. Debretsion. He was the architect and enforcer of this desecration of an Ethiopian home grown building block.

To avoid doing the dirty job TPLF gave management services to a subsidiary of French Telecom – Orange (telecommunications). Orange is a third rate multi- national corporation and an easy prey for TPLF to push around. Without input from the workers, without consulting those affected Orange and the TPLF Politburo said ‘we got a deal you cannot refuse.’  They created five categories named N1-N5. N1 included the French team and Ethiopian management personnel. Over half of the twelve thousand employees were dumped on the road side. There was no explanation, no discussion and no review. One of those that was found to be superfluous was the head of the Union Ato Adisse Bore. You see the beauty of Woyane justice? There was no one left to speak for the workers! You can tell the whole idea was nothing but a naked assault on our people when you see that among the personnel the new organization is purported to keep the list included some dead and some on exile.  This is how Ethio Telecom was born.

Why do you think Ethio Telecom is a prized asset of the minority TPLF regime? It is because communications is the key to the future. The media opens our eyes to situations and places we will not even dream of. The media is the first causality of a repressive regime. Do you notice the first target of any coup d’état is the control of the radio and television transmission sites?  Ethio Telecom is the gate keeper. Ethio Telecom sustains the dictatorship.

Thus they got rid of half of the employees of ETC and made it in their own image. They trained a few, they imported a few of their own from the Diaspora and they either blackmailed or bought the rest. Today Ethio Telecom is a cash cow to the dictatorship and a very powerful security apparatus to safeguard a few while abusing the many.  Here is the composition of the N 1 Group managing the enterprise they established.

Please let us keep it real here. This is not some one’s imagination gone haywire, nor a just made up figure. It is real and we treat it as such until proven otherwise. Is this what federalism is all about? Ethnicity is the corner stone of Woyane rule. The above chart is based on Woyanes’ own classification of our people.

This investigative study at its best came out two weeks ago. Fellow Ethiopians took time and effort to find and compile such information so we can have a clear view of the actual situation in our homeland. As they say talk is cheap but facts speak for themselves.  After all is said and done the above picture does not lie. It is based on the TPLF’s definition of who is who in today’s Ethiopia.

Why do you think the TPLF regime under Debretsion finds communications important enough to control as a monopoly? It is because communications is the key. Leaders like Meles and now Debretsion are aware of the value of information. They are spin doctors. When it comes to a closed society like ours they make sure they are the only source of information. Our country Ethiopia is the last in any measure of technological advancement, why do you think that is so? They don’t allow it, they don’t foster it, and they don’t encourage it because the more we know the less we think of them.

The Federalism TPLF is building in our country is Apartheid. In the former South Africa the 9.6% white ruled over the 79% black population. In Ethiopia, today the 6.1% from Tigrai region are dominating the economic political and military life of the country. This is a very difficult statement to make and it is a very ugly thought to cross one’s mind. But it is also unfair and being a coward not to face reality. The situation in the military, the situation in Ethio Telecom is not something to ignore. It did not happen by accident. The TPLF party in a deliberate and callous manner created this Apartheid system in our country. The above pie chart showed the so called N 1 group in higher management what do you think N 2 looks like?

Knowledge is power. Knowing what the TPLF party is doing to our country and people helps us realize the problem, discuss the ramifications if left to continue and find a lasting solution so we can all move forward as one people. Uncovering such crime is not ethnic bating. Discussing such unfair and ugly reality is not hating on individuals or groups. It is real and it has to be dealt with. Dr. Debretsion and his friends have to answer why there is such naked discrepancy in the organization they are entrusted to administer in the name of the people. They have to explain to us the people why there are more from their own ethnic group in position of real power and influence than the rest. Is it because they couldn’t find a Gambelan, a Sidama, a Kenbatan, an Oromo or an Amhara to fill such slots? If there is a reasonable explanation we are all ears but changing the subject or accusing one of ethnic bating is not the way to go.

Now they have inserted their own people in key positions what do you think they are doing with the new and improved Ethio Telecom? Are they using it to connect the country, use the new found digital technology to jump start our economy and education system and usher an era of peace and prosperity? I am afraid a mind that relies on ethnicity and village mentality to get ahead cannot be expected to soar like an eagle but slither like a snake biting all that crosses its path. That is exactly what Ethio Telecom is, a venomous snake attacking our people and country every chance it gets. Check out our double digit growing economy.

Country Population Mobile Phone Internet users %population
Ethiopia 90 M 18 Million 960,000 1.1
Kenya 43 M 28.08 Million 12 Million 28
Ghana 24.6 M 21.1 Million 3.5 Million 14.1
Sudan 34.2 M 25 Million 6.4 Million 19

It is clear the regime is not interested in using the new technology to help our country join the community of nations. No question ethnic mentality and government monopoly stifles innovation, kills individual initiative and keeps our people in darkness. Here is a finding by Reporters Without Borders (RWB).

“Ethiopia’s only ISP, State owned Ethio Telecom has just installed a system for blocking access to the Tor network, which lets users browse anonymously and access blocked websites. In order to achieve such selective blocking Ethio Telecom must be using Deep Packet Inspection (DPI) an advanced network filtering system.”

Think about it, the ruling junta is willing to invest such huge amounts of money to spy on its citizens instead of using the money to wire schools and libraries. They use Chines technology to block any and all Internet, radio and our ESAT news broadcast. The few decide what is good for the many. It is not healthy. It does not end well. We have seen what a single ethnic domination does to people and country. Rwanda was just yesterday and South Africa will suffer the legacy of Apartheid for decades to come. The current arrangement in our country will not ensure a strong and vibrant Ethiopia where her children will prosper under one roof but rather a weak and divided Ethiopia that one day will fall prey to outsiders that will exploit the division.

At the beginning of this article I quoted the Chinese dissident Ai Weiwei speaking about the character of his people suffering under the totalitarian system. We in Ethiopia should know exactly what he is talking about. Under the weight of TPLF abuse we harbor deep seated animosity towards each other, instead of fighting the common enemy we point fingers at each other. There is no association, organization club where we Ethiopians relate to each other with respect and dignity. Our political organizations have become places of division. Even our church is not immune from this sickness. We see our Muslim brother resisting and we learn the power of steadfastness and unity of purpose. That is one group of citizen with anti Woyane virus shot.

One fact that should be made clear is that the TPLF party is not practicing this criminal behavior all by itself. We have to look at the enablers that grease the wheels to hurt our own people and destroy our country. Those Amharas’, Oromos’, Wolaitas’, Tigreans’, Hararis’ and others in position of marginal power and the willing Diaspora that invests on stolen land and fake buildings are part of this national degraedation. What are you going to tell your children when Ethiopia becomes another Somalia, the future Iraq or a dying Syria? When they ask you why didn’t you do something daddy or mommy how are you going to answer? You cannot say I did not know because that would be a lie. You cannot claim I tried because that would not be true. No one would say I did not stand up straight because I am spineless. When you go to sleep tonight think about it, please?

 

This article is based on the following works:

http://abbaymedia.com/2013/01/19/ginbot7-exposes-the-weyanes-ethnic-aparthied-in-ethiopian-telecom/

http://www.bloomberg.com/news/2012-10-11/zte-huawei-to-be-awarded-ethiopian-telecommunications-contracts.html

http://www.redress.cc/global/gpeebles20120619

http://apperi.org/2013/01/14/world-bank-advised-ethiopia-to-audit-large-telecom-agreements/

http://www.ethiopianreview.com/content/38649

http://www.internetworldstats.com/stats1.htm

http://www.thereporterethiopia.com/News/ethio-telecom-layoff-union-president-employees.html

 

 

 

 

 

 

 

 

 Abbay media.com

የሌለ ዲሞክራሲ ይሰጣልን?

ከይኸነው አንተሁነኝ
የካቲት 4 2013

ከታላቋ ሩሲያ መከፋፈልና ከኮሚኒዝም ርዕዮተ ዓለም መንኮታኮት በሗላ ጥቂት የማይባሉ ሀገሮች እና ለለውጥ እንታገላለን ሲሉ የነበሩ ድርጅቶች መመሪያችን ነው እያሉ ሲያመልኩት የኖሩትን የሶሻሊዝም አይዲዮሎጂ፤ የተናገሩት ሳያቅራቸው የጻፉት ሳያሳፍራቸው ባንዲት ጀንበር እርግፍ አድርገው፤ ጥቅም እስከተገኘ ድረስ በሉ የተባሉትን ለማለት ሁኑ የተባሉትን ለመሆን ተሯሯጡ። እጃችሁ ከምን እያሉ ሲያባብሏቸው የነበሩትን የትላንት ወዳጅ መከታ ሀገሮችን ረሱ። ሌላው ቀርቶ በየድርጅቶቻቸው ውስጥ ይሰጥ በነበረው ርዕዮት ያጠመቋቸውን የራሳቸውን አባላት ልጆቻቸውን ጭምር ክደው እንደ እስስት መልካቸውን ቀየሩ። እጅግ የከፉት እንደ ወያኔ ያሉት የጎጥ ድርጅቶች ደግሞ ስለ ለውጡ እንዴትነት የጠየቋቸውን የራሳቸውን ጓዶች ሳይቀር ቅርጥፍ አድርገው እየበሉ አሁን ላሉበት ደረጃ ደረሱ።

በአጥቢነት ላይ በራሪነትን ደርባ እንደለበሰችው እንደ ሌሊት ወፍ በእውነተኛው ኮሚኒስት ማንነታቸው ላይ ደርበው ግን ዲሞክራሲያዊነት መርሃችን ነው የሚሉት ወያኔዎች፤ ምንም እንኳ ጥቂት የማይባሉ የዲሞክረሲ መርሆችን ፖሊሲዎቻቸውን በከተቡበት ወረቀት ላይ ለማስቀመጥ ቢሞክሩም፤ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በደርዘን ለሚቆጠሩ ጊዜያት ኮሚንስታዊ አምባገነንነታቸውና አፋኝነታቸው በግልጽ ሲጋለጥባቸው እንደቆየና አሁንም እየተጋለጠ እንደሆነ የማይታበል ሀቅ ነው።

በደርግ የአምባገነን አገዛዝ ተረግጦ ሲገዛ ለነበረው ሕዝባችን ዲሞክራሲን ይዘንልህ መጣን ያሉት ወያኔዎች፤ በወያኔ መንደር በተለያዩ ቦታዎችና በተደጋጋሚ ከተነሱት የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ጋር አብሮ ለመጓዝ ወይም በተቃራኒው ለመንቀሳቀስ ሕዝባችንን ያልሆነውንና የማይፈልገውን እንዲሆን በጉልበት አስገድደዋል። ሕዝባችን ወዶ ያደረገውን ፈልጎ የፈጸመውን ድርጊት በግፊትና በተጽእኖ እንዳደረገው በመስበክ የእኛ እናውቅልሃለን አፈናቸውን ፈጽመዋል። በጥቅሉ በዲሞክራሲ ስም ኢድሞክራሲያዊነታቸውን አሳይተዋል።

በአንዲት ሀገር የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት ውስጥ የዜጎች መሰረታዊ ብቶች የሆኑት የመጻፍ፣ የመናገር፣ የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ መረጃ የማግኘት እና የሌሎችም ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበር የሚጠበቅ ነው። እነዚህን ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸው የሆኑትን እንእስቃሴዎች በማድረጋቸው ዜጎች ሊሳቀቁና ሊዋከቡ አይገባም። ይልቅስ ለዝግጅታቻቸውና ለእንቅስቃሴዎቻቸው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን ከማሟላት ጀምሮ በእንቅስቀሴው ወቅት ደረጃውን የጠበቀ ጥበቃ ማድረግ ከሀገሪቱ መንግስት ይጠበቃል። ይህ እንግዲህ ለሚያስተዳድሯቸው ሕዝቦች በእውነት የመንግስትነትን ስራ እየሰሩ ላሉ መንግስታት ነው። የኛው ሀገር ወያኔ ግን በዲሞክራሲ ስም አፈናን ግፍን አሰፋፍቷል። በመናገርና መጻፍ መብት ስም የወያኔን ፖሊሲዎችና አጠቃላይ አሰራሩን ተችተው የተናገሩትንና የጻፉትን አስሯል አሳዷል ገድሏል። መረጃን ለሕዝብ በማድረስ ስምም መድረስና መሰማት ያለባቸውን መረጃዎች ሳይሆን የወያኔን ፐሮፖጋንዳ በሁሉም ሬዲዮዎችና ቴሌቪዥኖች ሲሰብክ ከርሟል።

በወያኔ አሉታዊ ተግባር ወያኔ ያጸደቃቸውንና በጽሁፍ ላይ ብቻ የሚገኙትን መብቶች በመጥቀስ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ያልቻሉት ብርቅዬ ዜጎቻችን፤ በስደት ዓለም ጠንክረው በመንቀሳቀስ በራሳቸው ግለሰባዊ ወጭ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ማሰራጫዎችን ከፍተው የወያኔን ጠባብነት፣ ከፋፋይነትና ሀገር አጥፊነት በማጋለጥ ላይ ቢሆኑም እጀ ረዥሙ ወያኔ ግን ውቅያኖስ ተሻጋሪ ሴራውን ልሳኑ በሆነው ትግራይ ኦን ላይን በኩል እየሰነዘረ ይገኛል።

በውጭ የሚገኙት ወገኖቻችን የመናገር መብታቸውን ተጠቅመው ካቋቋሟቸው ማሰራጫዎች አንዱ በሆነው ኢሳት ሬዲዮና ቴሌቪዥን አማካኝነት ድምጽ ለሌለው ሕዝባችን ድምጽ ለመሆን እየሰሩ ባሉበት በዚህ ወቅት፤ ወያኔ ግን ሃሳብን በሃሳብ በመታገል ፋንታ በተካነው የመከፋፈልና እርስ በርስ የማጋጨት ጥበቡ፤ በኢትዮጵያዊነቱ ክርክር የማያውቀውን የትግራይ ሕዝብ ከተቀረው የሀገሪቱ ሕዝብ እና ከብቸኛው የኢትዮጵያ እውነተኛ ድምጽ ኢሳት ጋር ለማጋጨትና ያልተከለሰ እውነተኛ መረጃ እንዳያገኝ ለማድረግ በርትቶ እየሰራ ይገኛል። ወያኔ በትግራይ ሕዝብ ለመነገድ ትግራይን የበላይ ሌሎችን ብሕሮች ተከታይ አድርጎ ለማሳየት ሞክሯል። ወያኔ ሌላ የሚለው ብሔርም በማንነቱ እንዲያፍር፣ በሃይማኖቱ ለዘብተኛ እንዲሆንና ብሔራዊ ስሜቱም እንዲቀንስ ለማድረግ ጥሯል። የተዛባ፣ ያልተጠናና መሰረት የሌለው የፖለቲካ አካሄድን በመከተልና ዳር የወጣ ጠባብ ዘረኝነትን በማራመድ ወደፊት መቋጫ የሌለው የእርስ በርስ ትርምስ እንዲፈነዳ በርትቶ እየሰራ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪም ወያኔዎች ምንም እንኳ ከትግራይ ክልል የወጡም ቢሆኑ አገዛዙን የተቆናጠቱት ጥቂት ጉጅሌዎች ብቻ በሃብት፣ በስልጣን፣ በትምህርትና በመሳሰሉት ይጠቀሙ እንጅ ሂዎት ለተቀረው የትግራይ ሕዝብ ግን እንደተቀረው ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሽህ ቢታለብ ያው በገሌ መሆኑን የትግራይ ሕዝብ አሳምሮ አውቃል።

ይህን ያልተረዳው ወይም ሆን ብሎ ለመረዳት ያልፈለገው ወያኔ ግን አሁንም የጠባብ ዘረኝነት ድሪቶውን በትግራይ ሕዝብ ላይ ለመጫንና ከውጤቱ ተጠቃሚ ለመሆን እየሞከረ ይገኛል። የትግራይ ሕዝብ ግን እየደረሰበት ያለው ግፍና መከራው በተነሳለት እንጅ እውነተኛው ወገኑ ማን እንደሆነ ለማወቅስ በትግራይ ሕዝብ ስም እንደሚቀልደው እንደ ትግራይ ኦን ላይን ያለ አስተማሪ ባላስፈለገውም ነበር።

አውነት በተነገረ ቁጥር ማስፈራራት የሚቀናው ሚስጥራዊው ጎጠኛ ድርጅት ወያኔ የሚስጥር ጓዳው ሲበረበር ቢያብድ የሚያስገርም አይሆንም። ምክንያቱም እጅግ ሚስጥራዊ ከመሆኑ የተነሳ ዓለም የሚያውቀው መልኩና እውነተኛው ሚስጥራዊ ማንነቱ እጅግ የተለያዩ ነቸውና። በዚህ የተነሳም ይህ ሳምንት እውነተኛ ግለሰቦችና ኢሳትን የመሰሉ የዜና ድርጅቶች እውነትን በመናገረቸው ሚስጥርን በማጋለጣቸው ብቻ ማስፈራሪያ እየተላከላቸውና እየተጻፈባቸው ያሉት። ወያኔዎችም በዚህ መልኩ የዲሞክራሲ መብቶቻችንን የመርገጥና የማፈን እርምጃዎችን ቢቀጥሉም ትግላችን ግን እጅግ በበረታና በተጠናከረ መልኩ ቀጠለ እንጅ አላቆመም።

ecadf.com

“ጂሃዳዊ ሀረካት”፡ ሳይተወን የከሸፈ የወያኔ ድራማ

ሕውሃት ከጥንስሱ ጀምሮ የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪዎችን የዘር ታርጋ እየለጠፈ አንተ አማራ ነህ፤ ኦሮሞ እንዳያጠፋህ ቀድመህ አጥፋው፡ አንተ ስልጤ ነህ ጉራጌ እንዳያንሰራራ ቀጥቅጠው፡ አንተ ትግሬ ነህ አማራ ጠላትህ ስለሆነ ዘሩን አጥፋው በሚል አስተምሮት የተቃኘ እና ህዝብን በህዝብ ላይ በማነሳሳት፤ በማጋጨት እስካሁን ስልጣን ላይ መቆየቱን የማይረዳ ኢትዮጵያዊ ባሁኑ ሰዓት ሊኖር እንደማይችል አፌን ሞልቼ መናገር እችላለሁ።“ጂሃዳዊ ሀረካት”፡ ሳይተወን የከሸፈ የወያኔ ድራማ

የትግሬ ነጻ አውጭ ድርጅት ፕሮግራም እንዳሰቀመጠው መጀመሪያ ጠላት አርጎ የወሰደው አማራን ነው፡ ከዚህም በመነሳት በሚሊየን የሚቆጠሩ አማርኛ ተናጋሪዎችን መፍጀቱ ይታወቃል። ከዘር ቀጥሎ የወያኔ የመከፋፈያ ስልት ሓይማኖት መሆኑን እና ለዚህም እንዲጠቅመው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን በነታጋይ ጻውሎስ ተቆጣጥሮት እንደነበረና አሁንም ሌላ ካድሬ በመመልመል ላይ መሆኑን የማናውቅ የለንም። የክርስትና ሃይማኖትን እንደተቆጣጠረው ሁሉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችንም ለመቆጣጠር ባዘጋጀው ሰፊ ዝግጅት የእስልምና እምነት ምን መሆን እንዳለበት እስልምና ተከታይ ወገኖቻችን ላይ ሊጭን ሲሞክር ሓይማኖቴን አንተ አትጭንብኝም በማለታቸው፤ ተገለዋል፤ ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ተደብድበዋል፡ ይህ በግልጽ የምናውቀው ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው፡:

አሁን የኢትዮጵያ ህዝብ በገሃድ የሚያወቀውን ሃቅ ወያኔ ከምን ተነስቶ ነው እስልምና ተከታዮች ክርስቲያኖችን ሊያጠፉ ነው የሚለውን ድራማ ይቀበሉኛል ብሎ ያሰበው?አማራንና ኦርቶዶክስ እስከወዲያኛው እንዳያንሰራሩ አጥፍተናቸዋል እያሉ በእብሪት የሚያናፉት እነ ሳሞራ ዩኑስ፤ ስበሃት ነጋ እና ሌሎችም ወያኔዎች አደሉም እንዴ? አሁን ከየት መተው ነው ለክርስትና እምነት ተከታዮች ጠበቃ ነን ለማለት የሚቃጣቸው? ነው ወይስ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልነውን ሁሉ የመቀበል ግዴታ አለበት ከሚል ግልብ እብሪት የተነሳ ነው?

መላ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ አገር ውስጥም ሆነ ውጭ ያለኸው፡ ወያኔ በበረከት ስምኦን ተደርሶ ማክሰኞ ባፈ ወያኔ ቴሌቪዥን ጣቢያው ሊያሰተላልፈው ያሰበውን “ጂሃዳዊ ሃረካት” የሚለውን ሰቆቃዊ ተውኔት ተከታተሉት ቀርጻችሁም አስቀምጡት፡ ለነገሩ ሚሰጥሩ ቀድሞ ህዝብ ጆሮ ስለደረስ ላያስተላልፈው ይችላል። ወያኔን ሰምታችሁ የሚለውን እንደማትቀበሉ በጣም እርግጠኛ ነኝ፡ ግን ከዚያች ቀን ጀምሮ የእስልምና ተከታይ ወገኖቻችሁ የሚያደርጉት ትግል እንድትቀላቀሉ አደራ እላለሁ።

እስልምናና ክርስትና እምነት ተከታዮች አትዮጵያ ውስጥ አብረው የኖሩት  ከአንድ ሺ ዘመን በላይ ነው፡ በነዚህ ዘመናት እስልምናና ክርስትና ባላቸው የመቻቻል እና የመከባበር ባህል ለአለም አርአያ ሲሆኑ እንጂ እርስ በርስ ሲተራረዱ አላየንም አልሰማንም፤ ታሪክም አልዘገበውም። ትናነት የመጣ ወያኔ ያውም የባንዳ ወንጀለኞች ጥርቅም ነው እስልምና ተከታዮች ክርስቲያኖችን ሊያርዱ ነው የሚለን? የወያኔ ፌዝ እዚህ ላይ ይቁምና ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን ይህንን ያገር ነቀርሳ ማሰወገድ
መቻል አለብን፡

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ

እስከ ነጻነት

 

ሰራዊታችን ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ፡ ብዛት ያላቸው ሴት ታጋዮችም ግንባሩን ተቀላቀሉ!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ነበልባል ጦር ጥር 17-2005 ዓ.ም በወልቃይት ጎብለል በተሰኘ የወያኔው መከላከያ ካምፕ ላይ በወሰደው ድንገተኛ ማጥቃት በካምፑ የሚገኙ የመከላከያ አባላትን ደምስሷል። በውጤቱም 25 ሙት 36 ቁስለኛ እንዲሁም  20 ክላሽንኮፍ ጠብመንጃ ፣ 4 የእጅ ቦንብና 1 ስናይፕር ጠብመንጃ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመማረክ በማግስቱ ማለትም በትናንተናው እለት በቀጠለው የነበልባል ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት በወልቃይት ጠበቆ በተባለ ቦታ 24 የአገዛዙ ታጣቂዎች ሙትና 29 ቁስለኛ ሆኗል። በድምሩ በሁለት ቀናት ውጊያ በጠቅላላው 49 ሙት 65 ቁስለኛ ሲሆን፦ የአምባገነኑ አገዛዝ ሰራዊት የአርበኛውን ጡጫ መቋቋም ተስኖት እግሬ አውጭኝ ብሎ ከመፈርጠጡም ባሻገር የውጊያ ሞራሉ ክፉኛ በመዳከሙ ምክንያት በአድጎሹ ፣ አደባይ፣ሁመራና እድሪስ አካባቢ የሚገኙ የጦር አመራሮች በመሰባሰብ የመልሶ መቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደተወጠሩ ታውቋል።

ነበልባል በመባል የሚታወቀው ልዩ ኮማንዶ የኢህአግ ሰራዊት በአርማጭሆ፣ ጠገዴና ወልቃይት ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት በመፈፀምና ሕዝቡን በማንቃት እንዲሁም በማስታጠቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ሴት ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ያሉበት በርካታ ወጣቶችን ወደ ትግሉ ጎራ እንዲቀላቀሉ አስችሏል።

ግንባሩን በጥር 18-2005 ዓ.ም የተቀላቀሉ ሴት አርበኞች የወቅቱን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያም እኛ ሴቶች አገራችን ኢትዮጵያ አይታው በማታውቅ ሁኔታ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው መስክ አዘቅት ውስጥ እንደምትገኝ አብራርተው የእነሱ የትጥቅ ትግልን የመጨረሻ አማራጭ አድርገው የደም፣ የአጥንት፣ የጊዜ፣ የጉልበት፣ የእውቀት ብሎም የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን ለመቀላቀል ኢትዮጵያዊነት ስሜታቸውና ሕሊናቸው እንዳስገደዳቸው በመግለፅ መላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ዘር፣ ቋንቋ፣ ሐይማኖትና ፆታ ሳይለይ ከትግሉ ጎራ በመሰለፍ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ከጥፋት ሃይሉ የእብሪተኛ ቡድን የምናላቅቅበት ወቅት አሁን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርን በጥር 18-2005 ዓ.ም የተቀላቀሉ ሴት አርበኞች አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር

 ecadf.com

የሃይማኖት መብቶች እንዲከበሩ ለሁሉም መብቶች የመታገያ ግዜው አሁን ነው!

ፍትህ፣ ነጻነት፣ እኩልነትና አንድነት የብዙ ሃይማኖቶች መሰረታዊ መርህ  እሴቶች ናቸው። እነዚህ ቲውፊቶች ለአለፉት 20 አመታት በዘረኛው ወያኔ እየተሸረሸሩና እየመነመኑ ዛሬ ከእነ አካቴው በሀገራችን ኢትዮጵያ ስለመሰረታዊ የሰው ልጆች መብት ነጻነት እንዳይወራ፤ ወያኔ የጥይት አፈ ሙዞች በእያንዳንዱ የህዝብ አገልግሎት ተቋማት ላይ በመደቀን የአምልኮ ቦታዎችን ሳይቀር በመዳፈር ህዝበ ምእመናኑ የእኔ የራሴ የሚለው የአምልኮት ቦታ እና ህግ እንዲያጣና እንዳይኖረው እያደረገ ነው።

በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቀን ወደቀን እየተባባሰ የመጣው የእምነት ነጻነት እጦት ሁላችንንም ሊያሳስበን እና ሊያስተሳስረን የሚገባበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። በተለይም በታሪካችን፡ የኢትዮጵያ ህዝብ በእምነት፣ በዘር፣ በፖለቲካ እስከ ቅርብ ጊዚያት ድረስ ሳይለያይ ተከባብሮና ተሳስቦ የሚኖር ህዝብ እንደሆነ የማይካድ ሃቅ ነው።

ይሁን እንጅ ከቅርብ ግዜ ወዲህ አምባገነኖች በፈጠሩት ህገ- አራዊት በሆነው የከፋፍለህ ግዛ እና የአንድ ዘር የበላይነት ፖሊሲ አማካኝነት የምንወዳት ሀገራችን ኢትዮጵያ፤ አበው ለአንድነቷ፣ ለህልውናዋ የሞቱላት፣ ዘውግ፣ ቋንቋና የሃይማኖት ልዩነት ሳያግዳቸው የገነቧት እማማ ኢትዮጵያ፤ የልጆቿ የኤሎሄ ማሰሚያ ስፍራዎች፣ ተቋማትና የገዳማት አባቶች በህወሃት የጥፋት አለንጋ እየተገረፉ ናቸው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን 4ኛውን ፓትርያርክ ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ ከእምነቱ ቀኖና ህግ ውጭ በሆነ መንገድ ህጋዊውን ፓትርያርክ በማባረር በዘረኛው የወያኔ አስተዳደር ስርአት ውስጥ በማስገባት አባ ጳውሎስ እስከሞቱበት እለት ድረስ እና አሁንም ምእመናኑ በመከፋፈል የተሳካላቸው ወያኔዎች፤ በቅርቡ ሊደረግ የነበረውን የእርቀ ሰላም ሂደት በወያኔ ጀሌዎች እንዲሰናከል የስርአቱ አገልጋይ አባቶች የሆኑትን፤ ልሳናቸውን በመጠቀም የኦርቶዶክስ ተዋህዶን እምነት አሁንም በወያኔ ቁጥጥር ስር ሆና እንድትመራ የተደረገው አሳዛኝ ክስተት አንዱ ነው።

ወያኔ አንግቦ የተነሳው አላማ፤ ዜጎች በዜግነታቸው በሚኖሩበት ሀገር  ምንም አይነት ነጻነት እንዳይሰማቸው፣ የጥቃት ሰለባዎች እንዲሆኑና የዜጎች የማምለክ ነጻነትን በማዋረድ ጸረ – ሐይማኖታዊ ተግባሩን እንደሙስሊሙ ማህበረሰባችን እና እንደተቀረው የህዝብ ተቋማት ሁሉ የደም እጁን በማስገባት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም ውስጥ ብሄርተኝነትን በማራመድ የተለመደ የፖለቲካ ስራውን እየሰራ ነው፡፡

በአንጻሩ ስለኢትዮጵያ አንድነትና ሰላም ቀን ከሌት የሚጸልዩትን አባቶች ደግሞ እንደጠላት በመፈረጅ ለእንግልትና ለስደት እያበቁ የእግዚያብሄርን ቤት የካድሬዎች ገዳም የፖለቲካ እድሜ ማራዘሚያ  ማድረጋቸው ለህዝበ ምእመናኑ እና ለቤተክርስቲያኗ ነጻነት ክብር እና ደንታ እንደሌላቸው የሚያሳይ  ሃላፊነት የጎደለው አምባገነናዊነት ነው።

ሰሞኑን ህጋዊው ሲኖዶስ ለህዝብ ይፋ በማድረግ ባወጣው መግለጫ፤ ሲኖዶሱ ለሀገራችን አንድነትና ሰላም ሲል የሞከረውን የእርቀ ሰላም ሂደት በማድነቅ፤  የወገናችሁ ጉዳይ አስጨንቋችሁ፣ አሳስቧችሁ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእምነት፣ በዘር፣ በጎሳና በፖለቲካ ሳይለያይ የሲቪሉም ሆነ የፖለቲካ ድርጅቶች በመተባበር በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ  እንታገለው ዝንድ ያቀረባችሁትን ጥሪ ተቀብለን በማሰተዋልና በጽናት ዘረኛውን ወያኔ እንታገለዋለን፡፡ ለዚህም ከእናንተ ጋር ሆነን ለድል እንደምንበቃ አንጠራጠርም።

ወያኔ በሃይማኖታችን፣ በኑሮአችን ጣልቃ በመግባት እምነትን ለማዳከም የሚያደርገውን አፈናና ረገጣ እሰከ መጨረሻው ታግለን በማስወገድ ዜጎች ካለምንም ጣልቃ ገብነት የእምነታቸው ነጻነት ይከበር ዘንድ አብረን ከእናንተ አባቶቻችን ጎን በመሰለፍ ትግሉን ወደፊት ለማድረግ እኛ የግንቦት 7 ንቅናቄ አባላትና አመራር ወያኔን ለማስገደድ ወይም ለማስወገድ ዛሬም ቆርጦ መነሳቱን በድጋሜ ቃል ይገባል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

 

 www.ginbot 7.org

ዳዊት ከበደ እየበራ ነው እየጠፋ!?

አቤ ቶኪቻው

ዳዊት ከበደ እየበራ ነው እየጠፋ!? የቀድሞው አለቃዬ እና የአሁን ወዳጄ ዳዊት ከበደ ሰሞኑን አወዛጋቢ ሆኖ ሰንብቷል። ለምን አወዛገበ? ምን አወዛገበ? እንዴት አወዛገበ? ማንን አወዛገበ…? ወዘተ የሚሉትን ሁሉንም ዘርዝሬ መዝለቄን እንጃ ግን እስቲ ትንሽ ነካ ነካ ላድረግማ፤

ባለፈው ጊዜ ዳዊት ከበደ ስለ ኢትዮ ሚዲያው አበርሃ የፃፈውን ወቀሳ በአውራምባ ታይምስ ድረ ገፅ ላይ አንብቤ ነበር። በኢትዮ ሚዲያ ላይ ስለ ዳዊት ከበደ የወጣውን ፅሁፍ አላየሁትም። የዳዊትን ምላሽ ግን አልወደድኩትም። ይህንን ለዳዊትም ነግሬዋለሁ። ሳስበው ዳዊት ያንን ፅሁፍ ሲፅፍ ክፉኛ ተበሳጭቶ እንደሆነ እገምታለሁ። ምን መገመት ብቻ በደንብ አውቂያለሁ እንጂ…በተናደድን ጊዜ የምንወስናቸው ውሳኔዎች ብዙ ግዜ መልከ መልካም አይሆኑም። ወይም ውጤታቸው አያምርም። በብስጭት ሲወሰን እንኳን ሌላው ቀርቶ ራስን ማጥፋት እንኳ አይሳካም። ለሁሉም ነገር ስክነት ያስፈልጋል። በስክነት ውስጥ ብስለት አለ። በጥድፊያ ውስጥ ግን ያለው ጥፊያ ነው መጥፋት እና ማጥፋት።

ይህ በሆነ በስንተኛው ቀን እንደሆነ እንጃ እንደ ገጠር ቤተክርስቲያን ሰንበት ሰንበት ብቻ የሚከፈተው አባመላ የተባለ ፓልቶክ ሩም ዳዊት ከበደን ይዞ ባለፈው ቅዳሜ ብቅ ብሎ ነበር። ወዳጄ ዳዊት ከበደ ወደዚህ ፓልቶክ ሩም ለቃለ ምልልስ ሲሄድ በፊት ከነበረው አቋሙ በአንዳች ምክንያት ለውጥ እንዳደረገ ተገንዝቤ ነበር።

ምን አይነት አቋም…!?

ከዚህ በፊት አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ እየሰራን ሳለ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለቃለ ምልልስ ቢጠራው እምቢኝ ብሎ እንደነበር አስታውሳለሁ። ዛሬ ግን የኢህአዴግ ዋነኛ አቀንቃኝ የሚባል ፓልቶክ ሩም ለቃለ ምልልስ ሲጠራው “ምን ችግር አለው” ብሎ ሄዷል። ይሄ በጣም ያስደሰተኝ ለውጥ ነው። ጥያቄዬ ለውጡ የመጣው በብስጭት ነው ወይስ በብስለት ነው? የሚለው ነው። መልሱም እኔው ዘንድ አለ። ዳዊት የአቋም ለውጥ ያመጣው በብስጭት ነው።

ዴቭ በዚህ ፓልቶክ ሩም ሁለት ነገሮችን አንስቷል። አንደኛው፤ በውጪ ሀገር ያሉ የተቃዋሚው ፓርቲ አመራሮች የመፃፍ ነፃነቴን ተጋፉት የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ትግሬ ስለሆንኩ በውጪ ሀገር ባሉት ተቃዋሚዎች ዘንድ በጥርጣሬ አይን እየታየሁ ነው። የሚል ነው።

ሁለቱም ነገሮች ቢሆን ተደርገው ከሆነ በእውነቱ በተቃዋሚዎቻችን እጅጉን ተስፋ ቆርጠን ፍራሽ አውርደን ልቅሶ መቀመጥ አለብን። በተለይም እዚህ ውጪ ሀገርም የፕሬስ አፈና የሚደረግብን ከሆነ በተለይ ከኢትዮጵያ ሸሽተን የመጣን ሰዎች ድጋሚ ሸሽተን ወደ ኢትዮጵያ መሄድ ሊኖርብን ነው ማለት ነው።

ለማንኛውም ዳዊት በዚህ የተነሳ ብስጭቱን ገልጿል። እኛም “ጎበዝ ዳዊት” ብለን አሞካሽተን ችግሩ ግን ብለን እንቀጥላለን…

ችግሩ ግን ዳዊት በቃለ ምልልሱ ወቅት አባ መላ የተባለው ጠያቂው በቀደደለት ቦይ ዝም ብሎ ሲፈስለት መመልከቴ ነው። ይሄኔ ነው ዳዊት እየጠፋ ይሆንን!? ስል ሰጋት የገባኝ።

ነገር ቢያበዙት በአህያ አይጫንም እንዲሉ አንድ ለምሳሌ ላንሳ፤

ጠያቂው አባ መላ “እስክንድር ነጋ በአሸባሪነት ከተሰየሙ ድርጅቶች ጋር ሲፃፃፍ ተይዞ ለምን ታሰረ? የሚሉ ሰዎች ዛሬ ግኡሽ አበራ በፌስ ቡክ ላይ ስሜቱን በመግለፁ ሲቃወሙ አግባብ ነው ትላለህ?” ብሎ ሲጠይቀው የዳዊትም መልስ ለመስማት ጆሮዬን አቆምኩ ወዳጄ ዳዊትም “ልክ ነህ!” ብሎ ገና ሲጀምር ታመምኩኝ።

እንደኔ እምነት እና እንደ አቃቤ ህግ ማስረጃ እስክንድር ነጋ ከአሸባሪ ቡድን ጋር ኢሜል መለዋወጡን የሚያስረዳ ነገር አላየንም። እንደኔ እምነት እስክንድር ነጋ የታሰረው ሀቅን ስለፃፈ ብቻ ነው። እንደኔ እምነት ዳዊት ከበደም የተሰደደው ሀቅን ስለፃፈ ብቻ ነው። እናም ወዳጃችን ዳዊት ጠያቂው አባ መላ በመላ ወደ ስርጡ ሲወስደው ሰተት ብሎ ሲሄድለት አየሁ። ይሄኔም ሰጋሁ ዳዊት እየጠፋ ይሆን!?

በጥቅሉ ዳዊት ከፍቶታል። ጥሩ ነው መከፋት። “ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህዴግ ሰራዊት!” እንዲሉ ብሶት የለውጥ መነሻ ነው። ግን ምን አይነት ለውጥ!?

ዳዊት የትግራይ ተወላጅ ስለሆንኩ ተቃዋሚ ስለመሆኔ በጥርጣሬ ታየሁ እንደውም ተቃዋሚ አይደለሁም የማንም ሳይሆኑ መኖር ይቻላል ብሎናል።

ድሮውንም በግሌ ዳዊት ከበደ ተቃዋሚ ነው ብዬ አላምንም። ልክ እኔ ተቃዋሚ እንዳልሆንኩት ማለት ነው። መንግስትን መተቸት ተቃዋሚ መሆን አይደለም። ለገባው መንግስት እንደውም ትችት ደጋፍ ነበር። የእኛ መንግስት የገባው ሳይሆን ግራ የገባው በመሆኑ፤ ደጋፊ አልፈልግም ብሎ አባረረን እንጂ…!

በመጨረሻም፤

እንደኔ እምነት የትግራይ ተወላጆች ተቃዋሚውን ዳዊት በሚያይበት መነፅር እያዩ ከሆነ በእውነቱ ሀገራችን ትልቅ ኪሳራ ላይ ናት።

አሁንም እንደኔ እምነት ተቃዋሚዎች የትግራይ ተወላጆችን፤ ዳዊትን በሚያዩበት መነፅር እያዩ ከሆነ ትልቅ እብደት ውስጥ ነን!

ecadf.com

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ክፍያ ሳይፈጽም ጫወታ ማሰራጨቱ የሚዲያ ስነምግባርን የጣሰ ውንብድና ነው ተባለ

ጥር ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለ ኤል ሲ ቱ የተባለ የቴሌቪዥን ጣቢያ ክፍያ ሳይፈጽም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከዛንቢያ ቡድን ጋር ያደረገውን ጫወታ ማሰራጨቱ የሚዲያ ስነምግባርን የጣሰ ውንብድና ነው ተባለ::

ምንጮቻችን ባደረሱን መረጃ መሰረት የአፍሪካ ዋንጫ የቴሌቪዥን ስርጭት ባለመብት ለሆነው ለ ኤል ሲ 2 ክፍያ ሳይፈጽም ስርጭቱን ማስተላለፉ ተመልክቶል::

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተፈጸመውና ውንብድና የተሰኘው ለስርጭቱ ባለመብት የ 18 ሚሊዮን ብር ሳይከፍል ጠልፎ በህገወጥ መንገድ ባስተላለፈው ጨዋታ ባለመብት የሆነው ድርጅት በህግ ይጠይቀው አይጠይቀው የተባለ ነገር የለም::

የሆነ ሆኖ የኢትዮጵያና የዛምቢያ ጨዋታ ሲደረግ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ክፍያ ሳይፈጽም ጫወታውን በውንብድና በመውሰድ እያስተላለፈ መሆኑን ከደቡብ አፍርካ የስፓርት ተንታኞቹ እየተቹበት እንደነበር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል::

ምንጮች እንዳመለከቱት የኢትዮጵያና የዛምቢያ ጨዋታ እየተካሄደ እያለ ያለክፍያ በመጥለፍ ኢቲቪ ሲያስተላልፍ የነበረው ስርጭት ሲቆረጥ በዲኤስ ቲ ቪ ጨዋታውን የሚከታተሉ ያለችግር ማየታቸውን ለመረዳት ተችሎል::

አሁን ዘግይቶ በደረሰንመረጃ መሰረት የተቀሩትን ጨዋታዎች ከባለመብቱ ድርጅት ተከራይቶ ለማሳየት የ ኢቲቪ ሰዎች እየተደራደሩ መሆኑ ተመልክቶል:

Esat news

ፓሊሶች በአራት ኪሎ የሚገኙ ቤቶችን በእሳት አቃጠሉ

ጥር ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ለረጅም አመታት በአራት ኪሎ አካባቢ የኖሩ  ሰዎች ቦታው ለሼራተን ሆቴል ማስፋፊያ ይፈለጋል በሚል ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ሲነገራቸው እንደቆየ የተናገሩት አይን እማኞች፣ ነዋሪዎቹ በበኩላቸው መንግስት ተተኪ ቤት እስካልሰጣቸው ድረስ አካባቢውን ለቀው እንደማይሄዱ ሲከራከሩ ቆይተዋል። ዛሬ ጧት ወደ አካባቢው ያቀኑት ፖሊሶች ነዋሪዎቹ እቃዎቻቸውን ሳያወጡ በቤታቸው ላይ እሳት በመልቀቅ ቤታቸውን አቃጥለውባቸዋል። ነዋሪዎቹ በጩሀት ወደ ፓርላማ በመሄድ አቤት ቢሉም ሶስት ሰዎችን በመወከል ችግራቸውን እንዲያቀረቡ ተነግሮአቸዋል። ፖሊሶች ወደ አካባቢው በመድረስ ተቃውሞ ሲያሰሙ የነበሩ ነዋሪዎችን አባረዋቸዋል።

አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የአይን ምስክር ለኢሳት እንደገለጡት፣ ተማሪዎች ደብተራቸውን እንኳን ሳያወጡ ቤታቸው እንደተቃጠለባቸው፣ ብዙዎችም በከፋ ችግር ላይ መውደቃቸውን ገልጸዋል።

በኢትጵያ ውስጥ በልማት ስም እየተበራከተ የመጣውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አለማቀፍ ሰብአዊ መብት ተማጓች ድርጅቶች ችላ እንዳሉት ተመልክቷል። በአላማጣ ላለፉት አንድ ወራት የከተማው ህዝብ በልዩ ፖሊሶች ሲዋከብ እንደነበርመዘገባችን ይታወሳል። በአዲስ አበባ ላፍቶ ክፍለከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው በርካታ ነዋሪዎች አሁንም በከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

 

 Esat news

“አንድ ጥምቀት፣ አንድ ሃይማኖት” የሚል ጥቅስ የያዙ ወጣቶች ታሠሩ

(ደጀ ሰላም፤ ጥር 12/2005 ዓ.ም፤ ጃኑዋሪ 20/2013/ PDF)፦ ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በላከው መልእክቱ ምዕራፍ 4 ቁጥር 5 ላይ ያለውን “አንድ ጌታ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንድ ጥምቀት” የሚል ጥቅስ ያለበት ቆብ ለሰንበት ት/ቤታቸው ገቢ ማስገኛነት በመሸጥ ላይ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ መታሠራቸው ታወቀ።
ጥር 11/2005 ዓ.ም ታቦተ ሕጉን ተከትለው በሞቀና በደመቀ ሃይማኖታዊ መንፈስ በማክበር ላይ እያሉ በፖሊስ የታሠሩት ስድስት ወጣቶች ሲሆኑ ጥቅሱ የተጻፈበትን ቆብ ይሸጡ የነበሩት ደግሞ ለብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት ገቢ ለማስገኘት በሚል እንደሆነ ተገልጿል። መንግሥት የሃይማኖት አክራሪነትን እዋጋለኹ በሚለው ዕውቀት የጎደለው ተግባር ‘አንድ ሃይማኖት’ የሚል ቃል የሚናገሩ ክርስቲያኖችን በሙሉ በማሳደድ ላይ ይገኛል። የመጽሐፍ ቅዱስ ኃይለ ቃል እና የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረተ እምነት የሆነውን ቃለ እግዚአብሔርን መናገር፣ ማስተማርም ሆነ በጽሑፍ መያዝ ሌሎች እምነቶችን እንደመዋጋት ተደርጎ እንዲቆጠር በመናገር በፖሊስ ጥብቅ ማዋከብና እንግልት የሚፈጽመው መንግሥት እነዚህን ስድስት ልጆች የያዘው በዚሁ ምክንያት መሆኑን በወቅቱ በቦታው የነበሩ እማኞች ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ቀደምት መንግሥታት ሁሉ በባሰና በከፋ መንገድ በቤተ ክርስቲያኒቱ የውስጥ ጉዳይ ረዥም እጁን አስገብቶ የሚያምሰው የፖለቲካው መዘውር በቅርቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤያት ላይ ሳይቀር ባለ ሥልጣኖቹን በመላክ የሲኖዶሱ ተሰብሳቢ ለመሆን በመሞከር ላይ መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን ይታወሳል።
መንግሥት በአገሪቱ ቀደምት እምነቶች ላይ ያለውን አቋም ለካድሬዎቹ በተከታታይ ሥልጠኛ በመስጠት የሚያስጠናበት ሰፊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል። ለዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ድረስ በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና በሌሎች ኃላፊዎች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና እስልምና ላይ ያነጣጠረ ሲሆን በባለሥልጣናት ቁጥር ሰፊ ተሰሚነት ያገኙትን ፖሮቴስታንቶችን ግን ምንም አይነካም። መንግሥት በነባር አገራዊ ቤተ እምነቶች ላይ እያስፋፋ የመጣው ጣልቃ ገብነት ድንበሩን አልፎ የእስልምና መሪዎችን በማሰር፣ የቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶስ በመዘወር መገለጡ ይታወቃል።
መንግሥት ለባለሥልጣኖቹ የሚሰጠውን ሥልጠና ለማወቅ ለምትፈልጉ ወደፊት እንዳስፈላጊነቱ ሙሉ ዶኩመንቱን ለማቅረብ እንሞክራለን።
ቸር ወሬ ያሰማን
dejeselam.org

Endemic Corruption Ending the EPRDF rule?

Emulating the Pakistani uprising against corruption 

This piece is prompted by the recent development of crisis in Pakistan where “Pakistan‘s Supreme Court has ordered the arrest of the country’s prime minister on corruption charges, heightening the already extreme political uncertainty and fears the country’s fragile democracy could be derailed.”

Pakistan is a conservative Islamic state where one would have expected least corruption but, lo and behold, endemic greed is surprisingly becoming the foremost issue threatening to plunge the fragile country already beset with severe politico-economic problems into a more catastrophic situation.

Pakistan’s Prime Minister, Raja Pervaiz Ashraf, has been arrested in connection with a scandal involving contracts for power stations. The news broke on television stations as a “Muslim cleric, Islamic scholar Tahir-ul-Qadri, addressed tens of thousands of protesters who have massed on the capital city for an extended sit-in to protest against corruption and electoral malpractice by Pakistan’s politicians.”

Qadri declared to his supporters that the “false mandate of the rulers is over” and ordered President Asif Ali Zardar to dissolve parliament immediately. He told the crowd that the power of the President is over adding: “There are only two institutions in Pakistan that are functioning and doing their duties of the people. One is the judiciary of Pakistan and one is the armed forces of Pakistan and nothing else.” Qadri declared: “Victory, victory, victory by the grace of God!” Source: Google

Rampant corruption is increasing at an alarming rate in Ethiopia as admitted by the inactive EPRDF government waiting for its own downfall by popular uprising because the courts in the country are mere stooges of the ruling party. The determined public display of Pakistanis against corruption is one that impoverished Ethiopians should emulate knowing that the kind of support the judiciary and the military enjoyed by the former may not be available to the latter although it is worth soliciting through persuasion.  Nevertheless, the Ethiopian people have the all the justification to stage a series of debilitating and massive protests publicly to hold their incompetent and greedy leaders to account for, among other things, have failed miserably to bring corruption under control. Only an all-inclusive uprising comprising all stakeholders can effectively deal with the draconian and multiple problems created by the EPRDF over the last 21 years.

Lesson for Ethiopian opposition in fighting the corrupt EPRDF regime

Pervasive corruption is increasingly engulfing our global village threatening to topple governments in some countries. It is triggering popular wrath and fury at the scourge wrought by greed ushering in widening gap between the rich and the poor even in countries that had chosen scientific socialism as a model of growth for many years. Some interesting examples are provided below:-

1.          China: In my article titled “Reform in China vs. crisis within EPRDF” dated 15 November 2012 I wrote: “The GS in his speech to leading officials underlined the unprecedented stride in economic growth achieved in the last decade but asking them “to exercise strict self-discipline and strengthen supervision over their families and staff.” He said “Leading officials at all levels, especially high-ranking officials, must readily observe the code of conduct on clean governance and report all important matters” adding that “If we fail to handle this issue well, it could prove fatal to the Party, and even cause the collapse of the Party and the fall of the state”. He made a passionate plea that “the CPC must make unremitting efforts to combat corruption, promote integrity and stay vigilant against degeneration.” He singled out corruption as a major problem in his closing speech also. And the incoming General Secretary (GS) Xi Japing strongly underscored the same thing in condemning the rampant corruption.” Emphasis added

The CPC and its government made a phenomenal progress in amassing wealth in the last decade but with poor distribution of that wealth going to members of the CPC top echelons not to mention flagrant abuse to human rights over the period.

One has to watch the CCTV the progress China is making in fighting corruption, openness to the outside world and transparency at home.

The lesson from China’s experience for Ethiopians is logically to take into account equitable wealth distribution, respect for human rights, social justice, and economic development together – respect for human rights taking precedence at all times.

2.            Uganda: President Museveni has realized the danger that rampant corruption is posing to the stability of his government. So he is leading a concerted effort to fight the pervasive corruption in Uganda under the slogan: “Zero tolerance for corruption”. He is in part driven by the pressure of donors withholding funding for development projects and direct budgetary support plus the public cry demanding accountability for corruption. The opposition FDC led by its newly elected Party President is also promising to play a constructive role leaving behind the blame game of the past eight years. The recently formed group, which has christened itself: “Black Monday Activists” is also seen on the streets envy Monday wearing black dresses and sensitizing passers-by on the severity of corruption in the country and distributing brochures to that effect. The free print and broadcast media in Uganda and the East Africa region report profusely on the pervasive corrupt practices.

The Uganda example is something opposition activists and civil entities back home in Ethiopia may consider to intensify civil disobedience against the inactive government. I hope that the broadcast from the CCTV station to Africa will not be used in fostering the “vision of the dead man” Meles Zenawi, the former friend of Communist Party of China (CPC) China should act in its long term interest to side with the vast majority of the Ethiopian people by rethinking its policy of underpinning a minority TPLF party trading in the good names of the valiant people of Tigray.

3.            Ethiopia: The late Zenawi openly and in full view of the public complained about pervasive corruption in his government and the business sector. The mother of corruption Azeb Mesfin, the former TPLF ideologue and Chief Executive Officer ofEndowment FundforRehabilitation of Tigray (EFFORT) Sebhat Nega (the enemy of Amhara and the Ethiopian Orthodox Tewahedo Christian Church) and others in the den of thieves should face justice soonest by popular demand. No audit report of this mammoth business monopoly has been made public. Azeb Mesfin, the widow of Meles Zenawi, replaced Nega as CEO while her husband was alive.

The do-as-told Prime Minister Hailemariam is the flag bearer of the nauseating legacy of his predecessor.  He is not expected to address the colossal corruption problem for he has already proved himself timid, habitual liar and incompetent leader. He cannot be relied on to follow the example of President Museveni in leading the fight against corruption.

President Obama’s Inauguration Address (21/01/2013)

President Obama alluded to the Declaration of the United States of America on July 4, 1776 in which the immortal words “We hold these truths to be self-evident, that all men are created equal. That they are endowed by their creator with certain unalienable rights, and among these are life, liberty and the pursuit of happiness” are enshrined.

The part of his address that attracted my attention most is captured in the words: “Today we continue a never ending journey to bridge the meaning of those words with the realities of our time. For history tells us that while these truths may be self-evident, they’ve never been self-executing. That while freedom is a gift from God, it must be secured by his people here on earth.”

Yes, indeed! As the old adage goes God helps only those who help themselves. We Ethiopians must rise up in unison to secure our rights, which are not “self-executing” unless we actively move to claim them.  This we must do by ourselves at any cost; it would however be a bonus if the President would keep his pledge this time around to support our quest for democracy and be on the side of the overwhelming majority of the Ethiopian in the best long-term interest of the United States of America. Extremists and terrorist are better fought and defeated by siding with the majority seeking peace, stability, democracy, prosperity and harmony in earnest.

Conclusion

The TPLF is a terrorist organization identified as such by Genocide Watch, the Global coalition to end genocide and mass atrocities. Genocide Watch has been vindicated by the recent plot of assassination on the renowned journalist and human rights Abebe Gelaw in the United States. We Ethiopians everywhere should relentlessly plead with the Obama Administration to rethink its policy of working with a terrorist organization perceived as such by the international community and verified by the heinous plot of assassination intended to be carried out on the homeland of the US citizens.

Pervasive corruption in Ethiopia is certainly one of the top crimes of the EPRDF leading to the collapse of the regime. Opposition forces and civic organization at home and in the diaspora should seize corruption as a weapon to expedite the downfall of the EPRDF repressive government.

President Yoweri Museveni of Uganda has realized the grave danger that rampant corruption is posing to his government and has taken the lead in fighting the scourge. The same cannot be expected of Desalegn Hailemariam, the puppet Prime Minister of the EPRDF regime. So the best choice for us Ethiopians is emulating the Pakistani uprising against pandemic corruptionin Ethiopia of which the massively unemployed young persons are the main victims.

In closing I would like to renew my solidarity with the 33 opposition parties in Ethiopia vying to initiate popular protest to assert their right to participate in the forthcoming local elections.

My mantra: “The Almighty God has done His part leaving to us what we in the opposition and the Ethiopian people can do together. It is critical to act in unison to save Ethiopia. It is high time to boost the morale of renowned main opposition political entities and civic movements at home!

Release all political prisoners including Andualem Aragie, Eskinder Nega, Bekele Gerba, Reeyot Alemu, Leaders of the Ethiopian Muslims et al!

LONG LIVE ETHIOPIA!!!

rababya@gmail.com

 

አባ ሕዝቅኤል ለምን ስብሰባ ረግጠው ወጡ?

“የማንም አሿሿሚ አልሆንም የሥልጣን ጥመኞችን አላገለግልም”በማለት አራት ወራት የቀረውን የሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነታቸውን የሚለቁ መሆናቸውን በደብዳቤ ገለጡ እየተባለ ሰሞኑንethiopian orthodox church in Addis Ababa የሚወራላቸው አባ ሕዝቅኤል  ቀደም ሲልም ስብሰባ ረግጠው ቢወጡ የፈረሰው ቀኖና ይመለስ ብለው እንዳልሆነ መታወቅ አለበት

አባ ሕዝቅኤልና በአዲስ አበባ የሚገኙት የሲኖዶስ አባለት ለእርቅና ለሰላም እንዲሁም ለሀያ ዓመታት የዘለቀውን የቤተ ክርስቲያን መለያየት ወደ አንድነት ለማምጣት በቅንነት እና ግልጽ በሆነ መንገድ ቢጓዙ ኖሮ ለዚህ ለከፋ መከፋፈል እንዲሁም ለመንግሥት ጣልቃ ገብነት ባልተዳረጉ ነበር ይልቁንም አባ ሕዝቅኤል  የመንግሥት ጣልቃ ገብነት አለ መባሉ ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነና ቅዱስ ሲኖዶስ ለምርጫ የሚያስፈልጉ ደንቦችን ከማውጣት በቀር መንግሥት ጣልቃ አልገባም በማለት በአደባባይ ተናግረው ጸሐይ የሞቀውን እውነት የካዱ አባት ናቸው አቡነ ገብርኤልም ይሕንኑ ሀቅ ክደው በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ በሰጡት ቃል የአባ ሕዝቅኤልን ውሸት ደግመውታል

ይልቁንም አባሕዝቅኤል በአፋቸው ስለ እርቅና ሰላም እያወሩ እሳቸውና መሰሎቻቸው  ከእኛም ወገን ይድረሰን ከሚሉት ግብረ አበሮቻቸው የሚፈልጉትን ፓትርያርክ ለማስመረጥ የሚሄዱበት መስመር እየተዘጋ በመንግሥት የሚደገፉት የነ አባ ሣሙኤል ክንድ እየበረታ ሲሄድ  ማንንም አሿሿሚ አይደለሁም፤ የሥልጣን ጥመኞችን አላገለግልም ማለቱ እና  አራት ወር የቀረውን የጸሀፊነት ሥልጣን እለቃለሁ ማለቱ ምክንያታዊነቱ  ፈጽሞ አይታይም

በሐቅና በእውነት የአባ ሕዝቅኤል አቋም ሲታይ ፣

ethiopian orthodox church Addis Ababa, ethiopia

ከወያኔ ጋር አብረው አ/አበባ የገቡት አባ ተከስተ የአሁኑአባ ሳሙኤል

1ኛ/የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከሁለትና ከዚያም በላይ ተከፋፍላ የምትገኘው ፓትርያርክ መርቆሬዎስ ያለ አግባብ በፖለቲካ ውሣኔ መንበራቸውን እንዲለቁ መደረጉን አምነው አይቀበሉም፣

2ኛ/ሕገ ቤተ ክርስቲያን ተጥሶ ፓትርያርክ በሕይወት እያለ አባ ጳውሎስ መሾማቸው ቀኖና መሻሩን አምነው ለመናገር አይደፍሩም ታዲያ የአባ ሕዝቅኤል አቋም እና እውነት የት ላይ ነው ?

ሁሉም ማወቅ ካለበት እርቅ እንዲመጣ የቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት እንዲመለስ ከተፈለገ ከእርቁ በፊት የምርጫ ሕግ ማውጣት ለምን አስፈለገ ? እርቁ መቅደም አልነበረበትም ? አውነት እንነጋገር ከተባለ የሰላሙን በር አስቀድመው የዘጉት አባ ሕዝቅኤል  አይደሉምን ?ከመንፈስ ቅዱስ ሀሳብ ይልቅ የቁጥር ስሌት ገብተው አምስት ስንል ኖረን አራት አንልም ብለው መግለጫ ከመስጠት አልፈው ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስን በፓትርያርክነት ለመቀበል አንችልም ይልቁንም  ታሪክ ይፋለሳል አምስተኛ ፓትርያርክ እያልን ኖረን ከ20 ዓመት በኋላ ወደ ኋላ መመለስ አይቻልም፡፡ ይህ አስቸጋሪ ስለሆነ ቀኖናውንም ታሪኩንም የሚጥስ ስለሆነ ነው እንጂ አቡነ መርቆርዮስ ወደ ቦታቸው እንዳይመጡ የጠላ ማንም የለም፡፡ ሁሉም ሰላሙን ፈልጓል፡፡ አቡነ መርቆርዮስ ወደ ሃገር መጥተው በፈለጉበት ቦታ መቀመጥ ይችላሉ፡፡ ሰላሙ ተመስርቶ በውጭ የሚገኙ አባቶቻችን አዚህ መጥተው የመምረጥም የመመረጥም ዕድል ይኖራቸዋል፡፡በፈለጉበት ቦታ እንደማንኛውም ሰው ገብተው መቀመጥ ይችላሉ በማለት በአንድ መጽሔት በሰጡት ቃለ ምልልስ ደግመው አረጋግጠዋል

አባ ሕዝቅኤል እውነት ለመናገር የማይደፍሩ በተለያዩ ሚዲያዎች እንኳን ለሚቀርብላቸው ጥያቄ አስተያየታቸውን  ለመናገር ቀጠሮ የሚያበዙ ነገሮችን በማድበስበስ ግልጽ አማርኛ ለመናገር ቋንቋ የሚያጥራቸው ግለሰብ ናቸው ታዲያ በምን መመዘኛ ነው አባ ሕዝቅኤልን ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ቆሙ የምንለው

ዘመነ ካሣ

ከጀርመን

ecadf.com

ምስጢራዊው የበረሃው ሲኖዶስና የማህበረ ቅዱሳን ፓትርያርክ፣ ከአብየ አዲ እስከ አዲስ አበባ

ቤተ ማህቶት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን በተመለከት ÷ ለሰሚ የሚገርሙ ዜናዎች መሰማት ከተጀመረ ከርሟል :: ግን ቤተ ክርስትያኗ እንዲህ ትሆን ዘንድ ከበረሃ ጀምሮ የተጠነሰሰና የታቀደ ረቂቅ እቅድ መኖሩናን ÷ አሁንም እየተተገበረ ያለው ያ መሆኑን በርካታ ዜጎች ያወቁ አይመስልም:: ህወሀት በረሃ እያለ በ1980ዎቹ ውስጥ ፓትርያርክ እንዳዘጋጀ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? ። ቤተ ክርስትያኗን እሰክወዲያኛው ለመቆጣጠር የህወሀት ካድሬዎች ጳጳሳት ሆነው የቤተ ክርስትያኒቱ ከፍተኛ መዋቅር ላይ እንዲቀመጡ ተደርጓል:: ሌላም ሌላም:: የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን በኢህአዴቅ ቅኝ ግዛት ውስጥ እንዴት እንደወደቀች በማስረጃ እንመልከት:: ነገርን ከስሩ ውሃን ከጥሩ ነውና ከመጀመርያው እንጀምር:: የመጀመርያው መጀመርያ::

መቻ ኦርቶዶክስ – ህወሀትና ለቤተ ክርስትያኗ የደገሰው የሞት ድግስ

የትግራይን ብሄርተኝነት (Tigray Ethnicism) አንግቦ የተነሳው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ÷ ይከተል የነበረው ርእዮተ ዓለም

( Marxism) ማርክሲዝም ሌኒንዝም ነበር:: ሲጀመር ማርክሲዝም ጸረ ሃይማኖትና ሃይማኖትን ማዋረድና ማራከስ ዓላማው የሆነ ፖለቲካዊ እሳቤ ነው:: ከዚያ ፍልስፍና በመነሳት ይሄ ድርጅት ታሪካዊቷን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንን  “ፊውዳልና መመታት ያለባት” አድርጎ ፈረጀ:: ሲቀጥል ደግሞ ህወሀት ብሄርተኛነት ( Ethnicity) ላይ እንጂ ብሄራዊነት ወይም አሀዳዊነት

( Unitary) ወይም አንድነት ላይ ንቀት የነበረው ደርጅት ስለነበረ÷ ያገሪቱ አንድነትን የሚያንጸባርቁ ድርጅቶችን በሙሉ እንደጠላት የማየት አባዜ የነበረበትና አሁንም ያለበት ድርጅት ነው:: ቤተክርስትያን ደግሞ ሕብረ ብሔራዊት መሆኗ ህወሀት ጥርስ ውስጥ ለመግባት በቂ ምክንያት ነበር:: ይህንንም የሕወሀት መስራችና የቀድሞ መሪ የነበሩት ዶክተር አረጋዊ በርሄ A Political History of the Tigray People’s Liberation Front (1975-1991): Revolt, Ideology and Mobilization in Ethiopia

በሚለው ለዶክትሬት ማሟያ በጻፉ ድርሳናቸው ውስጥ እንዲህ ሲሉ በማያወላዳ ቋንቋ ገልጸውታል

The pragmatic TPLF understood the church’s role in village social life and its support for the unity of the country. It also understood a possible alliance between the Church with forces that stood against socialism and nationalization of the land as well as against separatism. The church was viewed as a force standing in the way of the TPLF but one that should be handled with caution. .. There was no doubt that that it wanted to subordinate the church to its cause.[i]

ይህንንም ዓላማ ዳር ለማድረስ የተመቀበት መሰሪ ዘዴ

1ኛ የቤተ ክርስትያን ሰው መስሎ አብያተ ክርስትያናቱ ውስጥ መሰግሰግ÷

2ኛ በትልልቅ ገዳማት÷ መነኮሳትንና ካህናትን በማሳሳት ለሕወሀት ጸረ ቤተ ክርስትያን ዓላማ ተገዢ ማድረግና

3ኛ ለዘለቄታው ቤተ ክርስትያኗን ለማሽመድመድና በቁጥጥሩ ስር ለማስገባት የራሱን ካድሬዎች ሲኖዶስና ከፍተኛ አመራር ውስጥ በማስገባት ሙሉ በሙሉ ቤተ ክርስትያኗን  መቆጣጠር ነው:: እያንዳንዱን በደጋፊ መረጃ እንመልከት

የሀወሀት ካድሬዎች  ገዳም መግባት

የህወሀትን ታሪክ ከጻፉት ጥቂት ሰዎች መካከል ለአሜሪካ የመረጃ ድርጅት ቅርበት እንዳላቸው የሚታመነው John Young, Peasant Revolution in Ethiopia: The Tigray people Liberation Front ( 1975- 1991) በሚለው መጽሀፋቸው ገጽ 176 ላይ የሕወሀት ካድሬዎች ላሰቡት ስውር ዓላማቸው እንዲረዳቸው የቤተ ክርስትያንኗን ትምህርት ማጥናት እንደጀመሩ እንዲህ ሲሉ ይገልጹታል

“TPLF cadres spent considerable time studying the Bible and the teaching of the church so as to equip themselves for the task[ii]

እነዚሁ በዓላማ የቤተክርስትያኗን ትምህርት እንዲያጠኑና መነኩሴ እንዲመስሉ የሰለጠኑት የህወሀት ካድሬዋች በአቶ ስብሀት ነጋ በሚመራ የስለላ መዋቅር በየገዳማቱ እንዲበተኑ እንደተደረገና ÷እነዚህም ሰላይ የድርጅት አባላት የየገዳማቱን ቁልፍ ቦታ እንዲይዙና መንፈሰ ልል መነኮሳትን እንዲመለምሉ መደረጉን ሁኔታውን ባይናቸው ያዩትና ÷ በወቅቱ ይድርጅቱ ሰብሳቢ የነበሩት ያሁኑ ዶክተር አረጋዊ በርሄ እንዲህ ሲሉ ነበር ያስቀመጡት

This process involved the mobilization of parish priests and ordinary Christians to isolate them from the church’s national hierarchy. To weaken church authority, an intelligence group was formed under Sibhat Nega to infiltrate the well-established monasteries in Tigrai, such as Debre Damo, by planting TPLF members camouflaged as monks and influencing church activities in the interests of the TPLF. [iii]

የጭቁን ካህናትና ሰላይ መነኮሳት መፈጠር

የቤተ ክርስትያንን ትምህርት አጥንተው ÷ የቤተ ክርስትያን ሰው መስለው ወደየገዳማቱ በመሄድ ስልጣን የተቆናጠጡት መልክተኞች ቀስ በቀስ የአብያተ ክርስትያናቱንና የገዳማቱን ማህበረሰ ማሽከርከር ጀመሩ:: የተቃወሟቸውን አባቶች በማስገደልና በማሳፈን ሌሎቹንም በተለያየ ሁኔታ በማምታታት ባጭር ግዜያት ውስጥ በርካታ ገዳማትና ትልልቅ አብያተ ክርስትያናት የህወሀት መጋለቢያ ምቹ  ሜዳዎች ሆኑ:: ጥቂቶችን ካህናትን የሃይማኖቱ ህግ ከሚፈቅደው ውጭ ጠመንጃ በማስታጠቅ ታጋይ ቀሳውስት ሲያደርጓቸው ሌሎቹን ደግሞ የስለላ መዋቅር ውስጥ በመሰግሰግ በተሳካ ሁኔታ  ተዋጊ ካህናትና ሰላይ መኮነሳትን ለመፍጠር ቻሉ::ይህንኑ ጉዳይ አጥብቆ የተመራመረው አሜሪካዊው ምሁርና የፖለቲካ ተንታኝ ፒተር ያንግ ይሄን የካድሬ ካህናት ጉዳይ በሰፊው እንዲ ሲል ከመጀመርያው አሳስቦ ነበር

Some priests rejected the church’s prohibition against taking up arms and became TPLF fighters, but most were too old to keep up with the youthful fighters and were more likely to join local militias or serve as teachers in front established schools. … Some priests  played an important role in introducing fighters to other priests and local people in recently liberated  territories. Such priests told people that unlike the atheistic Derg, the TPLF was made up of true Christians

Other priests assumed a similar role outside Tigray. Two such priests… reported that they served in the TPLF for seventeen years as political cadres , not carrying guns, but “agitating people” throughout newly liberated territories in Tigray and beyond to Gondar and Wello, as the Front took the struggle south in the final stages of the war. Since Amharigna and geez were the languages of the church they could be effectively employed throughout northern Ethiopia by the priests. Following the TPLF, these ambassadors–priests held meetings where fighters would be introduced to the priests of newly liberated territories as their “children” and always the contrast was made between the TPLF who came as liberators and the “atheist Derg”. Older and respected priests would then be recruited from each area to carry the word forth.[iv]

የበረሃው ቤተ ክህነትና የጫካው ሲኖዶስ ምስረታ

ቀስ በቀስ እነዚህ ታጣቂ ቀሳውስትና “ጭቁን ነን” ባይ መንኮሳቶች የስራ አድማሳቸው እየሰፋ መጣ:: ቁጥራቸው እየደገና እየተበራከተ መምጣቱን የተረዱት እነዚሁ አካላት ባካባቢያቸው ያሉትን አድባራትና ገዳማት ከመቆጣጠር አልፈው የቤተ ክርስትያን ቀኖናን መደንገግ ጀመሩ:: ክጥቂት ግዜያትም በኋላ የጫካውን ቤተ ክህነትና ሲኖዶስ ለመመስረት ቻሉ::

These conferences held near Abi Adi in 1983 and Roba kazi in 1984 did much to consolidate TPLF support from priesthood . Some 747 priests attended the first conference  and 550 priests attended the second , at which delegates agreed to … . Significantly in the liberated territories , thus giving rise to a “TPLF secretariat” and a “ Derg Secretariat” which continued to function out of Mekele when Mekele was captured by the TPLF in 1989 the” Derg supported” Tigrayan secretariat was  transferred to Wello., and the TPLF – supported secretariat assumed responsibility for the administration of the whole Tigray.[v]

ይሄም የበረሃ ቤተ ክህነትና ሲኖዶስ ሀወሀት መቀሌን ሲቆጣጠር መንበሩን መቀሌ ላይ በማደርግ ” ነጻ የወጡ” አካባቢዎች ቤተ ክህነት መምራት ጀመረ:: ያዲስ አበባው የመቀሌ ሀገረ ስብከት ደግሞ ወደ ደሴ በመሸሽ መንበሩን ደሴ ላይ ተክሎ ግልጋሎቱን ቀጠለ:: ደሴ በህወሀት ሲያዝ ደግሞ ደሴ ቢሮ ከፍቶ የነበረው የትግራይ ሀገረ ስብከት ወደ አዲስ አበባ ሲሸሽ የጫካው ቤተ ክሀነት ደግሞ ደሴ ላይ ስሩን ተከለ:: ሀወሀት እየገፋም መጥቶ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ይሄው የጫካው ቤተ ክህነት አብሮ አዲስ አበባ ገባ:: የጫካው ቤተ ክህነት ግን የራሱን ፓትርያርክ መርጦ ጨርሶ ነበርና ቀጣይ ስራው ከተሾሙ ሶስት አመት ያልሞላቸውን ፓትርያርክ መርቆርዮስንና መሰል አባቶችን ቦታ ማስለቀቅ ነበር::

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጸሀፊ የነበሩት ሌንጮ ለታም ሕወሀት ገና ጫካ እያለ ሲኖዶስና ቤተ ክህነት መመስረቱን አልፎ ተርፎም ደግሞ ጳጳስ አዘጋጅቶ እንደነበረ The Ethiopian State at the crossroads  በሚለው መጽሀፋቸው ላይ ለዓለሙ ማህበረሰብ እንዲህ በማለት ገልጸው ነበር

Despite the fact that TPLF was an avowed Marxist –Leninist organization, it was engaged in conducting conferences in Tigrean clergy in the latter part of 1980s. One possible aim was to explore the selection of a new Patriarch or Abuna… What is of importance of the issue that we are dealing with is that an attempt was being made to create a new kind of relationship between the emerging authority and the institution of the church. The observable result was the emergence of a new kind of priest in TPLF held areas. A “militant priest” was supposedly fashioned in the process, as distinct from the priest that still continued to stay “ in the service’ of the regime.[vi]

የአቡነ ጳውሎስ ሹመትና የቤተ ክሀነቱ ባዲስ የሰው ሃይል መተካት

መርቆርዮስ ፓትርያርክ በሆኑ በሶስት አመታቸው ” በህመም ምክንያት” በሚል ከስልጣን ወርደው አቡነ ጳውሎስ ስልጣኑን ተቆጣጠሩት:: ከሳቸውም ስልጣን መያዝ ጋር ተያይዞ በርካታ አዳዲስ ” ካህናትና መነኮሳት” የቤተ ክህነቱ ሹመኞች ሆኑ:: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ታይቶ በማይታውቅ መልኩም ÷ አቡነ ጳውሎስ አዳዲስና ወጣት ጳጳሳትን መሾም ቀጠሉ:: መረጃዎች እንደሚያሳዮት አቡነ ጳውሎስ በህይወታቸው እያሉ ከ 40 በላይ ጳጳሳትን ሾመዋል:: ይሄም በሁለት ሺህ አመት የቤተ ክርስትያን ታሪኳ ውስጥ ታይቶና ተሰማቶ የማይታወቅ ቁጥር ነበር:: በመሰረቱ የጳጳሳት በብዛት መሾም በራሱ እንደ ችግር ላይታይ ይችላል:: ነገር ግን ባቡነ ጳውሎስ የተሾሙት ጳጳሳት አብዛኞቹ ” የበረሃው ሲኖዶስ አባላትና የህወሀት ስራ አስፈጻሚ “ሲሆኑ አላማቸውም ለመንፈሳዊው ጉዳይ ሳይሆን ፓለቲካ ዘመም ነበር :: ይህም በተለያዩ ግዜያት በተካሄዱ የሲኖዶስ ስብሰባዎች ታይቷል::

አሁንም እንደሚታየው የአዲስ አበባው ሲኖዶስ ተከፋፍሏል:: ክፍፍሉም የሚታየው ነባሮቹ ጳጳሳትና አዲስ በተሾሙት ጳጳሳት መካከል ነው:: ነባሮቹ “ከፓትርያርክ ምርጫ በፊት እርቁ ይቅደም” ሲሉ አዲሶቹ ” ባስቸኳይ ሌላ ፓትርያርክ ይመረጥ ” የሚል የሃሳብ ጽንፍ ይዘው እየተሟገቱ ሰንብተዋል:: በቁጥር አብላጫውን የያዙት አዲሶቹ ያባ ጳውሎስ ጳጳሳትና የበረሃው ሲኖዶ ምልምሎች ሲኖዶሱን እየተቆጣጣሩት ብቻ ሳይሆን : በፍጹም ከቤተ ክርስትያን ተሰምቶ የማያውቅ ድምድ እያሰሙ ነው:: በስብሰባው ላይ አንዱ የበረሃ ጳጳስ ያለ ሃፍረት እንዲህ ሲሉ ነበር የተናገሩት”ፓትርያርክ መርቆርዮስ የሚመለሱ ከሆነ ትግራይ የራሷን ፓትርያርክ ትሾማለች” [vii] :: እንግዲህ ጳጳሳት በመሆን በአቡነ ጳውሎስ ተሹመው ቤተ ሲኖዶሱን የተቀላቀሉት እንዲህ አይነት አባቶች ናቸው::የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን እንዲህ አይነት አደገኛ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች::የህወሀት አምባሳደርና ካድሬዎች የነበሩ መነኮሳት ሲኖዶሱን እየተቆጣጠሩትና ሲኖዶሱንም የፖለቲከኞች ስራ ማስፈጸሚያ እያደረጉት ነው::

የማህበረ ቅዱሳን ፓትርያርክ

የሴራው መሀንዲሶች ይሄን እኩይ ስራቸውን ለመሸፈንና ራሳቸውን ከደሙ ንጹህ ለማሰመሰል በርካታ ማጭበርበርያዎችን ሲጠቀሙ ቆይተዋል:: ከዚህም አንዱ “ማሀበረ ቅዱሳን የራሱን ፓትርያርክ ሊያሰመርጥ እየተሯሯጠ” እንደሆነ ማስወራትና ሕዝቡን ለማደናገር መሞከር ነው::ይሄም አላማው ሁለት ነው:: ባንድ በኩል ማህበረ ቅዱሳንን በሕዝቡ ለማሰጠላት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የፓትርያርክ ሹመት ሽኩቻው ውስጥ መንግስት እጁ እንደሌለበትና መተራመሱ ያለው የተለያየ አላማ ባላቸው የቤተ ክርስትያኗ አካል እንደሆነ ለማስመሰል ነው:: ይሄንንም ከዳር ለማድረስ በተለይ ወያኔ በውጭው ዓለም ያሰማራቸው ሰላይና ቅጥረኛ ጸሀፊዎቹ ” ከፓትርያርክ ሽኩቻውና እርቀ ሰላሙ አለመሳካት ጀርባ ማሀበረ ቅዱሳን መኖሩንና ዓላማውም የራሱን ፓትርያርክ ማስመረጥ” እንደሆነ ጆሮ አደንቁር የሆነ ጽሁፍ በማውጣት የወተቱ ጠቆረ ማሩ መረረ ዘመቻውን አፋፍመውት ከርመዋል- የሚሰማቸውና የሚያምናቸው ባይኖርም::

ሌላ የጨለማና የውዝግብ ዘመን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን

የፓለቲካውን ጉዳይ ለማስፈጸም እንጂ ለቤተ ክርስትያኗ እድገት ብዙም ደንታ ባልነበራቸው በአቡነ ጳውሎስ ዘመን ቤተ ክርስትያኗ የተከታዮቿን ሰባት ፐርሰንት አጥታለች:: በቀረውም ምእመን ላይም ከባድ የሞራል የስነ አእምሮና ባባቶች ላይ ተስፋ የማጣት ሁኔታ ተከስቷል:: ተጀምሮ የነበረው እርቀ ሰላምም መክሸፉ የብዙዎችን ልብ ሰብሯል:: ከሁሉም በላይ አሳሳቢው ግን አሁንም ቀጣይ የሚመረጡት ፓትርያርክ ጉዳይና ሁለቱም ሲኖዶስች ውስጥ እየታየ ያለው ሃይማኖትን የመገዝገዝ አባዜ ነው:: የውጭው ሲኖዶስ በቤተ ክርስትያኗ የሀይማኖት ህጸጽ ( ስህተትና ኑፋቄ) ተገኝቶባቸው ከቤተ ክርስትያን ተለይተው የነብሩ መናፍቅ ሰባክያንን በማወቅም ይሁን ጡንቻ ለማጠንከር እያስጠጋቸው ነው:: አልፎ ተርፎም የቤተ ክርስትያን አስተዳዳሪ ሲሆኑ እየታየ ነው:: ከዚህም አልፎ የውጭው ሲኖዶስ በሚያስተዳድራቸው አብያተ ክርስትያናት ውስጥ ” ዘመኑን ለመዋጀት ” በሚል ሽፋን በቤተ ክርስትያኗ ቀኖና ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተደነገጉ እነ ኦርጋንና ፒያኖን የመሰሉ መሳርያዎች ገብተው የአምልኮውን መልክ እየቀየሩት ነው:: የአዲስ አበባውም ሲኖዶስ የመንግስት under cover agents የሆኑ ጳጳሳት ተሰግስገውበታል:: እነዚም ወገኖች ዓላማቸው የፖለቲካውን አጀንዳ ማስፈጽም እንጂ ሃይማኖት ባለመሆኑ ለቤተ ክርስትያኗም ሆነ ለመንጋው ደንታ የሌላቸው ጨካኞች ናቸው:: ቤተ ክርስትያኗ ከሁለት ወገን ተንጋላ እየታረደች ነው::

ለዚህ ሁሉ መሰረት የሆነውን ችግር ታላቁ ካናዳዊው ተመራማሪ ፕሮፌሰር ቴዎዶር ቬስቴል ይህንን ጉዳይ እንዲህ ሲሉ ነበር ያስቀመጡት

“This and other acts of violence in and around churches have alienated the Patriarch from his spiritual flock and have contributed to the EPRDF goal of exploiting internal contradiction with in the EOC leadership to weaken any opposition to the front. [viii]

ግን ወያኔ ለዘላለም ይኖር ይሆንን? የቤተ ክርስትያን አምላክ ሆይ ቤትን አጽዳ!

ማጣቀሻ መጻሕፍት


[i] Berhe, Aregawi , A Political History of the Tigray People’s Liberation Front (1975-1991): Revolt, Ideology and Mobilization in Ethiopia

http://harep.org/ifaapr/7219.pdf

[ii] John young  , Peasant revolution in Ethiopia The Tigray people Liberation front 1975-1991  Cambrige University Press 1997 pp 176

[iii] Berhe, Aregawi , A Political History of the Tigray People’s Liberation Front (1975-1991): Revolt, Ideology and Mobilization in Ethiopia (http://harep.org/ifaapr/7219.pdf)

[iv] ibid

[v] Ibid

[vi] Leencho Leeta , The Ethiopian State at the crossroads  Red Sea Press

[viii]  Theodore M Vestel , Ethiopia : a post cold war african state pp 158

ecadf.com

ኢትዮጵያ፡- ሃለፊነታቸውን የዘነጉት ግድ የለሽ ምሁራን

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

በቅርቡ ናኦም ቺሞስኪ: የኤም አይ ቲ (M.I.T.) ዩኒቨርሲቲ የስነ ቋንቋ ፕሮፌሰርና የአሜሪካ ቀደምት ምሁር፤ ለአልጀዚራ ስለአሜሪካ የቀለም ሰዎችና ምሁራን በሰጡት ቃለ መጠይቅIrresponsibility-of-Privileged Irresponsibility of the Privileged? Alemayehu G. Mariamላይ ምሁሮቹ ሃላፊነት ጉድለትና ግድ የለሽነት አንደሚያሳዩ መግለጫ ሰጥተው ነበር፡፡ ላለፉት 4 አሰርት ዓመታት የ84 ዓመቱ ቺሞስኪ ተጋፍጠው ፤ ሃይላነ ጉልበተኞች ነን የሚሉትንም በሃቅ አለንጋ ሲሸነቁጣቸው ነበር፡፡ በቅርቡም የፕሬዜዳንት ኦባማን ደካማ ጎን አስመልክቶ ትችቱን ሲያሰሙ ፤ ፕሬዜዳንቱ ‹‹የዓለም አቀፍ የግድያ ዘመቻ ለመፈጸም›› የድሮን (ሰው አልባ አሮፕላን )ጦርነት አካሂደዋል›› በብለወ ነበር:: በሃቅኝነታቸው  ምክንያት ቺሞስኪ ‹‹ግራ ክንፈኛ›› ‹‹አክራሪ ፖለቲከኛ›› ከዚያም አልፎ ‹‹ኮሚኒስት›› በመባል ተኮንኗል፡፡ በርካታ ዋጋ ቢስ ቅጽል ስሞችም ተለጥፎባቸዋል፡፡ ያሻውን ቢባሉም  ተናጋሪው የዕድሜ ባለጸጋ ከቆሙበት ዓላማ ዝንፍ ሳይሉ፤ ያነሱትን ነጥብ ሳይለቁ ሳይስቱ  ተጠናክሮ እንደቀጠሉ ነው፡፡አሁንም ካታሊዝምን፤ ኒዎ ሊቤራሊዝምን፤ግሎባላይዜሽንን፤ጦር ሰባቂነትን፤ ሙስናን፤ ጭቆናን፤ ስልጣንን አለአግባብ መጠቀምንና በስልጣን መባለግን፤የሰብአዊ መብት መደፈርን፤በአሜሪካና በሌሎችም ሃገሮች ያለውን ሁኔታ ይተቻሉ፡፡ ከዚያ ባሻገር ደሞ የስነ ቋንቋ ምሁራዊ ተግባራቸዉን ከማከናወን ዝንፍ አላሉም ፡፡

‹‹ኖአም ቾምስኪ፡ የተሳካላቸው ሃላፊነት››፤ በሚል ለአልጄዚራ በሰጡትው ቃለ መጠይቅ፤ ቾምስኪ የአሜሪካንን ምሁራን ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ  የዜጎችን ስልጣን ለመግፈፍና ግራ በማጋባት ወደ ግዑዝነት በመለወጥ፤ተለማማጭ በማድረግና መከታ በማሳጣት ረገድ ማሕበራዊ ሃላፊነት ማጣት፤ንፉግነት፤ዘራፊነታቸውን አስመልክቶ ተችቷል፡፡

አል ጀዚራ፡-በፖለቲካ ውስጥ መካተት የምሁራንና የሌሎችም አዋቂዎች ሃላፊነት ነው?

ቾምስኪ፡- ሰብአዊ ፍጡሮችን ሁሉ ያካትታል፡፡ ሃላፊነት እኮ በምቹ ጊዜ ላይ ነው የሚለካው፡፡ ድሃ ሰው ከሆንክና በዝቅተኛ ቦታዎች የምትኖር ከሆነ፤ ምግብህን ለማግኘት ብቻ በሳምንት 60 ሰአታት የምትለፋ ቢሆን፤የሃላፊነት ደረጃህ ከምታገኘው ጥቅም አኳያ የሚለካ ይሆናል፡፡

አልጀዚራ፡- የተሻሻለ ጠቀሜታ ካለህ በምላሹ የበለጠ እንድትሰጥ ትገደዳለህ?

ቾምሰኪ፡- ነውና፡፡ የበለጠ ተጠቃሚ ከሆንክ፤ የበለጠ ስለሚመችህ ያንኑ ያህል ማበርከት ይኖርብሃል፡፡ የበለጠ ተጠቃሚ ስትሆን ሃላፊነትህም ያንኑ ያህል ነው፡፡ ይህ እኮ በጣም ተራ ግልፀ ነገር ነው፡፡

አልጀዚራ፡- ይህን ሁኔታ ታዲያ ለምን በአሜሪካ አናየውም? ስለሰዎች በሃብት እየደረጁ መሄድ ብዙ ይሰማል፤ በርካቶችም ወደ ድህነቱ እየወረዱ ነው፤ያም ሆኖ በሃብት የደረጁትና ያካበቱት ጊዜያቸውን፤ከሃብታቸው፤ ከችሎታቸው ከጥቅማቸው አኳያ ሲያውሉ አይታዩም?

ቾምስኪ፡- እንደእውነቱ ከሆነ ሃባታሞች የሆኑት እኮ ለዚህ ነው፡፡ህይወትህን የምትመራው እራስህን ብቻ ለማበልጸግ ከሆነና ጥቅምህና ሃሳብህ ያ ከሆነና የሌሎች ችግር ካልታየህና ግድ የለሽ ከሆንክ፤ ስለሌሎች ማሰቢያ ሕሊናም አይኖርህም፡፡ ይህ ‹‹እራስ ወዳድነት ነው›› እንደሙት አካል መሆን ነው፡፡ ይሄ የአያን ራንድ ፍልስፍና ነው:- ‹‹ስለማንም ግድ የለንም፡፡ እኔ እራሴን ለማደርጀት ብቻ ነው የማስበው፤ያ ደሞ ክቡርና የተቀደሰ ተግባር ነው፡፡”

ዕውቁ ጋናዊ ኢኮኖሚስት እና በአፍሪካ ግንባር ቀደሙ ምሁር፤ ጆርጅ አይቴ በአፍሪካውያን ምሁራንና ዕውቀት የዘለቃቸው ታዋቂዎች ስላጡት የሃላፊነት ብቃት ቅሬታውን ከማሰማት አልቦዘነም፡፡ የአፍሪካ የምሁራን ክፍል ‹‹ከአፍሪካ ደም መጣጭ መሪዎች›› ጋር አንሶላ በመጋፈፍ ከመናጢውና ምስኪኑ ሕዝብ ላይ በመግፈፍ ኪሳቸውን ለመሙላት አሸሼ ገዳሜ ላይ ናቸው፡፡ በ1996 ለአፍሪካ ምሁራን ስለምንነታቸው ከምር የሚያምንበትን ነግሯቸዋል፡፡ “የፖለቲካ ሰዎች፤ የበቁ መምህራን፤ጠበቆች እና ሃኪሞች እራሳቸውን እንደሴተኛ አዳሪ በችሎታ ከነሱ አናሳ የሆኑትን ወታደራዊ ወሮበሎችን ፈላጭ  ቆራቾችን ላመገልገል እራሳቸውን አቅርበዋል፡፡ ደግመው ደጋግመው መልሰው መላልሰው እየተደፈሩ፤ ክብራቸው እየተገፈፈ፤ እየተሰደቡ፤ተሰልፈው ካገለገሉ በኋላ እንደቆሻሻ ጥራጊ ይጣላሉ—የባሰም ሊሆን ይችላል፡፡ እነዚህኞቹ ሲጠረጉና ሲጣሉ፤የበለጠ ክህሎት ያላቸው ምሁራን ሴተኛ አዳሪዎች በቦታቸው ለመተካት አንዱ በአንዱ ላይ በመጨፈላለቅ ይሽቀዳደማሉ›› ነበር ያሉት  አይቴ፡፡

የታደሉትና የተሟላላቸው ኢትዮጵያዊ  ምሁራን ሃላፊነት ማጣት

እና ታዲያ ለምንድንነው የኢትዮጵያን ምሁራን በፖለቲካው መስክ የማናያቸው? ምናልባት በአሜሪካን አቻዎቻቸው እግር በመተካት ላይ ይሆኑ? ወይስ የአያን ራንድ ፍልስፍና ተከታዮች ሆነው ይሆን? ‹‹ስለማንም ደንታ የለኝም፡፡ እኔ ስለራሴ ብቻ ነው ጭንቀቴ፤ያ ደሞ  የተቀደሰና ክቡር ምግባር ነው::›› የአይቴ ነቃፊ ትችት ለኢትዮጵያ ምሁራንም ይሰራ ይሆን?

በጁን 2010 አንድ ጥያቄ አንስቼ ነበር፡- ‹‹የኢትዮጵያን ምሁራን ምን በላቸው የት ገቡ?›› የሚል፡፡ በዚያን ወቅት መልስ አላገኘሁም ነበር::  አሁንም ምላሽ ባላገኝም ቀድሞም ሆነ አሁንም፤  ጉልህ በሆነው ከሕዝባዊ መድረኩ መጥፋታቸው ለረጅም ጊዜ ግራ ተጋብቻለሁ፡፡ ድርጊታቸው የጥንቱን ‹‹የግሪክ ፈላስፋ ዲዎጋንን፤ በጠራራ ጸሃይ ፋኖስ ይዞ ታማኝ ሰው ፍለጋ›› በአቴንስ ጎዳናዎች ላይ  የወጣውን አስታወሰኝ፡፡  ልክ እንደዲዎጋን፤ ዓለም አቀፎቹን የምእራቡን የምሁራን አምባ፤ የስነጥበብን የሳይንስ ሙያ ሰፈሮችን ገዳም መሰል መሸሸጊያዎችን፤ችቦ በመያዝ የኢትዮጵያን ምሁራን በየጉዳንጉዱ ሁሉ መፈለግ ያስፈልግ ይሆናል::›› ሆኖም  የትም ቢዳከር አልተገኙም፡፡ምናልባትም በማያሳይ ልዩ መጠቅለያ ተጀቧቡነው ተሰውረው ይሆን?

እውነቱን ለመናገር እኔም ለረጅም ጊዜ በዚያ የኢትዮጵያዊያን ምሁራን በተሸጎጡበት ያልታወቀ መደበቂያ ውስጥ ምንም ላለመተንፈስ፤ መስማት የተሳነኝ ድምጽ አልባም የሆንኩ ነበርኩ፡፡ ከዚህ የተሸፈንኩበት ዋሻ ለመውጣት ያበቃኝ የመለስ ዜናዊ ጦረኞች 196 ንጹሃን ዜጎችን እያነጣጠሩ ለሞት ሲዳርጓቸውና ከ800 በላይ የሚሆኑትን ሲያቆስሉ ማወቄ ነው፡፡ መቸም በሴቷም ሆነ በወንዱ ሕይወት ውስጥ አንድ ወሰኝ ወቅት አለን::  ከታፈንበት ማነቆና ዝምታን በመስበር በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸመውን ኢሰብአዊነት፤ግድያ፤ ለማውገዝና ከተጎጂዎች ጋር ቆመን ለመጮህ የምንቆርጥበት፤ ክፉ ዘመንን አስወግደን ነጻነትን የምናመጣበትን ጊዜ የምናመቻች የምንሆንበት ወቅት ይመጣል፡፡ ላንዳንዶቻች  አንደዝዚህ ይሆናል::

ነገር ግን ትንፍሽ ላለማለት ለእራሳቸው ቃል ገብተው መኖርን፤ ምርጫቸው፤ የነቃ ሕሊናቸው፤ የወሰነላቸው በማድረግ የተሸሸጉ አሉ፡፡ምርጫ በጠራራ ጸሃይ ሲሰረቅ እያዩ በውቅታዊ መታወር መኖርን ምርጫቸው ለምን  አደረጉ? ለምንስ ንጹሃን ዜጎች በዘፈቀድ በደህንነት አባላት ሲያዙ፤ በእርባና ቢሱና ፍትሕ አልባ በሆነው ‹‹ችሎት›› ሲፈረድባቸው፤እየሰሙ ጆሮ ዳባ ልበስ ማለታቸውስ ለምን?  የዕምነት ነጻነት ሲደፈርና ሕብረተሰቡ ነጻነትን ሲማጸን እየመሰከሩ ለምንስ አብረው አልቆሙም አልወገኑም? ሕሊናቸውን በማጽናናትና በዝምታ በማማረር በማላዘን፤ በሰሙኝ አልሰሙኝ መቆጨት ምርጫቸው ለምን አደረጉ? በዝምታ ተሰውረው መኖር ነው ሕይወታቸው፡፡

ይህን መገንዘብ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ምናልባት ዝምታ ወርቅ ነው የተባለውን በማመን ይሆን? ወርቅ ከፈለግህ ዝም በል ማለት ነው? ጭቆናን የምያራዘመው ዝምታ አንደሆነ ዘነጉትን? ምናልባት ምናልባት፤ ዝምታቸው መሃይምናን እና ኋላቀር ብለው ለሚገምቷቸው፤ ስለሚያሰሙት ጩኸት ተቃውሟቸው ሆኖ ይሆን? ‹‹አረመኔያዊ የሆነው ውሸት በጸጥታ መገለጹን›› ቸል ብለውት ይሆን?  አረመኔያዊ ድርጊቶች በጸጥታ መታለፋቸውንስ? ይህ ስሜትን የሚነካ ተግባራቸው ‹‹ለማንም ደንታ የለኝም፡፡ እኔ ስለራሴ ብቻ ነው ጭንቀቴ፤ያ ደሞ  የተቀደሰና ክቡር ምግባር ነው›› የሚለውን የአያን ራንድን ፍልስፍና ተቀብለውት ይሆን?

ነገር ግን ዝምታ ወርቅ አይደለም፤ ዝምታ ገዳይ ነው፡፡ የጅርመን ምሁራን ናዚ ወደስልጣን መወጣታቱን በተመለከተ በዝምታ ሲዋጡ የታዘበው ናይሞለር ምሬቱን ሲገልጽ፡-

በቅድሚያ ኮሚኒስቶች ላይ አነጣጠሩ፤

የዚያን ጊዜ ኮሚኒስት ስላልነበርኩ ዝም አልኩ፤

ቀጥለው በሶሻሊስቶች ላይ አነጣጠሩ፤

የዚያን ጊዜ ሶሻሊስት ስላለነበርኩ ዝም አልኩ፤

ለጥቀው ወደ ሠራተኝው ማሕበር አነጣጠሩ፤

የዚያን ጊዜ የሠራተኛው ማሕበር አበል ስላለነበርኩ ዝም አልኩ፤

መጨረሻ ላይ ወደኔ መጡ፤

በዚያን ጊዜ ለኔ የሚጮህልኝ አንድም አልተረፈም ነበር፡፡

ዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር እንዳስጠነቀቁት፤ ‹‹በመጨረሻው የምናስታውሰው የጠላቶቻችንን ቃላትና ድርጊት ሳይሆን የወዳጆቻችንን ዝምታ ነው::››

የኢትዮጵያዊያንምሁራንማሕበራዊሃላፊነት?

የሕዝብ ድምጽ የዓምላክ ድምጽ ነው (vox populi, vox dei) ይባላል፡፡ ሆኖም ጸጥታ ከተጨቆኑ ጋር መነጋገርያ  መገናኛ ሊሆን አይችልም፡፡ ምሁሩ ለመናገር፤ለማሰብ፤ ለማወቅ፤ ለመፍጠር፤ በሃሳቡ ለማየት የታደለ ነው፡፡ ጸጥታ ዝምታ የተጨቋኞች፤ የተወነጀሉት፤ የተፈረደባቸው ከታደሉት አነስተኛው ሁኔታ ነው፡፡ ዝምታ የምስኪኖች፤ የአቅመቢሶች፤ መከላከያ አልባ ለሆኑት የመጨረሻው የችግርና የአማራጭ ማጣት የመኖራቸው ምርጫ ነው፡፡

ምሁራን በዝምታ ለታገዱት የመናገር የሞራል ግዴታና ሃላፊነት አለባቸው፡፡ በዝምታ ቆሞ ምንም ሳያደርጉ በችግር ጨኸት ስር ማጉረምረም ጨርሶ ምርጫቸው ሊሆን አይገባም፡፡ ለመማር፤ ለማሰብ፤ ለመጻፍ፤ ለመፍጠር የታደሉት፤ በቁሳቁስ እጦት ለተጎዱት ብቻ ሳይሆን ሰብአዊ ክብራቸው ለተገፈፈባቸውም ሕዝቦችም መልሰው መስጠት፤ መክፈል  መቻል አለባቸው፡፡

በዝምታ የተዋጡት የኢትዮጵያ ምሁራን የሳቱት አንድ ነገር አለ፡፡ ዝቅ ተደርገው ለሚታዩት፤ ለተናቁት፤ ድምጻቸው ለታፈነባቸው መናገር ጫና ሳይሆን መታደል ነው፡፡ ድምጽ አልባ ለሆኑት ድምጽ ለመሆን መብቃት የተለየ ክብርና ሞገስ ነው፡፡ ለገዢዎችና ለጉልበተኞች፤ ኃይል ያጡትን ወክሎ ዕውነትን ማሳወቅ፤ዋጋ የማይተለምለት ታላቅ ስጦታ ነው፡፡

ዝምተኛው ምሁር፡- የሞራል ግዴታውን በመርሳት፤ደስታውን ከማሳደድ ባሻገር፤ ከራስ ለማትረፍ ከመሯሯጥ ባለፈ፤ በፕሮግራም ታስሮና ተለጉሞ ከዚያ ውጪ የማይንቀሳቀስ የከፍተኛ ትምህርት ምሩቅ ግኡዝ ሮቦት ከመባል ውጪ ሊሆን አይችልም፡፡ በአንድ ወቅት ኒትዝኪ እንዳለው፤ ሁሉም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ‹‹ሰዎችን ወደ ማሺንነት የሚቀይሩ ተቋማት ናቸው›› በሱ ዘመን ሮቦት (በራሱ የሚንቀሳቀስ ተሽከርካሪ)አልተፈጠረም  ነበርና፡፡

በኔ እምነት ምሁራን የሞራል ዝግጁነት ሃላፊነት ሊኖራቸው ብቻ ሳይሆን፤ በተግባርም ሊወጡት ተገቢ ነው፡፡ ማለትም አንድ ሰው ለአንድ ዓላማ ሲቆም፤ ይህ ውሳኔው ከራሱ ጥቅምና ፍላጎት ባለፈ በርካታ መስዋእቶችን እንደሚያስከፍለው መረዳት አለበት፡፡ በርካታ ምሁራን ስለሰብአዊ መብት መደፈር የመቃወም ግዴታ እንዳለባቸው አበክረው ቃል ይገባሉ፤ በዚያ ጉዳይ ላይ ለመናገር ግን ዝግጁ አለያም ፍቃደኝነቱ በተግባር የላቸውም፡፡ በስልጣን የሚካሄድን ብልግና ለማጋለጥ አፋቸው አይደፍርም፡፡ ለመጻፍም ብዕራቸው ይዶለድማል፡፡ እርሳሳቸውም መቅረጫው ተሰብሯል፡፡ አንዳንዶች አይናፋር ናቸው፤ሌሎች ደሞ ድንበር የለሽ ፈሪዎች ናቸው፡፡ስለዚህም የሚናገሩት ድምጻ አልባ በሆነው ዝምታቸው ነው::

በ1967 ቾምስኪ ሲጽፉ  ‹‹የገዢዎችን ቅጥፈት ማጋለጥና እውነቱን ማሳወቅ የምሁራን ግዴታ ነው:: ተግባራቸውን  በመመርመር፤ ዓላማቸውንና ድብቅ እቅዳቸውን ይፋ ማድረግ…ለዕውነት መቆም የምሁራን ድርሻ ነው እንጂ ተከታዩን የነጻነትን ጥያቄ ለማጭበርበሪያነት እንዲጠቀሙበት መፍቀድ አይደለም::›› እንደኔ  እምነት የኢትዮጵያ ምሁራን ሊሸከሙት የሚገባቸውም ይህንኑ ነው፡፡ ሙግት መግጠም ያለባቸው በስልጣን ላይ ያሉት ጨቋኞች ጋር ብቻ ሳይሆን እርስ በርሳቸውም ነው፡፡ የኢትዮጵያን ሕብረተሰብ ስለገጠመው ሁኔታና ችግሮች የተሻለ አማራጭ ብርታትና አለኝታነታቸውን፤ የጠነከረ ተስፋ ማቅረብ ይገባቸዋል፡፡ አምባገነኖችን በአዳዲስና ጠንካራ አስተሳሰቦች  መዋጋት ከፍተኛ ግዴታቸው ነው፡፡ ታሪክ እንደሚያረጋግጠው ጊዜው የደረሰ ጠቃሚ ሃሳብ ጨርሶ ሊሸነፍ አይችልም፤ ሊገታም አይሞከረም፡፡

ኢንተርኔት በጭቆና ተግባሪዎችና በነጻነት ድል አድራጊዎች መሃል ያለውን ትግል አኩል ለማድረግ ችሏል፡፡ኢንተርኔት የቅሬታን ክረምት በመግፈፍ በመካከለኛው ምስራቅ ላሉ በሚሊዮን ለሚቆጥሩ የችግርና የመከራ ሰለባዎች፤ በጋውን የበለጸገ የነጻነት ወቅት በማድረግ እስካሁንም ሳይጠወልግ እንደቀጠለ ነው፡፡ ሙባረክ፤ ቤን አሊ፤ ጋዳፊ፤ ባግቦ፤ እና በርካታ  ሌሎችም በሕዘቦቻቸው ውስጥ ዘልቆ የገባውን የጭቆና ስርአት በነጸነት የመተካቱ ሃሳብ ጨርሶ በህልማቸውም ታይቷቸው አያውቅም፤ የሚታሰብም አልነበረም፡፡ የኢትዮጵያም ዲካታተር ጨቋኝ ማን አለብኝ ገዢዎች፤ ምንም እንኳን ጋዜጦችን፤ ቴሌቪዥንን፤ ኢንተርኔትን እንደገል ንብረታቸው ይዘው፤ በርካታ ለሕዝብና ለሃገር የሚጠቅም ተግባር ሊከናወንበት የሚችለውን ከሕዝቡ በታክስና በተለያየ መነሾ የሚሰበሰበውን ገንዘብ በማውጣት ከውጭ ዕውነት የሚያጋልጡትን መገናኛ ብዙሃን ለማፈን ቢያውሉም፤ዕውነትን ሳንሱር በማድረግ ሕዝቡ መስማት የሚፈልገውን እንዳይሰማ ለማገድ ቢፍጨረጨሩም፤ ሕዝቡ የሚፈልገውን ከማድመጥና ከማወቅ ሊያቆሙት አልሆነላቸውም፡፡ ይህ በገሃድ የሚታይ አዉንታ ነው:: በዚህም ኢትዮጵያዊያን ምርጫቸውን እያዳመጡና እየተገነዘቡ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ምሁራን በዚህ የትም ባለው መገናኛ ላይ ድርሻቸውን ለመወጣት አልተቻላቸውም፡፡የዚህም ውጤት ወጣቱ ትውልድ ኢንተርኔትን ለርካሽ መዝናኛዎችና ለግሳንግስ ተረብ ሚዲያውን መጠቀሚያ ሊያደርገው ተገዷል፡፡

የኢትዮጵያ ምሁራን የሶሻል፤ፖለቲካዊና የሳይንሳዊ ለውጥ ግንባር ቀደም ሃላፊ መሆን አለባቸው፡፡ ይህን እያቆጠቀጠ ያለውን ሚዲያ፤ ለወጣቱ ትውልድ ትክክለኛውን እውቀት ለማስጨበጥና ሃገራቸው ላይ የተከመረውን መከራ መግፈፊያነት እንዲውል ማድረግ ገዴታቸው ነው፡፡ ወሳኙ ትንቅንቅ የወጣቱን አስተሳሰብና ልብ ለመያዝ መቻሉ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ከዲክታተሮችና ከጨቋኞች ጋር ያለውን ግብግብ በድል ለመወጣት አስፈላጊውና ወሳኙ፤ ጠመንጃና ታንክ ሳይሆን አዲስና ሃሳብና ፈጠራ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ከዚህ በማነቆ ከያዛት አስከፊ ስርአትና እርባና ቢሶች የስርአቱ አጎብዳጆችና ባለስልጣናት ማነቆ ለመላቀቅ ያለው ወሳኝ አማራጭ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ፤ኢኮኖሚ፤ ዕውቀት እስካልሆነና ምሁራኑም የመሪነት ሚናቸውን ለመወጣት እስክልተንቀሳቀሱ ድረስ፤ ከዚህ እራሱን በራሱ በመኮፈስ በዙፋኑ ላይ ከተከመረው ጨቋኝ ገዢ መላቀቂያው አስቸጋሪ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ምሁራን መላ ችሎታቸውን ጉልበታቸውን ጊዜያቸውን በኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ላይ ነው ማዋል ያለባቸው (በአቦሸማኔው ትውልድ ላይ):: አዳዲስ ጥልቅ ሃሳቦችን ለወጣቱ ትውልድ ነው መወርወር ያለባቸው፡፡ አዳዲስ ሃሳብን እንዲሞክሩትና በውጤቱ ሃይል ላይ እንዲጨምሩት፤ ሂሳዊ አስተሳሰቦችን በመዝራት እንዲያለሙት፤ ነጻ አስተሳሰብንና መጠያየቅን በውስጣቸው እንዲያስተላልፉ፤ ዘወትር በባለስልጣናት ገዢዎች ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በምሁራኑም በራሳቸው ላይ ተጠራጣሪ እንዲሆኑ ማበረታታት፤ ጥላቻን፤ቡድናዊ ስሜትን፤መንጋ አስተሳሰብን መዋጋት ማስተማር፤እራሳቸውንና አስተሳሳባቸውን የሚመዝኑበት መሳሪያ አስታጥቋቸው፤ተጻራሪ አስተሳሰቦች በማስረጃ ተደግፈው አሳማኝ ከሆኑ፤ሃሳባቸውን እንዲቀይሩ አስተምሯቸው፤የቆዩ ችግሮችን በአዲስ አስተሳሰብና መፍትሔ እንዲያርሙት አመላክቷቸው፡፡ስህተት ሲሰሩ ስህተታቸውን አምነውና ተቀብለው ለመታረምና በስህተታቸውም ይቅርታ እንዲጠይቁ ዝግጁ አድርጓቸው፡፡ ለዕውነት እንዲቆሙ፤ለሰብአዊ መብት መከበር ጥብቅና እንዲቆሙ በማስተማር መሆን ያለባቸውን ትክክለኛ ሆኔታ ለመሆን እንዲችሉ መንገዱን ምሯቸው፡፡

በጁን 2010 ባቀረብኩት ጦማሬ ላይ የኢትዮጵያን ምሁራን ከተጨቆኑት ጋር እንዲወግኑ አሳስቤም ተማጥኘም ነበር፡፡ያን ከጻፍኩ በኋላ፤የኢትዮጵያ ምሁራን ዝምታ አደናቋሪ ነበር፡፡ ይህን መልዕክት ልብን በሚያደፋፍሩ ቃላቶች ብዘጋው ደስ ባለኝ ነበር፡፡ ግን የዚያን ጦማር የመዝግያ አስተሳሰቤን አሁንም የቅሬታ ስሜቴንና የጨለመ ተስፋዬን  እንደያዘ ሰለሆነ ደግመዋለሁ፡፡

አመልካች ጣቴ ወደሌሎች በጠቆመ ቁጥር፤ ቀሪዎቹ ሶስት ጣቶቼ ወደኔ እንደሚያመላክቱ ቢጨንቀኝም አውቀዋለሁ፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ምሁራን ወዴት እንደደረሱ አውቃለሁ:: በዓለም ማእዘናት ገሚሶች ያልተዘጉት ዓይኖቻቸው ሳይጨፈኑ፤በዝምታ ውስጥ ታግተዋል፡፡ የትም ይሁኑ የትም፤ ደጋገሜ በድፍረት ላስጠነቅቃቸው የምሻው፤ በመጨረሻው ወቅት የ‹አይቴ አጣብቂኝ› ጥያቄ ጋር መጋፈጥ አይቀሬ ነው፡፡ ወይ ለኢትዮጵያ መወገንን ምረጥ፤ አለያም ከጨቋኞችና ከአምባገነን አውሬ መሪዎች፤ አስገድደው ከሚደፍሩ፤ ስልጣናቸውን አለአግባብ ከሚጠቀሙ፤ እና ሃገሪቱን ከሚያረክሱት ጋር አልጋ ተካፈል ፡፡

*የተቶረገመው ጽሁፍ (translated from):

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::) ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

ለተከታታይ አስር ቀናት የሕሊና እስረኞች ላይ ምስክር መደመጥ ይጀምራል።

ለተከታታይ አስር ቀናት የሕሊና እስረኞች ላይ ምስክር መደመጥ ይጀምራል።

Ethiopian muslim Prisoners

በመሪዎቻችንና በሌሎችም የሕሊና እስረኞች ላይ ነገ ምስክር መደመጥ ይጀምራል
ምስክሮች ዛሬ የማጠቃለያ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል፤
ከነገ ጀምሮ ምስክሮቹ ለሚደመጡባቸው አስር ቀናት አገር አቀፍ ዱአ እንዲደረግ ታዟል፤
አላህ በመስካሪዎቹ ላይ ተአምሩን እንዲያሳየን ሁሉም በዱአ እንዲበረታ ታዟል፤

ከሐምሌ አጋማሽ ጀምሮ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ታስረውና ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸው በማእከላዊ ለአራት ወራት ያህል የቆዩት በፊርማችን የመረጥናቸው ኮሚቴዎቻችንና ሌሎች የህሊና እስረኛ ወንድሞቻችን በተከሰሱበት የጸረ ሽብር ሕግ መሰረት ከነገ ጀምሮ ምስክሮች ይደመጡባቸዋል፡፡ ምስክርነቱ የሚደመጠው የበአላትና እረፍት ቀናትን ሳይጨምር ለተከታታይ አስር ቀናት እንደሆነም ታውቋል፡፡ መሪዎቻችን ለመወራት ያክል ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ ሲወያዩ ከቆዩ በኋላ ነገሮች ተቀልብሰው በተመሰረተባቸው የሽብር ወንጀል አቃቤ ሕግ 197 (አንድ መቶ ዘጠና ሰባት) የሰው ምስክሮችን አቀርባለሁ ብሎ መግለጹ የሚታወስ ሲሆን አዲስ የጸረ ሽብር ሕግ ስለሚፈቅድልኝም የምስክሮቹን ስምም ሆነ መልካቸውን ለደህንነታቸው ስል አሳልፌ አልሰጥም ሲል በክሱ ቻርጅ ላይ ገልጿል፡፡ ሆኖም አቃቤ ሕግ ያሰበውን ያህል ምስክሮች ማግኘት አንዳልቻለና ለመመስከር ፈቃደኛ የሆኑ በርካታ ሰዎችም በሐሰት አንመሰክርም የሚል ምላሽ በመስጠት ወደ ኋላ ማፈግፈጋቸው ተሰምቷል፡፡ ይህን ተከትሎም መንግስት አዳዲስ ምስክሮችን ከሰሞኑ ሲመለምል እንደሰነበተ ተሰምቷል፡፡

ይህ በእንዲህ አንዳለ ኮሚቴዎቻችን ላይ ከነገ ጀምሮ በሐሰት እንዲመሰክሩ የተመለመሉ የሐሰት መስካሪዎች ዛሬ ሙሉ ቀን በማእከላዊ ወህኒ ቤት ስልጠና ሲሰጣቸው መዋሉ ታውቋል፡፡ ዛሬ ጠዋት ጀምሮ በፕሮጀክተር በመታገዝና የኮሚቴዎቻችንን እና ሌሎች ታሳሪዎችን ፎቶዎች በማሳየት አቃቤ ሕጎች ለሀሰት መስካሪዎቹን ‹‹እንዳትሳሳቱ ይህ እከሌ ይባላል፣ የምትመሰክሩትም እንዲህ እንዲህ እያላችሁ ነው›› በማለት ሲያለማምዱዋቸው እና ሲያስጠኗቸው አምሽተዋል፡፡ ይህ የዛሬው ስልጠና እስከአሁን ለመስካሪዎቹ ሲሠጡ ለነበሩ ስልጠናዎች ማጠናቀቂያ እንደሆነም ታውቋል፡፡ ሆኖም በሐሰት መስካሪዎቹ በተለይም አንዳንድ ሽማግሌዎች ‹‹ኧረ በደንብ አይታይም፤ አልገባንም›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ መስካሪዎቹ በስልጠናው ሲመሰክሩ ምንም መደንገጥ እንደሌለባቸውና ከፌዴራል እስከ መከላከያ ድረስ ጥበቃ እንደሚያደርጉላቸው ተነግሯቸዋል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ ቀደም የሰሩት ወንጀል ካለ መንግስት እንደሚምራቸውና ከወረዳ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ ከሚገኙ የመንግስት አካላት የተለያዩ ጥቅማጥቅምች እንዲያገኙ የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጻፍላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል፡፡

ምንም እንኳ መስካሪዎቹ ከመንግስት መሰል የተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ቃል ቢገቡላቸውም መንግስት መሰል ጉዳዮች ላይ ካለው ልምድ በመነሳት ቃል የተገባው ነገር ፈጽሞ ተፈጻሚ እንደማይሆንላቸው አንድ አንድ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ አሰልጣኞቹ የመስካሪዎቹን ሞራል ለመጠበቅ እና ለማደፋፈር ‹‹እናንተ በአሁን ሰዐት የሃገሪቱ ትልቅ ባለውለታዎች ናችሁ›› እስከማለት የደረሱ ቢሆንም በሐሰት መስካሪዎቹ ዘንድ ያለው ፍርሃት ግን ከፍተኛ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለዚህ ፍርሃታቸው ማስታገሻም ለእያንዳንዱ መስካሪ በነፍስ ወከፍ እስከ 4 የሚደርሱ ደህንነቶች ተመድቦለታል፡፡ አንዳንድ መስካሪዎች ግን ፍርሃታቸው አይሎ ‹‹ነገ ህዝቡ መጥቶ ፎቶግራፍ እንዳያነሳን ጥበቃ ይደረግልን›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

መስካሪዎቹ ብዙዎቹ ያለፍላጎታቸው በማያውቁት ጉዳይ ሊመሰክሩ እንደሆነ ለቤተሰባቸው ከመናገራቸው ውጪ ማንም እንደማያውቅባቸው ቢያምኑም ከምስክርነቱ በኋላ ስማቸው እና ምስላቸው ለህዝብ እንደሚበተን በማወቅ በከፍተኛ ሁኔታ ሰግተዋል፡፡ ዛሬ መስካሪዎቹ ለምሳ እረፍት በወጡበት ወቅትም ሲጨንቃቸውና ትካዜ ሲወራቸው ታይተዋል፡፡ ጭንቀቱ የምርም ነገ ቀብር ላይ ስለሚጠብቃቸውና ረሱል ሰ.ዓ.ወ የከፋ ወንጀል አድረገው በጠቀሱት የሀሰት ምስክርነታቸው (ሸሀደተ ዙር) ጉዳይ ከሆነ አሁንም ግዜ እንዳላቸው መግለጽ ያሻል፡፡ በሐሰት መስክሮ በዱንያም በአኺራም የሚገጥማቸውን የሁለት አለም ኪሳራ ከመቀበል ባለመመስከራቸው መንግስት የሚፈጽምባቸውን ጥቂት እንግልት በጸጋ ቢቀበሉ ይሻላቸዋል፡፡ ሰውን ከመፍራት አላህን መፍራት ከምንም የላቀ ነውና፡፡

እኛም ከነገ ጀምሮ የሚካሄደውን የሀሰት ጉባኤ አላህ በተአምሩ የመሪዎቻችን ሰላማዊነት የሚያጸድቅበት፣ የሀሰተኞችም ሴራ የሚከሽፍበት ከምንም በላይ በመሪዎቻችን እና በሌሎችም ወንድሞቻችን ላይ ያለ ወንጀላቸው በሐሰት የሚመሰክሩ ግለሰቦችን መጨረሻን አላህ በቀናት ውስጥ እንዲያሳየን አብዝተን ዱአ ማድረግ እንጀምራለን፡፡ የሀሰት ጭፍሮች እውነትን በስልጠና እና በዱንያ ግሳንግስ ለመናድ የሚያደርጉትን ጥረት አላህ በተአምሩ ውድቅ አድርጎ እንዲያሳየን በጾም፣ በሰላት፣ በቁኑት፣ በሰደቃና ዱአ በርትተን በቀን በለሊት እንለምነዋለን፡፡ ከነገ ጀምሮም ሁሉም ሙስሊም ዘወትር ከነበረው መንፈሳዊነቱ የበለጠ ጊዜ ሰጥቶ በዱአ እንዲበረታ አደራ እንላለን፡፡ አላህ የተበዳዮችን ዱዐ የሚሰማ፤ የአማኞችንም እንባ የሚያብስ ጌታ ነውና፡፡
አላሁ አክበር

 Abbaymedia.com

ዛፍ በፍሬው ይታወቃል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ያስተላለፈው ውሳኔ ሀገራችንና ህዝባችን ምን ያክል አስከፊ ሁኔታ ውስጥ እንደገቡ ያሳያል፡፡ሲኖዶሱ በመንፈስ ቅዱስ ይመራል ቢባልም አንዴ ዶ/ር ሽፈራው ተክለማሪያም፤ አንዴ አቶ አባይ ጸሀዮ ፤ሲያስፈልግም አቦይ ስብሃት እና አቶ በረከት ስምኦን እየተፈራረቁ በቤተክርስቲያኒቱ ላይ የጥፋት በትራቸውን እያሳረፉበት ይገኛሉ፡፡እንግዲህ የመንግስት ሰዎች በዚህ መልኩ እየተፈራረቁ ተጽዕኖቸውን ሲያሳርፉ በውስጡ የተሰገሰጉት የወያኔ ወኪል አባቶች ደግሞ ህዝቡ ተደራጅቶ መብቱን እንዳያስከብር ጊዜ ለማግኘትና ውስጥ ውስጡን ለሰላም የቆሙ በመምሰል በሽምግልና እና በጸሎት አማካይነት ይስተካከላል እያሉ ሲያታልሉ ቢቆዩም ዛሬ የመንግስትን አቋም ለማስፈጽም መቆማቸውን በግልጽ አሳይተዋል፡፡

የመግለጫው ይዘት ስናየው ለማደናገሪያ ያክል በውስጡ አንዳንድ የመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶችና የግዕዝ ቃላቶች ከመግባታቸው በስተቀር ወያኔ በየሦስት ወሩ እያሳተመ ለአባላቶቹ ከሚያሰራጨው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ውዳሴ መጽሔት ከሆነችው የአዲስ ራዕይ መጽሔት፤ በበረከት ሰምኦን በኩል ከሚለቀቀው የመንግስትን አቋም የሚተነትን ተብሎ በመሰለ ገብረህይወት እየተነበበ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከሚቀርበው ፕሮፖጋንዳ የተለየ አደለም፡፡ከዚህ መገመት የሚቻለው መንግስት አስቀድሞ ተዘጋጅቶበት መግለጫው በሲኖዶስ እንዲነበብ መደረጉን ነው፡፡ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪወስ በ1984 ዓ.ም በአቶ ታምራት ላይኔ ፊርማ በተጻፈ ደብዳቤ መባረራቸው ያደባባይ ሚስጢር ሁኖ ሳለ ዛሬም በተለመደው ቅጥፈታቸው በገንዛ ፈቃዳቸው ጥለው ሸሽተዋል፣ስልጣኑን ለፈለጋችሁት ስጡት ብለዋል ተብሎ የተጻፈን ጽሁፍ የሲኖዶስ ውሳኔ ነው ብሎ ማውጣት ምን ያክል አሳፋሪ ተግባር ነው፡፡ጳጳሱ ወታደር ያላቸው ይመስል የቅድስተ- ማሪያምን ቤተክርስቲይን በታንክና በመትረጌስ አስከብበው የተወሰኑ ካድሬ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ተብየዎች የተቃውሞ ሰልፍ እንዲያዘጋጁ ተደርጎ በተቀነባበረ ሴራ እንደተባረሩ እየታወቀ በገዛ ፈቃዳቸው ለቀቁ ሲባል በተለይ አለም በቃን ካሉ መነኮሳት መስማት ምን ያክል አሳፋሪ ተግባር ነው፡፡

ማቴ.7፤16-20 ” ጥሩ ዛፍ መጥፎ ፍሬ አያፈራም፡፡እንዲሁም መጥፎ ዛፍ ጥሩ ፍሬ አያፈራም፡፡ዛፍ ሁሉ በፍሬው ያታወቃል፡፡” ባለፉት 38 ዓመታት ወያኔ ያፈራቸው የክህደት ፍሬዎች እንዳይናቸው ብሌን እንዲንከባከቡ ከእግዚያብሄር የተረከቡዋቸውን የመንፈስ ልጆቻቸውን በመበተን ይህን አሳፋሪ ተግባር አሜን ብለው ተቀብለዋል፡፡ዛሬም ቢመሽም ቅሉ ፈጽሞ አልጨለመምና በተለያዩ ዛቻና ማስፈራሪያ ምክንያት ያላመናችሁበትን የፈጸማችሁ አባቶች የእግዚያብሔርን ቃል አስታውሱ፡፡ከቤተ-ክርስቲያንና ከምእምናን ጎን በመሰለፍ የእስልምና እምነት ተከታይ የሀይማኖት መሪዎች እንዳደረጉት እንንተም ለእምነታችሁ መከበርና ለቤተክርሰቲያናችሁ አንድነት ነገቢውን ዋግ ክፈሉ፡፡

ማቴ.10፤26-28 “ እንግዲህ ሰዎችን አትፍሩ፤ምክንያቱም የተሸፈን መገለጡ አይቀርም፤ተሰወረም መታወቁ አይቀርም፤በሹክሹክታ የሰማችሁትንም በከፍታ ቦታ ላይ በይፋ አስተምሩ፡፡ለእናንተ ለወዳጆቼ እንዲህ እላችኋለሁ፤ስጋን ከመግደል አልፈው ነፍስን መግደል የማይችሉትን ሰዎች አትፍሩ፤ ይልቁን ነፍስን እና ስጋን በገሀነም ሊያጠፋ ሚችለውን እግዚያብሄርን ፍሩ፡፡” ይላል የእግዚያብሄር ቃል፡፡

ሉቃ.13፤6-7 “አንድ ሰው በአትክልቱ ውስጥ የተተከለች አንዲት የበለስ ዛፍ ነበረችው፡፡ከዚያችም የበለስ ዛፍ ፍሬ አገኛለፉ ብሎ በተለያዩ ጊዜያት እየሄደ ቢሞክርም ምንም ፍሬ ሳያገኝ ቀረ፡፡ስለዚህ አትክልተኛውን ጠርቶ ከዚች ዛፍ ፍሬ ለማግኘት ሦስት አመት ሙሉ ተመላለስኩ፤ ግን ምንም ፍሬ አላገኘሁባትም፤አሁን ቁረጣት ስለምን የአትክልቱን ቦታ በከንቱ ይዛ ታበላሻለች አለው”፡፡ እንግዲህ ከዚህ ምሳሌ መረዳት ሚቻለው ባለፉት 21 አመታት ፍሬ ያልሰጡትን አቡነ ጳውሎስን እና አቶ መለስ ዜናዊን የአትክልቱ ቦታ ባለቤት በቁጣ ቢነቅላቸውም ከትፋጣቸው መማር የማይችሉት ደቀ- መዛሙርቶቻቸው እነ አቶ አባይ ጸሀዬ እና አቦይ ስብሀት አንዲሁም ሌሎች የወያኔ ቡችሎች በጥፋታቸው ቀጥለውበታል፡፡ይባስ ብሎ በእነሱ ግፍና መከራ በስደት ኑሮዋቸውን መግፋት ሳያናሳቸው ሽብርተኛ በመሆናቸው አቡነ መርቆሪወስ ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል ሲሉ “አቫይ ጸሀዬ” ነግረውናል፡፡ወያኔዎች መልካም ፍሬ ለማፈራት የማይችሉ ተሰጣቸውን ሀገርን የማስተዳደር ትልቅ ሀላፊነት በተጠናወታቸው የዘር ልክፍት ምክንያት ህዝቡን ለብጥብጥ፣ ለሞት፣ለችግር እና ለስደት ከመዳረግ በቀር ሌላ ነገር የለም፡፡ውድ ኢትዮጵያውያን የእግዚያብሄርም ቃል የሚነግረን ፍሬ የማያፈሩትን ዛፎች ቆርጦ መጣል እንደሚገባ ነው፡፡የሌሌች ሀገሮችም ተሞክሮ የሚያሳየን ያለ ሀይል አልለቅም ብሎ በግድ የተጣበቀብንን ካናሰር በኃይል ቆርጦ መጣልና ነጻነታችንን ማስመለስ ነው፡፡

 

ከዕርቀ ሰላም ይልቅ ለ6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ ቅድሚያ የሰጠው የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ ተስፋዎችን አጨላሚ ሆነ

ደጀ ሰላም፤ ጥር 8/2005፤ ጃኑዋሪ 16/2013/

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና ከመነሻውም በውጪ ተጽዕኖ ሥር የወደቀው የቅ/ሲኖዶስ ጉባኤ እንደተፈራውም ዕርቀ ሰላሙን አሽቀንጥሮ ወርውሮ 6ኛ ፓትርያርክ በመፈረሙ ላይ ጸንቷል። በብፁዕ አቡነ አብርሃም በተነበበው መግለጫ ላይ እንደተጠቀሰው ቅ/ሲኖዶሱ ያደረገው ሙከራ ያልተሳካው በአሜሪካ የሚገኙት አባቶች ባቀረቧቸውና ከዕርቁ ጋር በማይገናኙ ሌሎች ምክንያቶች የተነሣ ነው። ይህ “ከእርቁ ጋር የማይገናኝ” የተባለው ምክንያት አሜሪካ ያሉ አባቶች የሚያነሧቸው “ፖለቲካዊ ጥያቄዎች” መሆናቸውን ደጀ ሰላም ትረዳለች። በተለይም ለብዙዎቹ የቅ/ሲኖዶስ አባላት የተነገራቸው ምክንያት “አገር አቀፍ ዕርቅ” ይውረድ ይላሉ፤ ውጪ አገር አሉት ፖለቲከኞችም አብረውን ካልገቡ ይላሉ የሚለው መልዕክት ነው።ከዕርቀ ሰላም ይልቅ ለ6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ ቅድሚያ የሰጠው የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ ተስፋዎችን አጨላሚ ሆነ

ዛሬ በቅ/ሲኖዶሱ ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሳይሆን ከሰሞኑ በተለያዩ ዜናዎች ስማቸው ተደጋግሞ ሲጠቀስ በሰነበተው በብፁዕ አቡነ አብርሃም የተነበበው መግለጫ የብዙዎች ምእመናንና ካህናትን ተስፋ እንደሚያጨልምና ወደ ቀቢጸ ተስፋም እንደሚከታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው። ጥበብና አስተዋይነት በጎደለው፣ ከሃይማኖታዊነት ይልቅ ፖለቲካዊ አንድምታው ጎልቶ በሚሰማው በዚህ ውሳኔ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከ20 ዓመታት በኋላ ድጋሚ ልታገኘው ትችል የነበረውን የአንድነት መንፈስ ተኮላሽቷል። ለዚህም ከታዋቂ ሰባኪ ነን ባዮች እስከ አንዳንድ “ልጅግር” ጳጳሳት፣ ተሰሚነት አለን ከሚሉ ጦማርያን እስከ ፖለቲከኞች ያደረጉት ርብርብ በርግጥም ቤተ ክርስቲያኒቱ አንድ እንዳትሆን የሚሠራው አካል እስከ ደም ጠብታ እንደተዋደቀ አሳይቷል፤ የብዙዎችንም አሰላለፍ በርግጥ ተረድተንበታል። የቤተ ክርስቲያን አምላክ ይፈርዳል!!

አንዳንዶቹ ጳጳሳትና ብሎገሮች እንዳሉት በርግጥ ለጳጳሳቱ ደሞዛቸውን የሚከፍላቸው አሜሪካና አውሮፓ፣ አረብ አገርና በሌሎች ዓለማት በስደት የሚገኘው ምእመን አለመሆኑ ብቻ የሚያስንቀው ከሆነ አገር ቤትም እያለ ጠቀም ያለ ገንዘብ መክፈል የማይችለው ደሃ ምእመን በእነርሱ ዘንድ ሞገስ የለውም ማለት ነው? በዚህ ደሃ ሕዝብ ገንዘብ ቤታቸውን አልሰሩምን? የሚንደላቀቁትስ በዚሁ ደሃ ምእመን ጥሪት አይደለምን? በሌላ ጊዜ ለዕረፍትም ለመዝናናትም የሚሆዱባቸው የአሜሪካና አውሮፓ አገራት ምእመናን አይሰሙ/ አይሰማቸው መስሏቸው ይሆን? ለማንኛውም በዚህ ውሳኔ አንድነምታ ዙሪያ ተከታታይ “ምልከታዎች” ማቅረባችን ይቀጥላል። ደጀ ሰላማውያንም ሐሳባችሁን እንድትሰጡ ከወዲሁ እንጋብዛለን።

ቸር ወሬ ያሰማን፤ አሜን።

 

ባለራዕይ አንባገነኖችን ህግ ያስጣሰ አውራዶሮ!

ገበሬ ነኝ ከቤልጄም

ሰላም ጤና ይስጥልን አንባቢያ !

በዘመናችን በተለይ አሁን ባለንበት እንሰሳት ታምራትን እያሳዮን ይገኛል!

አሁን በቅርብ ከጥቂት አመታት በፊት እንኳን አፍሮ የተባለ ፍየል ልክ እንደ ሰው

ቢራ ይጠጣ ፣ምግብ ይበላ እንደነበር ትዕይንቱን በቴሌቭዥን ተመልክተናል።

በሌላ በኩል ደግሞ ደቡብ ወስጥ እንድ ወደል እህያ ሽክሙን እንደያዘ በአንድ ወንዝ አካባቢ ከዕነ ሽክሙ ይተኛል  ቢደበደብ ቢደበደብ ጭራሽ እንደሞተ ሆኖ በመንፈራፈሩ ባለቤቱ አይ ጣር ይዞት ነው በማለት ሽክሙን ያራግፍና ቢያየው በዛው የሞተ መስሎ በመተኛቱ ጭነቱን ወደሌላ በማዛዎር እዛው ወንዝ አካባቢ ጥሎት ወደ ገበያው ያቀናል ።

ገበሪው ከሄደበት ገበያ እህሉን ሽጦ ወደቤቱ ሲመለስ አህያውን ከቦታው በማጣቱ በዓይኑ አካባቢው ይቃኛል ::

ያየውን በማየቱ ይደናገጥና ሰፈርተኛ ገበያተኛ መንገደኞችን እርዳታ ይጠይቃል፣አህያው ከተኛበት ሆኖ ያገኘው ጅብ ለመብላት ጠጋ በሎ ሊዘነጥለው ሲዳዳ ቆፍጣናው ወደል አህያ ከተኛበት ተፈናጥሮ የጅቡን ማጅራት ነክሶ ትግል ይገጥማል:: ገላጋይ በሌለበት ትግሉ ለረጅም ሰዓት ይቀጥላል!!

አያ ጅቦ ማጅራቱን ክፉኛ ተነክሶ በቆፍጣናው ወደል አህያ በመያዙ አቅም እያነሰው ይመጣና በዛው ያሽልባል ::

ወደል አህያው ግና የለም አለቅም እኔም ከአሳዳሪዪ በተመሳሳይ ቴክኒክ (ዘዴ) ከሽክም ተርፊያለሁ አንተ ግን ወደ ሆድህ ልትከተኝ በመሆኑ አለቅም ያለ ይመስል የኣያ ጅቦን ማጅራት እንደነከሰ ነበር የአህያው ባለቤት የተመለከተው ።

ስዎች ጉድ አሉ በጉድ ብቻ አልቀረም ሥራ ተጀመረ፣በተለምዶ እንደሚባለው እህያን ከጅብ ለማስለቀቅ ሳይሆን ፣ ጅብን ከአህያ ለማስለቀቅ የአህያው ባለንብረትና ገበያተኛው ደፋቀና ማለት ቀጠሉ።

ጅቡ መሞቱን ያረጋገጡት አልሞት ባይ ተጋዳይ ከቀን ጅብ ጋር ተጋጥሞ ያሽነፈወን ወደል አህያ ፣ ለማላቀቅ አሁንም እንደ ጠዋቱ ቢደበደብ ፣ ቢቀጠቀጥ፣ቢባል ፣ቢስራ ወይፍንክች የሽክም ጠላቱ ልጅ ፣በመጨርሻ እሳት አንድደው በሜጫ አፉን በማቃጠላቸው ለያዥ ለገረዥ የታከተው ወደል አህያ መቆም የለም ይበራል ይበራል ይበራል ፣ ለጉድ የተፈጠረው አህያ ወደቤቱ ሰተት ብሎ መግባቱን ስንሰማ ከጉድ ያለፈ ምንም አላልንም ።

በሊላ በኩል ደግሞ ጅብና አንበሳ በያመቱ የሚያደርጉት ጦርነት ከጅብ ስልሳና ሰባ ከአንበሳ አስርና አስራ አምስት ይሞታል።

ታዲያ የተናካሹን አውራ ዶሮ ብሶት እናም የህግ አግባብነት ያልተመለከተው ዳኛ ፣የዶሮው ጤንነት ሳይመረመርና በሽተኛነቱ ሳይረጋገጥ እንዲወገደ መወሰኑ ኢትዮጵያ ወስጥ ያለው ህግ መጣስ ፣ ከመጣስ አልፎ ለህግ ትኩረት ያለመስጠትና ለስረዓቱ አሽቃባጭነት ብቻ የቆመ የአሻንጉሊት ህግ ከመሁኑም ባሻገር በህግ ሞያ ያልሰለጠነ የስረዓቱ አሽቃባጭ ተቀጣሪ እንጂ ዳኛ አለመኖሩን ያረጋገጠ ነው እላለሁ።  ነጻነት የፍትሕ መሰረት ነው።

 

የጥፋት ራእይ፤ የክህደት ሌጋሲ

ራእይም ይባል ሌጋሲ፤ህልምም ይባል ምኞት አንድ ነገር እውነት ነው። ሰውየው፤ከተጀመረ ጀምሮ በሰላም ኑሮ እንቅልፍ አግኝቶ ስለማያውቅ ህልም አለመ፤ራእይም ነበረው፤አስቦና መዝኖ ሠራ ለማለት አይቻልም። ከፊቱ ነገ አልነበረችም። ሊባል የሚቻለው፤ የነበረው የጥፋት፤ የማፍረስ፤ የመበተን፤ የክህደት ቅዠት ብቻ ነው።

የዛፉ ምንነት በሚያፈራው ፍሬ ይመዘናልና፤ የተዋቸውን እናስቀጥላለን ከሚባለው ራእይ ባዶ ኳኳታና ጩኸት ማካከል ጥቂቶችን እንመልከት። ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል እንዲሉ፤ያልነበረውን እንደነበረ፤ ባዶውን እንዳለ፤ የማይሆነውን እንደሚሆን ሲሰበክና ሲቅራራ ሲወሸከት ሕዝብ እንደታዘበ፤ ታሪክም እንደመዘገበና የፈጠጠው እውንታ የሚታይ መሆኑን መካድ አይቻልም። ሚዛኑ፤የሕዝቡ የእለት እለት ኑሮ፤ያለው ነጻነትና መብት፤ስነልቡናው፤የዓለምአቀፍ ሕብረተሰቡ የሚወተውተው ምን እደሆነ ማየት ነው።

ዓይናችሁን ጨፍሉ ላሞኛችሁ፤እንደሰጎን ራስን አፈር ውስጥ ቀብሮ አልታይም-የብልጣብልጥ ሞኝነት ሲዘበት ሁለት አስርተ አመታት እንደለፉ፤ በእነዚህ ወርቃማ አመታት መልካም አስተዳደር፤ ቅን አመለካከትን ጥረት ታክሎበት አገር ትመጥቅ ነበር ማለት ምኞት ብቻ ቢሆንል፤ በእድገቷ ከሌሎቹ ቀርቶ ከአአህጉር እህት አገሮች ጋር በተስተካከለች ነበር፤ ምን ያህል ብዙ በተሰራ ነበር ያሰኛል። በእርግጥም ብዙ ሕይወት ተገብሯል፤ ሕዝብ ተጎሳቁሏል፤ መብት አልባ ሖኗል፤ ታፍኗል፤ ታስሯል፤ ተሰዷል፤ አገር ተበትናለች፤ ንብረት ባክኗል፤ በአገር በሕዝብ ላይ ከመቸውም የበለጠ አደጋ አንዣቧል።

እውነቱ ሌላ፤የሚወራው ሌላ። ብዙ ጊዜ በማደናቆር፤በመዋሸት፤በማሳሳት፤በተንኮልና ሸፍጥ አልፏል።

ህልምና ቅዠት፤ እውነትና ውሸት፤ማታለል፤መደለልና እውነተኛ ሕዝባዊ አረማማድን ሌለውም ሌላውም ሕዝቡ በሚገባ ለይቶ ስለሚያውቅ፤ነገ እንደታሪክ እንደሚወራ ማዘንጋት አያሻም። ትላንት ዛሬ ነበረች፤ ዘሬም ነገ ትሆናለች፤ ባጭሩ እንደማንኛውም ስርአት፤ ይኸም ስርአት ይሻግታል፤ይበሰብሳል ያልፋል። እውነታው ግን ለትውልድ ፈጥጦ ይቀራል።
ከእንግዲህ የሚሞኝ ከተገኘ በራሱ ፈረደ። ወደድንም ጠላንም፤የመዋሸት፤የማታለል፤የክህደት፤የጥፋት ጊዜ፤አብቅቷል። ሁሉም እርምጃውን ጠብቆ፤ጊዜውን ቆጥሮ ይመጣል። የተሰጋጀም ተዘጋጀ፤ የባከነም በከነ፤ጊዜው ሲደርስ እንደበሰበሰም ሆነ እንደ እንተዘመመ እንዳልነበረ ሲሆን፤ዞር ብሎ ትላንትን በመልከምም በሌላም መቃኘት አይቀርም። በተለያየ መልኩ፤ብዙ ዝምታ መስማማት ቢመስልም፤ከምዙ ዝምታ በሗል አበይት ክስተቶች ይኖራል። የሕዝብም ዝምታ ከዚሁ አይለይም። ዝም አለ ከተባለ ማለት ነው።

ብዙ ሳንርቅ፡ይህ ራእይ እየተባ ሲነገርለትና እንቀጥለው የሚባለው ምኑ ነው? ዲሞክራሲ ቢባል ዲሞከራሲ የለም፤ ነፃነት ቢባል፤ ነጻነት የለም፤መብት ቢባል መብት የለም፤እድገት ቢባል እድገት የለም-የሕዝቡ ኖሮ ምስክር ነውና፤እንደተባለውም “ምንም የለም”፤ሁሉም የለም። ታድያ እንቀጥል የሚባለው ምኑን ነው? በነበረው በአስ ጉልበት እንቀጥል ከሆነ፤የሆነው ለመቀጠል አያበቃም፤ቢመኙትም ከሕዝብ ፍላጎት ውጪ ነው። ፊት በሐይል በጡንቻ ነበር፤የማያስኬድ መንገድም አይደለም። ሃይልም ቢባል፤ የሃይል ምንጭና ሃይል የት እንዳለ ማስተዋል ያስልጋል።

ነገርን ቢደጋግሙት መሰለቻቸት ነው። እስኪ አበይት ነጥቦችን እንወርውር።

1. ያገር ክህደት የአገር መሸጥ ሌጋሲ፤

አገርን ወደብ አልባ እንዳላደረገ፤ያዋሳኝ ለም መሪትን ለጎራባች አገር አሳልፎ እንዳልሰጠ፤የአገሪቱን ለም መሬት በማን አለብኝነትና ቅን አስተሳሰብ በጎደለው የግድ የለሽ ውሎች፤ድሀ ገበሬን ከመኖሪያው ፈንቅሎ በርካሽ መቸብቸብ እድገትንም ልማትንም እደማያመጠ፤ ጅማሬውም ፍጻሜውም ግልጽ የሆነው፤ የክህደት፤የቅዠት ጉዞ ሊዘነጋ አይገባም። ባለ ራእዩ ያተረፈን የተዘጋች፤ለአምሳና ከዚህም በላይ ዓመታት የተሸጠች አገር ነች።

2. የታሪክ ክህደትና ማጉደፍ ሌጋሲ፤

ጠለቅ ያለ ዝርዝር ከመስጠት አንጥቦ ለማለፍ፤የዘመናትን ታሪክ ሽሮ ሚሊኒየም እንዳላከበር፤የጀግኖች ልጆችዋን ታሪግ በባዶ እብሪትና ትምክህት እንዳላንኳሰሰ፤ እንዳላጎደፈ፤እንቀጥል የሚባለው የጥፋት መንገድ ይህ ነው-ታሪክን መካድ መሻር ማንኳሰስ።

3. የአገር ብተና ሌጋሲ፤

አገርን በዘር፤በቋንቓ ሽንሽኖ ለትውልድ የማይሽር የጥፋት መረብ የዘረጋ ያስተዳደር ስልተ፤ፈጠነብ ዘገየ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ የጥፋት ቀመር ለመሆሉ በየጊዜው የታየ አሁንም እንደሰደድ እሳት በየአራት ማእዘን እየጤሰ ያለ፤የሚአስቀጥል ራእይ ወይስ የጥፋት ቅዠት?

4. የዘረፋ ሌጋሲ፤

በእድገት ጭራ፤በዘረፋ ከአለም ቀደምት፤ ከድሃ አፍ ነጥቆ በውጭ ባንኮች ሀብትን ማድለብ፤ በሺ ብር ደሞዝ የሚሊዮን ብር ህንዳ መገንባት፤ ከመንግስት ተበድሮ ሰይከፍሉ መበልጸግ፤ ከመንግስት ካዝና ወርቅ ብር በሚሊዮን የሙቆጠር መዝረፍ፤ መጋዘኖችን ወዘተ ባዶ ማድረግ፤ ያገሪቱን ኢኮኖሚ መቆጣጠር፤ የዜጎችን እጅ ማሰር፤ ስንቱ ይነገራል። ይህ ነው እንግዲህ የሚያስቀጥል ራእይ። እራስን መታዘብ ቢያቅት፤ ሌሎች እንደሚታዘቡ መገመት ምንኛ ብልህነት ነው። የለመደበትን እጅ ለመሰብሰብ ይበጅ ነበር። በቀደምት ስርአቶች ያልታየ። የህን በዚህ እንተወው።

5. የአፈና ሌጋሲ፤

ሕዝቡ፤የሕዝቡ ልጆች፤ ወጣቱ፤ምሁራኑ አፋቸው እንዳይናገር፤ ዓይናቸው እናዳያይ፤ብእራቸው እንዳይፅፍ፤ እዳይሰበሰቡ፤እንዳይደራጁ፤ለአገር እንዳይመክሩ፤ ለመብት ለነጻነታቸው እንዳይቆሙ፤ይህንንም ካደረጉ፤ በህግ ከለላና ህግ ከሚፈቅድላቸው ውጪ የግፍ ግፍ ሲዘንብባቸው ለመኖሩ በየፈርጁ የተመዘገበ፤በቂ ማስረጃና ሕያው ዋቢ ያለው የሚያስጠይቅ እየቀጠለ ያለ ሂደት መሆኑ ባጽንኦ መጤን አለበት። በዚህ መስክ የጥፋቱ ራእይ እንደቀጠለ መሆኑ አይካድም።

6. የጥፍጠፋ (Cloning) ሌጋሲ፤

የፖለቲካ ድርጅቶችን፤የሲቪክ ማህበራትን፤ የሀይማኖት ድርጅቶችን በየፈርጁ እያሰላ በመጠፍጠፍ፤ሁሉንም በመልኩ ቀርጾ ሕዝብን በገዛ አገሩ፤በቤቱ፤በእምነቱና በባህሉ ባእድ ያደረገ የጥፋት መንገድ ከእርሱ ለእነነርሱ ራእይ እውነታው ግን የቅዠት መንገድ ነው።

7. የድምጽ መስረቅ ሌጋሲ፤

መዝግቦ ለማለፍ፤ለማስታወስ ካልሆነ በቀር፤ አይን ያወጣ የሕዝብ ድምጽ በቀትር ጠራራ ጸሀይ ሰለባ ሲካሄድ፤ደግሞ ተደጋግሞ ይባስ ብሉ በ99.6% ነጥብ አሸንፈናል ለማለት የበቃ፤እዚህ ላይ እየተሰረቀ ያለው የሕዝብ ድምጽ ሕዝብ ከነሕይወቱ መሆኑን ነው። ይህ ለእነርሱ የዲሞከራሲ ሌጋሲ ለእኛ ግን የሕዝብ ድምጽ በጠራራ ጸሀይ ሕዝብን ከነነፍሱ መዝረፍ ነው። ይህችም ፊደል በምትነጥብበት ወቅት እንኳ የሕዝም ድምጽ ለማፈን ለመዝረፍ ደባው እየቀጠለ ነው። ወይ ራእይ!

8. የአምባገነንንት ሌጋሲ፤

ከላይ በታያያዘ መልኩ፤ለሓያ አመታት፤አንድ ጊዜ ባለ ሙሉ ባለስልጣን ፕሬዘዳንት፤ በሚቀጥለው ጊዜ ባለ ሙኑ ስልጣን ጠቅናይ ሚኒስቴር፤ ሌለው እነዚህን የስልጣን እርከኖች ሲጨብጥ ባዶ እያደረገ የዘለቀ የሃያ አመት መሰሪ ላጠፋው ጥፋት ለፍርድ ሳይቀርብ ለማለፉ ለእነርሱ የመልካም አስተዳደር ራእይ፤ሌጋሲ ለታሪክ ግን አምባከነን የመሆኑን እውነታ ማሰቀመጥ ያስፍልጋል።

9. የውሸት የሀሰት የትእቢት ሌጋሲ፤

የሆነውን አልሆነም፤ያልሆነውን እንደሆኗል፤የነበረውን አልነበረም ያልነበረውን ነበር እይተባለ አይንን በጨው ያጠበ ነጭ ውሸት፤ፈሩን የሳተ የፐሮፐጋንዳ ዘመቻ ሲደለቅ አመታት ለማለፋቸው ሕዝቡ ከእነርሱ አንደበት የሚወጣው እንደማይጥመውና ጆሮውን እንደነፈጋቸው፤በልቡ ከእነርሱ እንደራቀ፤እንደካዳቸው፤ጊዜንና አጋጣሚን እየጠበቀ አንዳላ ከነርሱው አንደበት “የተቀመጥንብተ ወንበር የዛፍ ላይ እንቅልፍ” ሆነብን እስከሚሉ፤በእውነትም ራእይ ሳይሆን ቅዠት ላይ እንደጣላቸው፤ይህንንም ቅዘት ራእይ ብለው ሊመክሩ እደተነሱ አራሳቸውም አልዘነጉትም። ራእይና ቅዠት አንደ እይደሉም። ሲያንቀላፉ ከሳፉም መውደቅ። የውሸትና የትእቢተኝነት ሌጋሲ።

10. የዘር ማጥፋት ሌጋሲ፤

በአገሪቱ ለብዙ ጊዜ ባራቱም ማእዘናት፤ዘርን መሰረተ ያደረገ የጥፋት ዘመቻ የንጹሀን ደም በከንቱ ለጥቅም ለስልጣን ሲባል ሲፈስና ሲማገድ እንደነበር፤አሁንም በቅርቡ ድሀ ተገን የሌላቸው ዜጎች እየተማገዱ በየጥሻው እየተጣሉ እንዳሉ መዘንጋት አያሰፈልግም። የጥፋት ዘመቻው ለእነርሱ የሚቀጥል ራአይና ሌጋሲ ለዜጎች የሞት ሽረት ጉዳይ ሆኗል። ገበያ ባልወጣሽ የሚሉሽን ባልሰማሽ አሉ።

11. የትውልድ አፍራሽ፤የተበከለ ባህል ሌጋሲ፤

የዜሬው ትውልድ እዳለ ሆኖ የነገው ትውልድ የትምህርት፤የጤና፤የማህመራዊ ፤የእምለት ባጠቃላይ ተስፋው ጨልሞ፤ለአደገኛ ባህሎች፤ልምዶች ታጋልጦ፤በስራአጥነት ተጠምዶ በያለብት ወድቆ የወገን ያለህ፤የአገር ያለህ ሲል እንደሚታይ ሊደበቅ በማይይቻል መልኩ በያደባባዩ ተሰጥቶ ያለ እውለታ ነው። ካሁን በፊት የልነበሩ ያለተለመዱ የጥፋት ልምዶች፤ትውልድ አምካኝ ሂደቶች እንዳሽን እየፈሉ ለመሆናቸው እራሳቸው የማይክዱት፤ባለ ሌጋሲ የሚባለው መሰሪ ላገር ለትውልድ ያተረፈው የጥፋት ቅዠት ነው።

12. የአገርን ጥቅም አሳልፎ የመስጠት ሌጋሲ፤

ሞኝ እነደላኩት ነው ይሏል። እንዳዘዙት፤እንደሰደዱት፤የአገርን ሳይሆን የባእድን ጥቅም በማስቀደም፤ሲፈልግም በሪሞት ኮንትሮል የምንንቀሳቀስ የበናና ሪፑብሊክ አይደለንም እያለ፤ሲያሻው ሳንቲም ከእነርሱ አላገኘንም እያለ ሲሸመጥጥ በያለበት ወጣቱን እያስማገደ፤የወገንን ጉዳት ደብቆ፤ምስኪኑን በረሀ በልቶት እነደቀረ ለእነርሱ የሚቀጥል ሌጋሲ ለወገን ለአገር ግን የክህደት፤የአገርን ጥቅም መሸት ወንጀል ነው። ይህ ነው እንግዲህ እንቀጥል የሚባለው ቅዠት።

13. ኪራይ ሰብሳሚነትና የሞኖፖሊ ሌጋሲ፤

አገሪቱን በየፈርጁ -የፖለቲካ የኢኮኖሚ፤የመከላከያ፤የሰኩሪቲ፤የሲቪክና የእምንተ አውታሮችን ተቆጣጥሮ፤እኒህን በመመርኮስ ሊቃና ወደማይችል የኪራይ ሰብሳም የጥቅም ማጋበሻ ስርአት መስርቶ እንቀጥል፤በዚሁ ይቀጥል የሚለው ከንቱ ምኞት የሗላ ሗላ በእራስ ላይ መፍረድ መሆኑ ማታውቅ ይኖርበታል። ሕዝብ ኪራይ ሰብሳቢ ቢሉት፤ የቤት ኪራይ የመሬት ኪራይ እንዲመስለው በሚያሰለች መልኩ ሲደጋጋም ቢሰማም፤ሚስጥሩ የመንግስት ስልጣንን በመጠወም ሀብ ከማግበስብስ፤ሌላው ስርቶ እንዳይጠቀም በስልጣን ሀይል ማገድ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። ስርአቱ የተመቻቸው ለምዝበራ-ሊቃናም የማይችል የጥፋት ራእይ-ቅዠት ነው።

14. የተዋረደ ኢኮኖሚ ሌጋሲ፤

በዚሁ ሂደት በእድገት ጭራ፤በዝርፊያ ቀዳሜ፤ባሳቻ ቀመር አንደኝነትን የያዘ ስርአት ለመሆኑ ብዙ መዘርዘር አያስፈልግም። ስንቱ ብለቶ ጠጥቶ የድራል፤የስንቱ መሰረታዊ ፍላጎቶች ተሟሉ፤አምራች ዜጋና ምርት የትና የት ናቸው፤ማን ምንነ ይቆጣጠራል፤ማን አደገ ተመነደገ፤ማንስ ድሃ ሆነ ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ እዛው ፈላ እዛው ሞላ፤ እኔን ከደላኝ እድገት ይህች ናት ነው። እነርሱ ሲበሉ ሕዝብ የጠገበ ይመስል፤ብዙሀኑ እንደትላንቱ መከራቸውን እየገፉ ነው።

ታዲያ፤ላገር ለወገን መልካም እንደሰራ፤እያፈነ፤እያደናቆረ በሕይወቱ በቁሙ በደነዘ ካራ አንገቱን ሲገዘግዘው የነበረን፤ይተደራረበ ወንጀለኛ፤መልከም እንዳደረገ፤የሕዝብ ገዳይ፤የአገር ሻጭ፤የታሪክ ነቀዝ፤በተንኮል መበመሰሪነት የተጠመደን መጥፎ ከሀዲ፤መዘዙ ለትውልድ የሚዘልቅን የጥፋት መልእክተኛ፤ባለራእይ፤ባለሌጋሲ አድርጎ በጥፋት መስመሩ እንቀጥል ማልት፤በቀላሉ፤ሰው የለንም፤ እስካሁን እርሱ ነበረ አበቃልን፤የተንኮል ምንጫችን ደረቀጭ መንገዳችንን እንፈልግ፤ ከእንግዲህ የሚሰማን የለም ቢሉ ይቀላል። በሌላ በኩል ደግሞ አስበው መሥራት አለመቻልን በራሰ የመተማመን ጉድለትን ያሳያል፤ዱሮስ።

የለፈውም አለፈ-ግልግል፤አዲሱም ታየ-ለውጥ የለውም። ሁሉም ለትምህርት ይሁን። መንገድ መንገድ መንገድ።

ቋያ ቋያ ጢሱ እየጢያጤሰብሽ፤
ዳሩ መሃል ሆኖ እሳቱ ሳይበላሽ፤
አገሬ ተነሼ ሌላም መንገድ የለሽ።

ቸር ያሰንብትልን!

ecadf.com

ምን ይሆን ሚሰጥሩ ስንጥቅ የሚያረገኝ?

ምን ይሆን ሚሰጥሩ ስንጥቅ የሚያረገኝ?

ምን ይሆን ሚሰጥሩ ስንጥቅ የሚያረገኝ፡

ምን ይሆን ሚሰጥሩ ስንጥቅ የሚያረገኝ?
ቀስተ ደመና ሳይ ልቤን እሚርድብኝ?
ጨርቃችሁ ይውለብለብ ከወደዳችሁት ሲባል የነበረ፤
ለአንባሻ ማስጫ ሆኖ የተወጠረ፡
ደቡብ አፍሪካ ላይ ገነነ ከበረ።
አረንጓዴ ብጫ ቀዩ ሰንደቃችን፡
የበርሊን ታዳሚን ማሸማቀቂያችን።
በባንዳ ተቀዶ ሲደራረት ኖሮ፡
ዳግም ተወለደ ታየኝ ዛሬም አምሮ።
ምስጋና ለናንተ ጫፉን ለያዛችሁ፡
ለመናኛ ባንዳ መርዶ ያረዳችሁ፡
ሊሰቀል ሲዘጋጅ ጣረሞት ጥብቆ፡
ጀግናው ተሰለፈ በባንዲራው ደምቆ፡
ሞቶ ይሁን ተኖ ቅጡ ላልታወቀ የባንዳ አለቃ፡
ለምንስ ማቅ ትልበስ የደቡብ አፍሪቃ?
የማንዴላ አገር የነጻነት ጮራ፡
የጣረሞት ሳይሆን አንበሳው ያጓራ፡
ምንጊዜም ላርማዬ፤ ምን ጊዜም ላገሬ፡
በስደት፤ በስቃይ አይቀዘቅዝ ፍቅሬ፡

ብላችሁ

ተጎናጽፋችሁ ሳይ የክብር መንጦልያ፡
ምንም ብትከሺ አትጠፊም ኢትዮጵያ።
የሚለው ተስፋዬ ዳግም ለመለመ፡
የወያኔ ጫጉላ በቃው አከተመ።

እግዝአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ

እስከ ነጻነት

በደቡብ አፍሪቃ ተሰደው ለምገኙና ንጹሁን የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ አርገው ላገነኑ ላውለበለቡ ጅግኖች መታሰቢያ ትሁንልኝ

ጥር 10 2005

 

ለካስ ሙት ጀግና ነው!

ለካስ ሙት ጀግና ነው!

ለካስ ሙት ጀግና ነው!

እንደ እርጥብ ሸክላ በድምጽ የተናደ፡
አምባገነን ሲባል አካሉ የራደ።
ሁለት አሰርት አመት ከሰው ተሰውሮ የኖረ በጉድጓድ፡
የሰው አይን ካየው ሲመስለው የሚያነድ።
ሞቶ ጀግና ሆነ ወጣ አደባባይ፡
ራሱ እንኳ ባይሆን ሳጥኑ እንዲታይ።
ምንም ባናውቅ እንኳ ሳጥን ያዘለውን።
በሰው ተከበበ ሊያሳይ ጀግንነቱን።
እንኳን ራዕይ እና በውል ቅዠት አያውቅ፡
አሁን ምን ይባላል ደርሶ መጨማለቅ፡
ከኢትዮጵያ አለፎ ሳውዝ አፍሪቃ መዝለቅ።
ህዝብን አናንቆ አንቋሾ ለኖረ መድዴ ስድ አደግ፡
የሙት አጽሙን ለብሶ ማየት ሲያደገድግ።
ምንኛ ያስጠላል ያንገሸግሽማል፡
የሙት አጽም ለመልበስ ሰው እንዴት ያስባል?
እንደ የዋህ ጅግራ ራብ እንደጠናባት፡
ወያኔ ወጥመድ ውስጥ ዘሎ ላለመግባት፡
መጠንቀቅ ይጠቅማል ዘላቂን መመልከት።
የሙት መንፈስ ኪታ ተካድኖ መታየት፡
ጥቁር ማቅ ጥብቆ ያውም ጉድ ያለበት፡
ትንሽ ውሎ ሲያድር የሚያመጣው ጣጣ፡
እንኳን በይቅርታ በደምም አይወጣ፡
ስለዚህ ወገኔ የደቡብ አፍርቃው፡
ቲ ሸርቱን ጣልና በእግርህ እርገጠው፡
ጨልጦ ለጠጣ የነ ሽብሬን ደም፤ ቆራርጦ ለበላ የነቢዩን ስጋ፡
መሬት ትጸየፈው ትሁን አጋም ቀጋ፡
እያለ ሲራገም ወገን ከዳር አዳር፡
አንተስ ምን ትላለህ ተጠየቅ ተናገር?
አንቺስ እንዴት አሰብሽ?
ጥቁር ትለብሻለሽ ለወያኔ ሰግደሽ
ወይስ?
ሞት ለመለስ ብለሽ፡ የወገኖችሽን፣ እንባ ታብሻለሽ፡
መልሱን ላንተ ትቼ፡ መልሱን ላንቺ ትቼ ልሰናበታችሁ፡
ግን ልብ በሉ፤ ከህዝብ አትጋጩ ወያኔ አይጠቅማችሁ፡
ሆድ አድሮ እንግዳ ነው ሞልቶ አይሞላላችሁ፡
ለሁሌ ደስታ ህሊና ይግዛችሁ።
ደቡብ አፍሪቃ የመለስ ፎቶ የተለጠፈበትን ቲ ሽርት ለመልበስ ለተመለመሉ መልእክቴ ይድረሳችሁ

እግዝአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ

እስከ ነጻነት

 

 ecadf.com

የ“ዝም በል ዳያስፖራ” – አዋጅ፦ ከቤተ መንግሥት እስከ ቤተ እምነት

ኤፍሬም እሸቴ/Adebabay

በዚህ ሰሞን መቼም ከእግር ኳስ ውጪ ማውራት በሕማማት ስለ ቁርጥና ጥብስ እንደማውራት ሳይቆጠር አይቀርም። እኔም ብሆን ስለ እግር ኳሱ ማውራቱን መች ጠልቼው። በርግጥ ይኼ ሁሉ ወፈ ሰማይ የስፖርት ተንታኝ በየኤፍ.ኤሙ ሲተችበት በሚውለው የተጫዋቾቻችን ብቃት፣ ጥራት፣ የኳስ ጥበብ፣ የሽልማት ዓይነት፤ የተጋጣሚዎቻችን ሁኔታ፣ የተጫዋቾቻቸው ዝና፣ ማን ከየትና ከየትኛው ክለብ እንደመጣ፣ አሰላለፋቸው እና ከኢትዮጵያ ጋር ሲገጥሙ ሊኖራቸው ስለሚችለው አያያዝ ለመተንተን ሙያውም መረጃውም የለኝም። (“ችሎታ የለኝም” አለማለቴ ይሰመርበት። ማን ይሞታል። መቸም “አልችልም” ማለት ጎጂ ባህል ሆኗል።) ቢያንስ የእንጀራ አገሮቻችን አሜሪካ እና ስዊዲን ስላፈሯቸው እና ለእናት አገራችን ኢትዮጵያ ስላበረከቷቸው ተጫዋቾቻችን መወያየት ይቻላል።ምን ይሆን ሚሰጥሩ ስንጥቅ የሚያረገኝ፡

ኢትዮጵያውያን እንደ ጨው በመላው ዓለም ተበትነዋል። በብዙ ቦታዎች አንድ ትውልድ አልፎ ሁለተኛ ትውልድ ላይ ደርሷል። በቅርብ ከሚገኙት ኬንያና ሱዳን እስከ አረብ አገሮች፣ ከምዕራብ አውሮፓና ስካንዲኔቪያን አገሮች እስከ አሜሪካና አውስትራሊያ ድረስ ብዙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ። ከእነርሱ መካከል የአሜሪካ ሜኔሶታው ፉአድ ኢብራሒም እና የስዊዲኑ ዩሱፍ ሳላህ ተገኝተዋል። ፉአድ ኢትዮጵያ ተወልዶ አሜሪካ ያደገ፤ ዩሱፍ ደግሞ እዛው ስዊዲን ተወልዶ እዛው ያደገ እግር ኳስ ተጫዋች ነው። የብዙ ኢትዮጵያውያን የኋላ ማንነት ማሳይ ሊሆኑ የሚችሉ ልጆች ናቸው። አድገውና ለቁም ነገር ደርሰው አገራቸውን ለመወከል መብቃታቸው ደስ ይላል። “አለ ገና፣ ገና፣ አለ ገና” እንላለን።

ጣዕመ-ኢትዮጵያ፣ ባህለ-ኢትዮጵያ በቀዘቀዘባቸው ባህሎች መካከል አድገው በመጨረሻ አገራቸውን ለመወከል መቻላቸው ትልቅ ነገር ነው። ስለ ፉአድ ያነበብኩት አንድ ጽሑፍ ይህ ወጣት ለአሜሪካ እግር ኳስ ቡድን (ከ17 ዓመት በታች እንዲሁም ከ21 ዓመት ላሉት) ቢጫወትም የማታ ማታ ግን አገሩን ለመወከልና የአገሩን ማሊያ ለመልበስ መወሰኑን ያትታል። ስዊዲን እነ ኢብራሒሞቪችን (በአባቱ ቦስንያዊ) እና ታዋቂው ሔንሪክ ላርሰንን (አባቱ ከኬፕቬርዴ ናቸው) የመሳሰሉ ተጫዋቾችን በማሰለፏ እናውቃታለን። ዩሱፍም ተመሳሳይ በሆነ መልክ ተመሳሳይ ዕድል ሊያገኝ እንደሚችል እገምታለኹ። ነገር ግን ያንን ትቶ የአገሩን መለያ ለብሷል።

ዳያስጶራው ለረዥም ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ወደ አገሩ በመላክ አገሩን በቀጥታም በተዘዋዋሪም ሲደግፍ ቆይቷል። በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከዳያስጶራው የሚገኘው ገቢ አገሪቱ ከወጪ ንግድ ከምታገኘው በእጅጉ እንደሚበልጥ የዓለም ባንክ ጥናቶች በተደጋጋሚ አሳይተውናል። ከዚህ የቀጥታ ገንዘብ ርዳታ ባሻገር ትውልደ-ኢትዮጵያዊው በአገሪቱ አጠቃላይ ሕይወት ላይ በጎ ሱታፌ ማሳየቱ አገሩን ለሚወድ ወገን ሁሉ ትልቅ ተስፋ ነው። ዩሱፍና ፉአድ ለዚህ መልካም አብነቶች ይሆናሉ።

ዩሱፍና ፉአድ ወደ አገራቸው ሲመለሱ በዚያው መጠን ብዙ ኢትዮጵያውያን ወደ ዳያስጶራነት ጎራ እየተቀላቀሉ ነው። በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በዋሺንግተን ዲሲ የተደረገ በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ሐኪሞች ማኅበር ስብሰባ ተገልጿል እንደተባለው በአሁን ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዶክተሮች ይልቅ በውጪ የሚገኙት ቁጥር ይበልጣል። አዝማሚያውን ስንመለከተው ይኸው የዕውቀትና የአዕምሮ ስደት እንደሚቀጥል እርግጥ ነው። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ኢኮኖሚያዊ ዋስትና ማጣት እና ፖለቲካዊ ነጻነት አለመኖር ነው። ከኢኮኖሚው በበለጠ ፖለቲካዊ ጫናው ለብዙው ወገናችን መሰደድ ምክንያት ነው የሚለው የብዙዎች እምነት ነው። በፖለቲካዊ ምክንያቶች የተሰደዱት ደግሞ በየወጡበት አገር ባላቸው ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን መንግሥት ዘወትር መክሰስ ቀጥለዋል። በቅርቡም ይቆማል ተብሎ አይጠበቅም። ይህም ፉአድንና ዩሱፍን የመሳሰሉ ትልውደ ኢትዮጵያውያን በየሙያቸው ትውልድ አገራቸውን እንዳያገለግሉ እንቅፋት ይሆናል። በአገሪቱ ያለው የሰብዓዊ መብት ገፈፋ ሲሻሻል ዳያስጶራውም ተጠቃሚ ይሆናል። ዳያስጶራውን በጥቅማጥቅም ማባበል መጠነኛ ደጋፊ ያስገኛል፤ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት መጠበቅና ሕገ መንግሥቱን ማክበር ግን ሙሉ ድጋፍ ያስገኛል።

ዳያስጶራው በየሚኖርበት አገር የሚተነፍሰው ፖለቲካዊ፣ ኅሊናዊ፣ አካላዊ እና ሰብዓዊ ነጻነት ይኸው ነጻነት በአገሩ እንዲኖር በጎ ምኞት ይቀሰቅስበታል። ስለዚህ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ በአገሩ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ይኮንናል፤ ተጽዕኖ ለመፍጠርም የማይወጣው ዳገት የማይወርደው ቁልቁለት የለም። ይህም የተለያየ አመለካከት መፍጠሩ አይቀርም። ዳጳስጶራው “አክራሪ ነው” ከሚለው ጀምሮ “የአገሩን ነባራዊ ሁኔታ የማያውቅ” እንዲሁም “50 ዶላር ልኮ አገር ውስጥ ያለው ወጣት እንዲማገድ ይፈልጋል” ወዘተ ተብሎ ይቀርባል።

ሐሳቡ ቀደም ብሎ በመንግሥት ብቻ ተደጋግሞ ሲገለጽ የቆየ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ተርታ ዜጎችም በማኅበራዊ ድረ ገጾቻቸው ሲያስተጋቡት ይስተዋላል። በአጭር አባባል ለማቅረብ “ዳያስጶራ ዝም በል” ወይም “ዝም እንዲል አድርጉት” የሚል አዋጅ የተነገረ ይመስላል።

በመጀመሪያ ደረጃ አንድን ዜጋ ከአገሩ ርቆ በመኖሩ ስለ አገሩ ያለውን ሐሳብ፣ በመንግሥቱ ላይ የሚኖረውን ቅዋሜ እና ለችግሮች የሚኖረውን መፍትሔ ከማቅረብ ሊከለክለው የሚችል ሕግ የለም። ስለ አገርህ ለመናገር በአገርህ መሬት መኖር አለብህ የሚል “የቀበሌ ትእዛዝ” የመሰለ ሐሳብ ውኃ አያነሣም። ነቢዩ ዳዊት ስለ ኢየሩሳሌም ሲናገር “ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ” እንዳለው “እመሰ ረሳዕኩኪ ኢትዮጵያ  ለትርስዐኒ  የማንየ፣ ኢትዮጵያ ሆይ ብረሳኝ ቀኜ ትርሳኝ” የሚሉ ኢትዮጵያውያንን ‘እኮ ምን አግብቷችሁ’ ማለት ከስድብ ይልቅ ያማል።

ዛሬ ባንኖርባት ተወልደንባት አድገንባታል፤ ዘር ማንዘሮቻችን ኖረው አልፈውባታል። ክቡር አጥንታቸው ረግፎባታል። በየወቅቱ በሚመጣና በሚሄድ ሥልጣን የአንድ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱ አይገመገምም። ኢትዮጵያዊነትን ማንም ባለሥልጣን አልሰጠንም፣ ማንምም አይነፍገንም። ከደርቡሽና ቱርክ፣ ጣሊያንና ግብጽ፣ ከሌሎችም ድንበር ገፊዎች ሲታገሉ በወደቁ ወገኖቻችን የቆመ ዜግነት እንጂ እንጀራ ፍለጋ፣ ነጻነት ፍለጋ እንደምንኖርባቸው አገሮች በወረቀት ብቻ የሚረጋገጥ አይደለም። ኢትዮጵያዊ ዜግነት ከወረቀት እና ከፖለቲካ ወገንተኝነት እንዲሁም ከየብሔረሰባዊ ማንነታችን በላይ ነው።

በሌላም በኩል ካየነው ስለ ሰብዓዊ መብት ለመናገር የግድ የዚያ አገር ዜጋ መሆን፣ በዚያ አገር መኖርም አይጠይቅም። ሰብዓዊ መብቱ እንዲጠበቅለት የሚፈልግ ማንም ሰው የሌላው ሰው መብት ሲጣስ አይደሰትም። ሌላው ሁሉ ታሪካዊ ሐተታ እንኳን ቢቀር በቅርቡ ዘመን የኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ከኛ ሚሊሻ ጋር አብረው የተዋደቁልንን ኩባውያንን  መስዋዕትነት እንደምናከብረው፣ ዕድሜ ዘመናቸውን በሴቶች (ፊስቱላ) ሕክምና ረገድ አገራችንን የጠቀሙትን ሐኪሞች እንደምናመሰግነው ሁሉ ለዜጎቻችን ሰብዓዊ መብት የሚከራከሩትንም በዚሁ መነጽር ልንመለከታቸው ይገባል።

በተጨማሪም የመንግሥትን አሠራር ማሔስ አገርን መተቸት አይደለም። መንግሥት የአገር መሪ እንጂ አገር አይደለም። ፓርቲና መንግሥትነት ከዘር ጋር በመቆራኘታቸው ፓርቲውን መተቸት የመጣበትን ዘር እንደመውቀስ ተደርጎ መቆጠሩም ትልቅ ስሕተት ነው። ፓርቲዎች በዓላማቸውና በአሠራራቸው መነቀስና መተቸት ግዴታቸው ስለሆነና በዘር ላይ የተመሠረተ የፓርቲ አወቃቀር እስካለ ድረስ ከፓርቲው ጀርባ ያለው ዘር ወቀሳው ለርሱ የተወረወረ አለመሆኑን ለመረዳት ብዙ ጥበብ አያስፈልገውም።

እንኳን የኢትዮጵያ መንግሥት በዲሞክራሲያዊነታቸው ወደር የማይገኝላቸው አገሮች የየጊዜው መንግሥታት ሳይቀሩ ከትችት አያመልጡም። ትችት መንግሥታቱን ከዓምባገነንነት የሚያተርፋቸው ፍቱን መድኃኒት ነው። ተቃዋሚዎችን፣ ፕሬሶችን፣ ጥቃቅን ስብስቦችን ሁሉ በመዋጥና በዓይነ ቁራኛ በመመልከት፣ ትችትን ሳይሆን ተቺውን በማፈን ጥሩ መንግሥት መሆን አይቻልም። “ልማት ላይ ነን አትንኩን” የሚል ፈሊጥ ወንዝ አያሻግርም። ጥያቄው ግድቡና ሕንጻው ላይ አይደለም። የዜጎችን ሰብዓዊ ሕንጻ እያፈረሱ የድንጋይ ሕንጻ እንሠራለን ማለት አይቻልም። ከግዑዝ ሕንጻ ሰብዓዊ ዜጋ ይቀድማል፤ከግድብ ግንባታም መብት ይቀድማል።

በውጪ የሚገኘው ዜጋ የአገሩን ሁኔታ በትኩረት ለመከታተል ቴክኖሎጂው ትልቅ ዕድል ይሰጠዋል። አራት ኪሎ የተፈጠረው አቃቂ፣ አንዱ ክፍለ ሀገር የተሠራው ሌላው ሳይረዳው ሳይሰማ፤ እረኛና አዝማሪ እንኳን ለዘፈኑና እንጉርጉሮው በራሱ ላይ ግላዊ-ሴንሰርሺፕ በጣለበት ዘመን፣ ከአንድ አፍ በሚወጣ ተመሳሳይ፣ ተደጋጋሚና ቁጥጥር የተደረገበት ወሬ አገር በሚተዳደርበት ጊዜ፣ አለመስማትን እና አለማወቅን (መንግሥታዊ የመረጃ ግርዶሽን) መታገል ሲገባ የሰማውንና ያወቀውን “እኮ ማን ስማ አለህ” ማለት አያዋጣም። ይህንን የሚለው አካል ነገሩ እንዳይሰማበት የፈለገው እንጂ ተጎጂው አለመሆኑም በቅጡ ይታወቃል።

ዳያስጶራውን አምርሮ የመጥላት እና በጅምላ ክፉ ስም የመስጠት ተደጋጋሚ ሙከራ ፍሬ ማፍራቱን ለማወቅ ተርታ ግለሰቦች እና ቤተ እምነቶች ሳይቀር ማንጸባረቅ የጀመሩትን ተመሳሳይ አመለካከት መመልከት ይገባል። የግለሰቦቹን እንኳን ለጊዜው ብናቆየው የአንዳንድ ቤተ እምነት አስተዳደሮችና መሪዎች ከውጪ የሚመጣላቸውን የአማኛቸውን ሐሳብ፣ ልክ እንደ መንግሥት፣ “አፍራሽ፣ የተቃዋሚ ፖለቲከኞች ጥያቄ” አድርገው ሲመለከቱት ማየት እየተለመደ መጥቷል። ‘አጋጣሚ ነው ወይስ የተላለፈ አዋጅ አለ?’ የሚያሰኝ ነው። የቤተ እምነት መሪዎች ሰማያዊውን መንግሥት መጠበቅ ትተው ምድራዊውን መንግሥት ለመጠበቅ ደፋ ቀና ሲሉ እነርሱን የሚከተላቸው ምእመን እንደሚመለከታቸው እንኳን ይዘነጉታል። እነርሱም ከምድራዊው ባለ ጉልበት ጋር ተደርበው “ውጪ ያላችሁት ዝም በሉልን፣ እንደፈቀድን እንሁን” ሲሉ አዋጃቸውንም በደህና ጊዜ የሚናገሩትንም ሰማያዊ ቃል የሚሰማቸው ጆሮ ያጣሉ። በርግጠኝነት ግን ማንም ዝም አይልም።

መልካም ዕድል ለብሔራዊ ቡድናችን!!!!

 ይቆየን – ያቆየን

ecadf.com

መነቀል ያለበት ስር የሰደደ የወያኔ ዘረኝነት

የግንቦት 7 ንቅናቄ

ዘረኛዉ የወያኔ ስርአት የኢትዮጵያን ህዝብ ለጥቂት አመታት ኢትዮጵያዊያንን ባሰረና በገደለ ቁጥር ገንዘብ የሚሰጡትን አለም አቀፍ ድርጅቶችና አርዳታ ሰጪ አገሮች ደግሞ 21 አመት ሙሉ ካታለለበት መንገድ አንዱ የፌዴራል ስርአት መስርቼ ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር አደረኳት የሚለዉ ባዶ አባባሉ ነዉ። ይህንን ተጋልጦ እርቃኑን የቀረ አባባል የኢትዮጵያ ህዝብ ተገንዝቦ ወያኔን መታገል ከጀመረ ቆይቷል፤ ዋና ዋናዎቹ እርዳታ ለጋሾችም ቢሆኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ ደህንነት ግድ የሌለዉ ወያኔ ወጣቶቻችንን እየገበረ ጥቅማቸዉን ስለሚያስከብርላቸዉ ነዉ እንጂ ወያኔ እንኳን እየደገፉ እርዳታ የሚሰጡት በአንድ ተርታም አብረዉ ለመቀመጥ የማይመች የእኩዮች ስብስብ እንደሆነ ካወቁ ቆይቷል።

ህወሀት በፌዴራል ስርአቱ ዉስጥ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ በሚጠራዉ ፓርላማ ዉስጥ ያለዉ መቀመጫ 8 ብቻ ነዉ። እዚህ ፓርላማ ዉስጥ የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ የሚለዉ ህወሀት ነዉ፤ ትግራይ ደግሞ ኢትዮጵያ ዉስጥ አንድ ክልል ናት። የተቀሩት 8 ክልሎች በዚህ የእኩልነት ምልክት በሆነዉ ፓርላማ ዉስጥ ያላቸዉ የመቀመጫ ብዛት 569 ነዉ። ሆኖም በወያኔ መንደር የፖለቲካ ስልጣን ምንጭ ህዝብ ሳይሆን ጠመንጃ ነዉና ወያኔ ፓርላማዉ  ዉስጥ 8 ወንበር ብቻ ይዞ 569 ወንበር ያላቸዉን የኦሮሚያን፤ የአማራን፤ የደቡብ ክልልንና የተቀሩትን አምስት ክልሎች እንደ መኪና ይነዳቸዋል። የየክልሉን መሪ ይሾማል፤ ይሽራል ወይም የማይስማማዉን የክልል ባለስልጣን ያስራል። ፓርላማዉ ዉስጥ አንድ መቶ ሰባ ስምንት፤ አንድ መቶ ሰላሳ ስምንትና አንድ መቶ ሀያ ሦስት መቀመጫ ያላቸዉ የኦሮሚያ፤ የአማራና የደቡብ ክልል ፓርቲዎች በራሳቸዉ ጉልበትም ሆነ ህልዉና ስለሌላቸዉ አንዱ ከሌላዉ የበለጠ ስልጣን ወይም ሹመት ለማግኘት አንጋጥጠዉ ወደ ላይ የሚመለከቱት ህወሀትን ነዉ።

ለመሆኑ ወያኔ የፌዴራል ስርዐት መስርቼ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት አረጋገጥኩ ሲል ምን ማለቱ ነዉ? እኩልነቱ የፖለቲካ ነዉ  የኤኮኖሚ? ወይስ በየአመቱ ህዳር ወር ላይ የፌዴራልዝም ቀን ሲከበር እንደምናየዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት የተረጋገጠዉ በዘፈን ብቻ ነዉ? የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስርዐት ከላይና ከታች የሚቆጣጠረዉና ይህንኑ የፖለቲካ ስርአት የሚደግፍ የኤኮኖሚ መዋቅር ዘርግቶ የአገራችንን ኃብት የሚቦጠብጠዉ ህወሀት ብቻ ነዉና የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ተረጋገጠ የሚባለዉ አባባል ከተራ የቃላት ድርደራ ዉጭ ሌላ ምንም ትርጉም የለዉም።

አፄ ቴዎድሮስን እንደ ልጅነት ሞዴሉ የሚመለከተዉ ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም የመጀመሪያዉን የኢትዮጰያ ዘመናዊ ወታደራዊ እንጂኔሪንግ ተቋም ሲመሰርት ስሙን “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ ነበር የሰየመዉ። ስያሜዉ የአፄ ቴዎድሮስ ስራና ስም ህያዉ ሆኖ እንዲኖር ለማድረግ የተደረገ ሙከራ እንደነበር ግልጽ ነዉ። የኢትዮጵያን የቀድሞ መሪዎች በጅምላ የሚዘልፈዉ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ከአንዲት የአገር ዉስጥ ጋዜጠኛ ጋር ባደረገዉ ቃለ ምልልስ አፄ ቴዎድሮስ ጋፋት ላይ ያሰሩትን መድፍና መንግስቱ ኃ/ማሪያም “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ  የሰየመዉን ወታራዊ ተቋም አስመልክቶ ሁለቱንም መሪዎች ሲያንቋሽሽ ተደምጧል። የሚገርመዉ ዛሬ ወያኔ የብረታብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺን ብሎ የሚጠራዉ ግዙፍ የሲቪልና ወታደራዊ እንዱስትሪ ተቋምና በዚህ ተቋም ዉስጥ የሚገኙ ዋና ዋና ፋብሪካዎች ደርግ  “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ የጀመራቸዉ የከባድ እንዱስትሪ ጅምሮች ናቸዉ። በ1970ዎቹ አጋማሽ ላይ “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ስራዉን ሲጀምር የፋብሪካዉ ሀላፊዎች፤ እንጂኔሮች፤ የመምሪያ ሀላፊዎችና ቴክኒሺያኖች የስራ ዕድል የሚያኙት የትምህርት ደረጃቸዉ፤ ችሎታቸዉና የሰራ ልምዳቸዉ ብቻ እየታየ ነበር፤ ወይም ትግርኛ ስለተናገረ ስራ የሚከለከል አማርኛ፤ ኦሮምኛ ወይም ሌላ ቋንቋ ስለተናገረ አድሎ የሚደረግለት ዜጋ አልነበረም። ዛሬ ወያኔ ከደርግ ስርአት ተረክቦ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ብሎ በሰየመዉ እንዱስትሪ ዉስጥ አብዛኛዉን የሀላፊነት ቦታ የያዙ ሰዎች ለቦታዉ የበቁት በስራ ልምዳቸዉና ችሎታቸዉ ሳይሆን የተወለዱበት ዘርና የሚናገሩት ቋንቋ እየታየ ነዉ። ወታራዊዉ አምባገነን ደርግም ሆነ  ወያኔ ይህንን እንዱስትሪ የወደፊቱ የኢትዮጵያ ከባድ እንዱስትሪ ዘርፍ መሰረት ይሆናል የሚል ራዕይ ነበራቸዉ። ልዩነታቸዉ የእንዱስትሪዉ አስፈላጊነት ላይ ሳይሆን እንዱስትሪዉን ማን ይቆጣጠረዋል የሚለዉ ጥያቄ ላይ ነዉ። ደርግ በሱ መሪነት ለማንም ችሎታ ላለዉ ኢትዮጵያዊ የእንዱስትሪዉን በር የከፈተ ሲሆን ወያኔ ግን እንዱስትሪዉ እንዳለ በአንድ ዘር ቁጥጥር ስር እንዲገባ አድርጓል።  ደርግም ወያኔም አምባገነኖች ስለሆኑ አንዱስትሪዉን ከህዝብ ቁጥጥር ዉጭ አድርገዉታል፤ ወያኔ ግን ከአምባገነንም የጎሳ አምባገነን ስለሆነ ይህንን ትልቅ እንዱስትሪ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች ቁጥጥር ስር አድርጎታል።

ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ባለለፉት ሦስት አመታት ይህንን ወያኔ ገነባሁ የሚለዉን የፌዴራል ስርአትና በስርአቱ ዉስጥ የተለያዪ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የሚጫወቱትን ሚና በመረጃ አስደግፎ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ አቅርቧል። የዛሬ ሁለት አመት ግንቦት ሰባት በኢትዮጵያ መላከያ ሰራዊት ዉስጥ የተዘረጋዉን የወያኔ የዘረኝነት መረብ ከሰሞኑ ደግሞ የኢትዮቴሌኮምን የዘረኝነት አደረጃጀት በመረጃ በማስደገፍ ለህዝብ ማቅረቡ ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺንን የዘረኝነት አደረጃጀትና በዚህ አደረጃጀት ዉስጥ ማን ምን እንደሆነ ያጣናዉን የጥናት ዉጤት በመረጃ አስደግፎ ያቀርባል።  ግንቦት ሰባት ሃያ አራት ሰአት ሙሉ የሚከታተሉትን የወያኔ የደህንነት ሰራተኞች ከበባ ጥሶ የወያኔን ዘረኝነት የሚያጋልጡ መረጃዎችን ከራሱ ከወያኔ ጓዳ እየጎተተ አዉጥቶ ለህዝብ የሚያቀርበዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔን ዘረኝነት አያውቀዉም በሚል አስተሳሰብ አይደለም። ግንቦት ሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ የፈጠረዉ ከፍተኛ የመረጃ ጉድለት አለ ብሎ ያምናል፤ስለሆነም ህዝቡ የወያኔን ዘረኝነት ቢረዳም መጠኑን፤ስፋቱንና ጥልቀቱን በሚገባ ላያዉቅ ይችላል ብለን እናምናለን። በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በየቀኑ ደሙን እንደ መዥገር የሚመጠዉን ወያኔን የመሰለ የጀርባ ላይ አጥንት ተሸክሞ መኖር የለበትም ብለን ስለምናምን ህዝብን ለትግል ከምናዘጋጅበትና ከምናነሳሳባቸዉ መንዶች ዉስጥ አንዱ እንደዚህ ህዝብ በገዛ አገሩ “እኩል አደረግንህ” ብለዉ በሚነግሩት ከሀዲዎች ቅኝ አገዛዝ እየተገዛ መሆኑን በማሳወቅ ነዉ።

ባለፈዉ ሳምንት የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዋና ዳይረክተር ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ ፓርላማ ዉስጥ ተገኝቶ የኮርፓሬሺኑን የሁለት አመት የስራ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ኮርፓሬሺኑ የግል ባለኃብቶችን አያሳትፍም እንዳዉም እያቀጨጫቸዉ ነዉ፤ ለሙስና የተጋለጠ ነዉ፤ ደግሞም አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኛ የመከላከያ ሰራዊት አባል ነዉና ይህ አሰራር  ሠራተኞችን ለማስተዳደር አስቸጋሪ አይሆንም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዉለት ነበር። የግሉን ዘርፍ መቅጨጭ በተመለከተ ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉንም ቢሆን “የወያኔ ዘርፍ” እንጂ የግል ዘርፍ የሚባል ነገር የለምና ጥያቄዉ መቅረብም አልነበረበትም።  ሙስናም ቢሆን የወያኔ ስርዐት ዋናዉ መገለጫ ባህሪይ ስለሆነ ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ ሙስና  “ሙስናን እናጠፋለን” ስለተባለ ብቻ የሚጠፋ ነገር አይደለም። ግንቦት ሰባትን እጅግ በጣም ያሳዘነዉና ያስገረመዉ ነገር ያንን ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ የሚናገርለትን ፓርላማ ያስጨነቀዉ (ተጨንቆ ከሆነ) የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር መዉደቁ ሳይሆን አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኞች የመከላከያ ሰራዊት አባላት መሆናቸዉ ነዉ። በእርግጥ የአንድ ትልቅ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች በአብዛኛዉ  የጦር ሠራዊት አባላት ሲሆኑ የአሰራርና የአስተዳደር ችግር መፈጠሩ አይቀርም፤ ሆኖም የሠራዊቱ ታማኝነት  ለህዝብ ታዛዥነቱ ደግሞ ለህገ መንግሰስቱ ብቻ ቢሆን ኖሮ ይህ ችግር በቀላሉ የሚወገድ ችግር ይሆን ነበር።

ginbot 7 exposing woyane 1

የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአምሰት አመቱ የእድገትና የትራንስፎርሜሺን ፕላን ዉስጥ የሚጫወተዉን ቁልፍ ሚና ፓርላማዉ በሚገባ የሚገነዘበዉ ይመስለናል፤ ታዲያ ይህ በአገር እድገት ዉስጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወተዉ ኮርፖሬሺን ሙሉ በሙሉ በአንድ ብሔር ቁጥጥር ስር ሲወድቅ ምነዉ የብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት የሆነዉ ፓርላማ አፉን ዘግቶ ተመለከተ? ፓርላማዉን ይበልጥ የሚገድደዉ የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር ሆኖ ሌሎቹ ብሔረሰቦች ተመልካች ሲሆኑ ነዉ ወይስ የአንድ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች  በአብዛኛዉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲሆኑ ነዉ? ለመሆኑ የወያኔ ዘረኝነት በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዉስጥ ምን ያህል ዘልቆ ገብቷል? የኦሮሞ፤ የአማራ፤ የሶማሌ፤ የሲዳማና ሌሎቹም ብሔር ብሔረሰቦች በዚህ ለአገር እድገት ቁልፍ በሆነ ኮርፖሬሺን ዉስጥ የሚጫወትቱት ሚና ምን ይመስላል?

ginbot 7 exposing woyane 2

የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በአስራ አንድ መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች የተዋቀረ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎቸን ያስተዳድራል፤ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀቀበት ቀን ድረስ ቁጥራቸዉ በዉል ተለይቶ ባይታወቅም አስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎችም እያንዳንዳቸዉ በስራቸዉ ብዙ ፋብሪካዎችንና የማምረቻ ተቋሞችን ያቀፉ ናቸዉ። የኮርፖሬሺኑን  አስራ አንድ ትላልቅ መምሪያዎችና አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱሰትሪዎች በዋና ሀላፊነት፤ በዳይረክተርነተና በምክትል ዳይረክትርነት የሚመሩ 29 የከፍተኛ አመራር አባላት አሉ። ከእነዚህ 29 ከፍተኛ አመራር አባላት ዉስጥ 69 በመቶዉ ወይም ሃያዉ ህወሀት ሆን ብሎ ያስቀመጣቸዉ ትግርኛ ተናጋሪ የሆኑ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸዉ።በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ያላቸዉ ቦታ 31 በመቶ ወይም ከእያንዳንዳቸዉ በቅደም ተከተል ሦስትና ስድስት ሰዎች ብቻ ሲሆን ከተቀሩት አምስት ክልሎች በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የተመደበ አንድም  ሰዉ የለም። ኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ እንዱስትሪ ለመገንባት በሚደረገዉ ጥረት ዉስጥ ከፍተኛዉን ሚና ይጫወታል የሚባለዉ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በሲቪልና ወታራዊ መምሪያዎች ተከፋፍሎ የተዳራጀ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎች ይገኛሉ። እነዚህን እንዱስትሪዎች በማስተዳደሩ በኩል የብሔር ብሔረሰቦችን ድርሻ ወይም ኮታ ስንመለከት  ከአስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎች ዘጠኙን የሚያስተዳድሩት የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። በኮርፖሬሺኑ ዉስጥ ከፍተኛ ስልጣን ከተሰጣቸዉ የትግራይ ተወላጆች ዉስጥ እነ ብረጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ  የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን ዋና ዳይረክተር ፤ ኮ/ል ተከስተ ኃ/ማሪያም  በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮዳክሺን ግንባታ ሀላፊ ፤ ኮ/ል ፀጋሉ ኪሮስ በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ወታደራዊ ምርቶች ሀላፊ ፤ ኮ/ል ሙሉ ወ/ሰንበት በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮጀክቶች አስተደዳደር ሀላፊ፤ሻምበል ካህሳይ ክሽን የምርመራና ልማት ዳይረክተርና  ሻምበል ገ/ስላሴ ገ/ጊዮርጊስ የአቅም ግንባታና ስልጠና ማዕከል ዳይረክተርን የመሳሰሉ የህወሀት ታጋይ መኮንኖች ይገኙበታል።

ginbot 7 exposing woyane 3

ከትግራይ ዉጭ ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔሰቦች በብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን እንዱስትሪዎች ዉስጥ ከፍተኛ የሀላፊነት ደረጃ ባለዉ የአመራር ቦታ ላይ የመቀመጥ ዕድል ያገኙ ኢትዮጵያዉያን ቁጥር አራት ብቻ ነዉ። ይህ ጥናት የተጠናዉ ከ2004 እስከ 2005 ዓም ባለዉ የአንድ አመት ግዜ ዉስጥ ነዉ። በ2004 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ 90 ሚሊዮን አንደሚሆን የተገመተ ሲሆን ከዚህ ቁጥር ዉስጥ በትግራይ ክልል  5.4 ሚሊዮን ህዝብ በተቀሩት ስምንት ክልሎች ደጎሞ 84.6 ሚሊዮን ሀዝብ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል። ይህ ጥናት በዋናነት የሚያመለክተዉ በዋና ዋና የሀላፊነት ቦታ የተቀመጡትን ግለሰቦችና ግለሰቦቹ የመጡበትን ብሔር ስለሆነ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺንን የሰዉ ኃይል ምደባና የደረጃ እድገትን ጠለቅ ብለን ስንመለከት አብዛኛዎቹ እንጂኔሮችና ቴክኒሻኖች የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ፤ የደረጃ እድገትን በተመለከተም ከሌሎች ሰራተኞች ጋር ሲነፃፃር በፍጥነት የደረጃ እድገት የሚያገኙት እነዚሁ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። ይህ ደግሞ በአጋጣሚ የሆነ ነገር ሳይሆን ወያኔ በረሀ ዉስጥ እያለ አቅዶት ባለፉት ሃያ አመታት በስራ ላይ ያዋለዉ የረጂም ግዜ እቅድና ዝግጅት ዉጤት ነዉ።  ለምሳሌ ወያኔ ትግራይ ዉስጥ ኤም አይ ቲ  ወይም የመቀሌ ቴክኖሎጂ እንስቲቲዩት ብሎ የሚጠራዉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ተቀብሎ የሚያስተምረዉ የትግራይ ተወላጆችን ሲሆን ከዚህ ተቋም የሚመረቁ እንጂኔሮችና ተክኒሺያኖች ናቸዉ በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን የሚሊታሪ ክንፍና በኢትዮቴሌኮም የስለላ ተቋሞች ዉስጥ ተመድበዉ ከፍተኛ የስለላ ስራ የሚሰሩት።

ginbot 7 movement exposing woyane 4

ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝና አገር ዉስጥና በዉጭ አገር የሚገኙ ቡችሎቹ የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ድርጅቶች በተለይ በዳያስፖራ ዉስጥ የሚገኘዉን ለእናት አገሩ ተቆርቋሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጅምላ “የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች” እያሉ ለአመታት ሲዘልፉን ኖረዋል። የፖለተካ ትግላችን አላማና ግብ ከጥላቻ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለዉ ቢሆንም – ለመሆኑ ይህንን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተና አንዱን አለቃ ሌላዉን ተላላኪ፤ አንዱን የሚሾም ሌላዉን የሚሽር፤ አንዱን አብልቶ የሚያጠግብ ሌላዉን የበይ ተመልካች የሚያደርግ፤አንዱን የአገር መሪነት ቦታ ተረካቢ ሌላዉን ኮብልስቶን ድንጋይ ጠራቢ የሚያደርግ ስርዐት የሚወድ ማን አለ? ይህንን በንጹህ ዜጎች ደም እጁ የቆሸሰና ያደፈ ዘረኛ ስርአት ዉደዱ የሚለንስ ማነዉ? በምድርም በሰማይም የከሰሩ እነ ሚሚ ስብሀቱን የመሳሰሉ የፖለቲካ ሴሰኞች ሊነግሩን እንደሚፈልጉት ትግላችን የትግራይ ወንድሞቻችንንና እቶቻችንን በመጥላት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን የትግላችን ብቸኛ አላማ ከትግራይ ወንድሞቻችን ጋር ሊያጋጩን የሚሞክሩትን የህወሀት ወንጀለኞች አስወግደን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር ማድረግ ነዉ።

የግንቦት 7 ንቅናቄ

 

Austrian tourist killed in Ethiopia attack

Austrian tourist killed in Ethiopia attack

(AFP)

VIENNA — A 27-year-old Austrian tourist was killed in northern Ethiopia when his group was attacked during a whitewater rafting trip on the Nile, Austria’s foreign ministry said Monday.eth_bahir_dar_map

The attack occurred on Sunday near Bahir Dar, 550 kilometres (340 miles) northwest of the capital Addis Ababa, ministry spokesman Martin Weiss told AFP.

The victim was part of a group of 10 Austrians on an organised whitewater rafting trip in the region.

Four of the group had spent the night camping on the banks of the Nile when they were apparently attacked by robbers. The victim’s three companions were unharmed in the incident.

“There were gunshots,” Weiss told AFP.

One of the tourists “was mortally wounded, the three others managed to escape and called the Austrian embassy in Addis Ababa.

“The (local) authorities were later informed and we received information this morning that the three individuals were safe. Shocked but in safety,” he added.

“Technical equipment was stolen, the boats were damaged. It was probably a band of bandits.”

Weiss added the attack did not seem to have been political motivated, saying: “It was just a robbery.”

No arrests have been made, the ministry spokesman said.

In its latest travel advice on Ethiopia, published in November, the Austrian foreign ministry warned of “a heightened risk of terrorist attacks”.

In January 2012, five foreign tourists, including an Austrian, were killed on the slopes of the Erta Ale volcano in northern Ethiopia. Addis Ababa blamed the attack on groups trained and armed by neighbouring Eritrea, an accusation the Eritrean government denied.

 

 Abbaymedia.con

The original Ethiopian flag arrived in Johannesburg: Excitement and jubilation…

The Horn Times News
by Getahune Bekele, Pretoria-South Africa

“Sendekalamachin!”

Excitement and jubilation as Ethiopian refugees received delivery of the original national flag.

South-Africa-2013-Ethiopia

Shock, anxiety and bewilderment griped TPLF officials at the Ethiopian embassy in Pretoria as refugees totally rejected the satanic flag of the minority junta; a symbol of the brutal internal colonization of Ethiopia.

On Thursday morning the original Ethiopian flag arrived in Johannesburg directly from China, ahead of the black lions opening match against the copper bullets of Zambia in Nelspruit, much to the delight of thousands of patriotic fans. It was immediately distributed, all thanks to the sterling work of the Ethiopian community association in South Africa and the anti TPLF organization known as Bête-Ethiopia.

It will be proudly displayed on Monday at Mbonbela stadium.

“We have a big surprise for the enemy of our flag, our history and our tradition- the ruling junta. We are going to shame the dead tyrant Meles Zenawi who once called our flag ‘a piece of garment.’ In bringing this flag here, great gallantry has been displayed by great individuals here in South Africa. Long live the Ethiopian community association! Long live Bête- Ethiopia!” an elated refugee told the Horn Times.

With some of the flag stretching for up to 10m, it is now all systems go.
The Horn Times also watched some Ethiopians publicly dumping the TPLF flag they received earlier from embassy officials.

Meanwhile, despite the minority junta’s attempt to sabotage the national team’s arrival, we are all at Oliver Tambo international airport in Johannesburg to welcome the black lions of Ethiopia.

infohorntimes@gmail.com

 

 Abbaymedia.com

ኢትዮቴሌኮም የወያኔ ዘረኝነት ፖሊሰ መንጸባረቂያ መሆኑን የግንቦት ሰባት የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ አጋለጠ

የመረጃ ቴክኖሎጂ መሠረት የሆነዉ የቴሌኮሚኒኬሺን ዘርፍ አፍሪካ፤ ላቲን አሜሪካና ኢሲያ ዉስጥ የሚገኙ በእደገት ወደ ኋላ የቀሩ አገሮችን ለዘመናት ከተዘፈቁበት የኋለ ቀርነት ማጥGINBOT 7 Movement ዉስጥ ጎትቶ አዉጥቶ ወደ ፈጣን የእድገት ጎዳና ይወስዳቸዋል ተበሎ የታመነበትና በአንዳንድ አገሮች ዉስጥ ይህ ለእድገት አመቺነቱ በተግባር የተመሰከረለት ዘርፍ ነዉ። ይህ ዘርፍ ገበሬዉ፤ ሰራተኛዉ፤ ተማሪዉ፤ ወታደሩና ለሌላም በማንኛዉም የስራ ዘርፍ ለተሰማራ የህብረተሰብ ክፍል የእዉቀት ምንጭ በመሆን የስራ ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የሚረደና በህብረተሰብ መካከል ፈጣን የሆነ የመረጃ ልዉዉጥ አንዲኖር የሚያደርግ ዘርፍ ነዉ። በእድገት ወደ ኋላ ለቀረችዉ አገራችን ኢትዮጵያም ይሀ ዘርፍ እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆነ ዘርፍ ነዉ። ነገር ግን በአፍሪካ ዉስጥ አገራችን ኢትዮጵያ እጅግ በጣም ወደኋላ ከቀርችባቸዉና ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ሆን ብሎ እድገታቸዉ እንዲገታ ካደረጋቸዉ ኋላ ቀር ዘርፎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ይሄዉ የቴሌኮሚኒኬሺን ዘርፍ ነዉ።

እራሱን “ልማታዊ መንግስት” ብሎ የሚጠራዉ የወያኔ አገዛዝ ስልጣን ከያዘባቸዉ የመጀመሪያዎቹ አመታት ጀምሮ አስከ ቅርብ ግዜ ድረስ እንደ ቤት ዉስጥ ዕቃዉ ከተቆጣጠራቸዉና የኢትዮጵያን ህዝብ በሚጠቅም መልኩ እንዳያድጉ ካደረጋቸዉ ቁልፍ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ አንዱ ኢትዮቴሌኮም ነዉ። ወያኔ ኢትዮቴሌኮምን ያላደረገዉ ነገር የለም። ዘረኝነትን በሚጠቅም መልኩ አደራጅቶታል፤ የራሱን ሰዎች ጠቅጥቆበታል፤ ቻይናዎችን አምጥቶ የስለላ ተቋም አድርጎታል፤ የሚገርመዉ ዛሬ ኢትዮቴሌኮም የተራቀቀዉ በስልክ፤ በኢንተርኔትና በሌሎችም የመገናና አገልግሎቶች ሳይሆን ዜጎችን በመሰለልና የመረጃ ጨለማ በመፍጠር ርካሽና ጎታች ስራዎች ነዉ። ይህንን ርካሽ ስራ ደግሞ በቅርቡ የአገዛዙ የኢንፎርሜሺን ደህንነት ኤጀንሲ ሹም ብ/ጄኔራል ተክለብርሃን ወልደአረጋይ “የኢትዮጽያ ቴሌኮምኒኬሽን” የኀብረተሰቡን ሰላም የሚያጠፉ ዌብሳይቶችን የመቆጣጠርና የኢንተርኔት ድረገጾችና ብሎጎችን የማገድ አቅም ሊኖረው ይገባል፡፡መርሁም ይህ ነዉ በማለት በአዳባባይ አረጋግጧል።

የግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ በላፉት አስራ ሁለት ወራት ይህንኑ ኢትዮቴሌኮም በሚል መጠሪያ የሚተወቀዉንና በስለላ ስራ ላይ የተሰማራዉን የሲቪል መስሪያ ቤት አደረጃጀት፤ አወቃቀርና የሰዉ ኃይል አመዳደብ በቅርብ ተከታትሎ ከዚህ ቀትሎ የሚታየዉን መረጃ አጠናቅሯል።

ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚገባ እንደሚያዉቀዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የኢትዮጵያን ቴሌኮሚኒኬሺን ተቋም ከኋላ ቅርነት ለማላቀቅ በሚል ሰበብ የኮርፖሬሺኑን የማኔጅመንት ዘርፍ ለፈረንሳይ ኩባኒያ መስጠቱ የሚታወስ ነዉ። ወያኔ እንደሚለዉ የኢትዮቴሌኮም ማነጅመንት ለፈረንሳዩ ኩባኒያ የተሰጠዉ የኮርፖሬ ኑን አቅም ለማሳደግ ቢሆን ኖሮ መልካም ነበር፤ ነገር ግን ወያኔ የሚናገረዉና የሚሰራዉ ስራ የተለያየ በመሆኑ ዛሬ ወያኔ ኢትዮቴሌኮም በየዘርፉ የረጂም ግዜ ልምድ ያላቸዉን ባለሙያዎች አባርሮ ታማኝ የህወሀት ታጋዮችን በመተካት ኮርፖሬሺኑን የለየለት የስለላ ተቋም አድርጎታል። ስለሆነም ዛሬ ብዙ የአፍርካ አገሮች ትልቅ ግስጋሴ ያደረጉበትና የዜጎቻቸዉን ህይወት የለወጡበት ዘርፍ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎችን እየሰለለ አገረን የመረጃ ጨለማ ዉስጥ የከተተ ተቋም ሆኗል።

ባላፉት ሁለት አመታት የኢትዮቴሌኮም ማነጅመንት ኤን አንድና ኤን ሁለት በሚባሉ ሁለት ከፍተኛ የአስተዳደር እርከኖች ተከፍሎ በሁለቱም ከፍተኛ የአመራር እርከኖች ዉስጥ የሰዉ ኃይል ተመድቧል። ይህ በከፍተኛ ማነጅመንት ደረጃ የተመደበዉ የሰዉ ኃይል ኢትዮጵያዉያንንና የፈረንሳይ ዜጎችን የሚያጠቃልል ነዉ። በኤን አንድና በኤን ሁለት የማነጅመንት ደረጃ የስራ ድርሻ የተሰጣቸዉ ኢትዮኦጵያዉያን በቁጥር 54 ሲሆኑ ከዚህ ዉስጥ 46.3 በመቶ ወይም ሃያ አምስቱ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። በዚህ ከፍተኛ የማነጅመንት እርከን ዉስጥ የኦሮሞ፤ የአማራና የተቀሩት ስድሰት ክልሎች ድርሻ በቅደም ተከተል 18. 5 በመቶ፤ 29.6 በመቶና 5.6 በመቶ ብቻ ነዉ። ከሁለቱ የማነጅመንት እርከኖች ዉስጥ ኤን አንድ የሚባለዉ ከፍተኛዉ ሲሆን በዚህ እርክን ዉስጥ ሰምንት የትግራይ ተወላጆች ሲኖሩ የአማራና የኦሮሞ ተወላጆች እያንዳንዳቸዉ ሁለት ቦታ የያዙ ሲሆን በዚህ ከፍተኛ የአመራር እርከን ዉስጥ ከተቀሩት ስድስት ክልሎች የተመደበ አንድም ሰዉ የለም።

ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ ከእያንዳንዱ 3.3 ሚሊዮን የኦሮሞ ተወላጅ ዉስጥ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ የተሰጠዉ አንድ የኦሮሞ ተወላጅ ብቻ ሲሆን ትግራይን ስንመለከት ግን ከእያንዳንዱ 194 ሺ የትግራይ ተወላጅ ዉስጥ ቢያንስ አንድ ሰዉ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ ተቀምጧል። ይህ የስራ አመዳደብ የትምህርት ችሎታንና ልምድን ተከትሎ የተሰራ ነዉ ቢባል እንኳን የላቀ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ያለቸዉ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ካላቸዉ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር በአስር እጥፍ መብለጡ ምንም ጥርጥር የለዉም። ሌላም መራራ ሀቅ አለ። 66 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆነዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚያቅፉት ከኦሮሚያና ከአማራ ክልል N1 በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር አርከን ዉስጥ በአመራር ቦታ የተቀመጡ ዜጎች ብዛት አራት ብቻ ነዉ (ሁለት ከኦሮሚያ ሁለት ከአማራ)። ከጠቅላላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ 5.4 በመቶዉ ብቻ ከሚኖርበት ከትግራይ ክልል ግን ስምንት ሰዎች ኤን አንድ በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ ተቀምጠዋል።

በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ ከተቀሩት ስድስት የአገሪቱ ክልሎች የመጡትን ሰዎቸ ስንመለከት የሚታየዉ ስዕል እጅግ በጣም የሚያሳዝንና ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት እያለ ከሚሰብከዉ ስብከት ጋረ የሚጋጭ ነዉ። በ2012 ከኦሮሚያ፤ ከአማራና ከትግራይ ክልል ዉጭ በተቀሩት ስድስት ክልሎች ዉስጥ የሚኖረዉ ህዝብ 25,627,349 እንደሚሆን ይገመታል። ከዚህ ህዝብ ዉስጥ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የመቀመጥ እድል ያገኙት 0.000012 በመቶ ብቻ ወይም ከእያንዳንዱ 8.5 ሚሊዮን ህዝብ አንዱ ብቻ ነዉ። እንግዲህ ይህንን ነዉ ወያኔ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነታቸዉን ተጎናጽፈዋል እያለ የሚናገረዉ።

የግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከዚህ ቀደም ወያኔ “የኢትዮጵያ መከላከያ” ጦር እያለ የሚጠራዉን ሠራዊት ምን ያክል የኔ በሚላቸዉ የህወሀት ሰዎች ብቻ እንደሚቀጣጠር የሚያሳይ መግለጫ በመረጃ አስደግፎ ለህዝብ ማቅረቡ የሚታወስ ነዉ። አሁንም ወያኔ ኢትዮቴሌኮምን ምን ያክል የራሱ የቤት ዉስጥ እቃዉ እንዳደረገዉ የሚያሳየዉን በጽሁፍና በአኀዝ የተፈገፈ መረጃ በዛሬዉ እለት ለህዝብ ይፋ የሚያደርግ መሆኑን እየገለጸ ከአሁን በኋላም የወያኔን ዘረኝነትና ህግወጥነት የሚያጋልጡ ስራዎችን በተከታታይ እየሰራ ለህዝብ የሚያቀርብ መሆኑን ይገልጻል።

የጥናቱ እጠቃላይ ውጤት

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication1

ማስታወሻ: ከላይ በስዕሉ የሚታየው እንደተጠበቀ ሆኖ በኢትዮ-ቴሌኮም ቁልፍ የሃላፊነት ቦታወች ውስጥ ቢያንስ ቢያንስ ወደ 50% የሚሆነው ቦታ የተያዘው በትግራይ ተወላጆች ነው።

ይንንም ለማብራራት ያህል በአሁኑ ሰአት ካለው ጠቅላላ የሃፊነት ቀልፍ ቦታወች 14ቱ በፈረንሳውያን የተያዙ ቢሆንም ከ14 የፈረንሳይ ባለሙያወች ከያዟቸው ቀልፍ ቦታወች ውስጥ 7ቱ በትግራ ተወላጆች እንደሚያዙ ይጠበቃል። ይህም ማለት በትግራይ ተወላጆች የተያዙትን እና የሚያዙትን ቁልፍ የኢትዮ-ቴሌኮም ቦታወች ከተጠቅላለው 64ቱ የሃላፊነት ቦታቸው ውስጥ 32ቱ በትግራይ ተወላጆች የተያዙ ይሆናሉ። ይህም ማለት ከጠቅላላወ የኢትዮ-ቴሌኮም ቁልፍ የሃልፊነት ቦታቸው ውስጥ ግማሹ ማለትም 47% የሚሆኑትን በትግራይ ተወላጆች የተያዙ መሆናቸው ያሳያል።

የጥናቱ ዝርዘር ማብራያ

በዚህ ሰነድ ላይ የተጠቃለሉት ስሞች በኢትዮ ቴሌኮም ዋና መስሪያ ቤት ዉስጥ በሁለት ከፍተኛ (N1 & N2) የአመራር እርከኖች ዉሰጥ የተመደቡ ሰዎች ስምና የመጡበት ብሔር ስብጥር ነዉ። ባጠቃላይ በሁለቱ የአመራር እርከኖች ዉስጥ 68 ሰዎች የሚገኙ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ አስራ ሰባቱ (N1 ዉስጥ 8 N2 ዉስጥ 9) የፈረንሳይ ተወላጆች ነበሩ። ሆኖም ቀስ በቀስ በተደረገዉ መሸጋሸግ የፈረንሳይ ዜጎች የለቀቁት ቦታ እየተመረጠ ለትግራይ ተወላጆች ብቻ በመሰጠቱ አሁን በN1 ዉስጥ 5 N2 ዉስጥ 9 ባጠቃላይ 14 የፈረንሳይ ዜጎች አሉ ፤ በቅርቡ አንድ ሌላ የፈረንሳይ ዜጋ በኢትዮጵያዊ የተተካ ቢሆንም ይህ ሠኢድ አራጋዉ የተባለ ግልሰብ አማራ ይሁን ትግሬ ለግዜዉ በዉል ለይቶ ማወቅ አልተቻለም። በእርከን አንድ ዉስጥ ስምንት የትግራይ፤ ሁለት የአማራና ሁለት የኦሮሞ ተወላጆች ሲኖሩበት ከሌሎቹ ሰባት ክልሎች የመጣ አንድም ሰዉ በዚህ N1 በሚባለዉ የአመራር አርከን ላይ አልተመደበም። በአጠቃላይ በ N1 የአመራር አርከን ዉስጥ 17 ሰዎች ሲኖሩ አስራ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን አምስቱ ደግሞ የፈረንሳይ ተወላጆች ናቸዉ። ከአስራ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን ዉስጥ ሰባቱ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። N2 በሚባለዉ የአመራር አርከን ዉስጥ ደግሞ 51 ግለሰባኦች በአመራር ቦታ ላይ የተመደቡ ሲሆን 42 ኢትዮጵያዉያን 9ኙ ፈረንሳዉያን ናቸዉ። ከአርባ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን ዉስጥ አስራ ሰባቱ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ።

ይህ በከዚህ ቀጠሎ የተቀመጠዉ ግራፍ እና ሰነተረዥ የሚያሳየዉ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የተቀመጡትን ሰዎች የብሔር ስብጥር ነዉ። ግራፉ የሚያሳየዉ ሦስቱን ማለትም ከኦሮሚያ፤ ከአማራና ከትግራይ ክልል የተመረጡ ሰዎችን ለየብቻቸዉ ሲሆን ከተቀሩት ሰባቱ ክልሎች የመጡት ሰዎች ግን ተጨፍለቀዉ አንድ ላይ ነዉ የቀረቡት።

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication2ማስታወሻ: ከላይ በሰንጠረዡ የጠቀሰው የህዝብ ብዛት እኤአ በ2007 CSO ያወጣዉን የህዝብ ብዛት መግለጫ ተንተርስሶ በ2012 የኢትዪጵያ ህዝብ ብዛት 90,076, 661 ይሆናል በሚል ግምት የተቀመረ ነዉ።

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication3

በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የተቀመጡት ሰዎች የብሔር ስብጥር

ከላይ በተቀመጠዉ የህዝብ ብዛት መሠረት በ N-1 እና በ N-2 የአመራር እርከን ኢትዮ ቴኦኮም ከተመደቡ ሰራተኞች ዉስጥ የሚከተለዉን ገሀድ እዉነት መመልከት ይቻላል።
ከእያንዳንዱ 3.3 ሚሊዮን የኦሮሞ ተወላጅ ዉስጥ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ የተሰጠዉ አንድ የኦሮሞ ተወላጅ ብቻ ሲሆን ትግራይን ስንመለከት ግን ከእያንዳንዱ 193.9 ሺ የትግራይ ተወላጅ ዉስጥ ቢያንስ አንድ ሰዉ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ ተቀምጧል። ይህ የስራ አመዳደብ የትምህርት ችሎታንና ልምድን ተከትሎ የተሰራ ነዉ ቢባል እንኳን የላቀ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ያለቸዉ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ካላቸዉ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር በአስር እጥፍ መብለጡ ምንም ጥርጥር የለዉም። ሌላም መራራ ሀቅ አለ። 66.2 በመቶ የሚሆነዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚያቅፉት ከኦሮሚያና ከአማራ ክልል N1 በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር አርከን ዉስጥ በአመራር ቦታ የተቀመጡ ዜጎች ብዛት 4 ብቻ ነዉ (2 ከኦሮሚያ 2 ከአማራ)። ከጠቅላላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ 5.4 በመቶዉ ብቻ ከሚኖርበት ከትግራይ ክልል ግን 7 ሰዎች N1 በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ ተቀምጠዋል።

ከዚህ በታች ያለው ሠንጠረዥ የሚያሳየዉ ኢትዮ-ቴሌኮም ዉስጥ N-1 በመባል በሚታወቀዉ ከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ የተቀመጡትን ባለሙያዎች የብሔር ስብጥር ነዉ፤ በዚህ ስብጥር ዉስጥ የፈረንሳይ ዜጎችም አሉበት። በ N-1 አመራር እርከን ዉስጥ ከትግራይ፤ ከኦሮሚያና ከአማራ ብሔረሰቦች ዉጭ ከሌሎቹ የተካተተ ማንም የለም።

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication4

ኢትዮ-ቴሌኮም ዉስጥ N-1 በመባል በሚታወቀዉ ከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ የተቀመጡትን ባለሙያዎች የብሔር ስብጥር

ከላይ ካለው ሰንጠረዥ ላይ እንደምንመለከተዉ በ N-1 የአመራር እርከን ደረጃ ላይ የተቀመጡ ኢትዮጵያዉያን ብዛት አስራ አንድ ሲሆን ሰባቱ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። የእነዚህን 7 ሰዎች የስልጣን ቦታ ስንመለከት ደግሞ ሁሉም የያዙት ቦታ ቁልፍ ቁልፋዩን ቦታ ነዉ። ለምሳሌ የፕሮግራም ማነጀር፤ ፕሮግራም ዳይረክተርና የቺፍ ፋይናንሻል ኦፊሰርነቱን ቦታ የያዙት የትግራይ ተወላጆች ሲሆኑ የኦሮሞዉና የአማራዉ ተወላጆች በቅደም ተከተል የህግ አማካሪነቱንና የኢዲተርነቱን ቦታ ነዉ የያዙት።

ከዚህ በታች ያለው ሠንጠረዥ የሚያሳየዉ ኢትዮ-ቴሌኮም ዉስጥ N-2 በመባል በሚታወቀዉ ከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ የተቀመጡትን ባለሙያዎች የብሔር ስብጥር ነዉ። በ N-2 ከፍተኛ የአመራር እርክን ዉስጥ ዘጠኝ የፈረንሳይ ዜጎች የሚገኙ ቢሆንም በሰንጠረዡ ዉስጥ የፈረንሳይ ዜጎች ቁጥር አልተካተተም (N-2 ከ N-1 ያነሰ ደረጃ ነዉ)።

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication5

ኢትዮ-ቴሌኮም ዉስጥ N-2 በመባል በሚታወቀዉ ከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ የተቀመጡትን ባለሙያዎች የብሔር ስብጥር

ኢትዮጵያ ዉስጥ በህዝብ ብዛትም ሆነ በተማረ ሰዉ ሀይል ብዛት ከፍተኛዉን ቦታ የያዘዉ የኦሮሚያ ክልል ነዉ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ከፍተኛዉን የመቀመጫ ቁጥር የያዙት የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች ናቸዉ። ሆኖም በሰንጠረዡ ላይ እንደምንመለከተዉ ኢትዮቴሌኮም ዉስጥ በN-1ም ሆነ በN-2 ደረጃ በአመራር ላይ ከተቀመጡት መሪዎች ዉስጥ የኦሮሚያ ድርሻ ከክልሉ ትልቅነት ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ነዉ ወይም ከትንሿ ትግራይ ጋር ሲወዳደር ቁጥሩ እጅግ በጣም አነስተኛ ነዉ።
በፖለቲካ ሀይል መስክም ቢሆን እንደዚሁ ነዉ። ህወሀት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዉስጥ ያለዉ መቀመጫ ብዛት 8 ብቻ ነዉ። ሆኖም የፖለቲካዉ ጡንቻዉ 178 መቀመጫ ካለዉ ኦህዴድ ጋር ሲወዳደር ሰማይና ምድር ነዉ። ህወሀት የአገሪቱን ጦር ሀይል፤ ፖሊሰ ሰራዊት፤ የደህንነት ተቋምና የኤኮኖሚ መዋቅሮች ይቆጣጠራል። ኦህዴድ ግን ከሰሞኑ እንደማስተዛዘኛ ከተወረወረለት የይስሙላ ምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ዉጭ ይህ ነዉ የሚባል የፖለቲካ ጡንቻ የለዉም።

ከሦስቱ ክልሎች ማለትም ከአማራ፤ ከኦረሚያና ከትግራይ ክልሎች ዉጭ በሌሎቹ ስድስት ክልሎች ዉስጥ 25,627,349 ያክል ህዝብ እንደሚኖር ይታመናል። ኢትዮቴሌኮም ዉስጥ በ N- 1 ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የእነዚህ ሰባት ክልሎች ድርሻ ሦስት ብቻ ነዉ። እንግዲህ ዜጎች በሞያቸዉ በሚሰሩት ስራ፤ በፖለቲካ ህይል አሰላለፍና በኤኮኖሚዉ ዘርፍ ዉስጥ በሚጫወቱት ሚና እንዲዚህ አይነት አይን ያወጣ አድሎ የሚደረግባቸዉ ከሆነ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፈጠርኩት የሚለዉ እኩልነት ምኑ ላይ ነዉ? የባህል ዘፈን መዝፈን ከሆነ እንደዛሬዉ በቴሉቪዥን አይታይም እንጂ ድሮም እንዘፍናለን።

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication6

ethio telecom, ethiopian telephone and mobile communication8

ሰበር ዜና፣ መንግስት በምስክር እጦት ጭንቅ ውስጥ ገብቷል፡፡

የብዙዎች ምላሽ ‹‹በሐሰት አንመሰክርም›› የሚል ሆኗል፡፡

በእስር ላይ የሚገኙ መሪዎቻችን እና ሌሎች ወንድሞቻችንን በአሸባሪነት ከስሶ ሲያንገላታ የቆየው መንግስት በምስክር እጦት ችግር ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ መንግስት ኮሚቴዎቻችን ላይ በመሰረተው ክስ በሐሰት ሊያስመሰክራቸው ያዘጋጃቸው 197 (አንድ መቶ ዘጠና ሰባት) ሰዎች መኖራቸውን ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም የተገለጸውን ቁጥር ያህል ምስክሮች ማግኘት አልቻለም፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው ለምስክርነት የታሰቡት ብዙዎቹ ግለሰቦች ምስክር ለመሆን ፈጽሞ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ነው፡፡ መሪዎቻችን ባልዋሉበት እና በማያውቁት ወንጀል የከሰሳቸው መንግስት በየአካባቢው ‹‹ድጋፍ ይሰጡኛል፤ እተማመንባቸዋለሁ›› የሚላቸውን ግለሰቦች ለምስክርነት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርግላቸውም በሐሰት አንመሰክርም የሚል ቆራጥ አቋም ማሳየታቸው ተሰምቷ፡ል፡ሰበር ዜና

ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውን የመብት ጥያቄዎች ለመንግስት እንዲያደርሱለት በአስር ጣቱ አምኖባቸው የመረጣቸው ኮሚቴዎቻችን እና ሌሎች ዳኢዎች መንግስት እውቅና ሰጥቷቸውና ስለ ሰላማዊነታቸውም በመንግስት ብዙሀን መገናኛዎች መስክሮላቸው፤ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ድርድር ሲያደርጉ እንደቆዩ ይታወሳል፡፡ ሆኖም መንግስት የቀረቡትን የመብት ጥያቄዎች ለመመለስ አለመፈለጉና እነሱም ጥያቄዎቹ እንዲመለሱ ተደጋጋሚ ጥያቄ በማቅረባቸው ‹‹አሸባሪ›› የሚል ታፔላ ተለጥፎባቸው ከሐምሌ 2004 ጀምሮ በእስር እና ስቃይ ላይ የሚገኙት መሪዎቻችን ንጹህ መሆናቸውን የተረዱ ብዙዎች በሀሰት እነሱ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በቀጥታ መግለጽ ችለዋል፡፡

መንግስት ይህን የመስካሪዎች እምቢታ ተከትሎ አዳዲስ ምስክሮችን ለመመልመል ቀን ከሌት እየሰራ እንደሚገኝ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ የመንግስት ደህንነቶች ቁጣና ንዴት በተሞላበት መልኩ ሰዎችን ምስክር እንዲሆኑ በአካልም ጨምር እየሄዱ በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ደህንነቶቹ በአዲስ አበባ አንድ አንድ መስጊዶች በመገኘት ግለሰቦችን በግድ በመያዝ ምስክር እንዲሆኑ እየጠየቁ ሲሆን፤ ፈቃደኛ አልሆንም ያሉ ሰዎችንም ‹‹የማትመሰክር ከሆነ አንተን ነው የምንከስህ›› በማለት በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የሀሰት ምስክርነትን (ሸሀደተ ዙር) አስከፊ ወንጀልነት የተረዱ በርካታ ሙስሊሞች አሁንም በእምቢታቸው የዘለቁ ሲሆን፤ አሁንም ግን ጥቂት የማይባሉ ‹‹ተገደን ነው የምንመሰክረው›› የሚል ምላሽ እየሰጡ ያሉ ግለሰቦች በመኖራቸው ከዚህ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡና ከአስከፊው የሀሰት ምስክርነት መዘዝ እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ አደራ እንላለን፡፡

አቡበከር ሲዲቅ (ረ.ዓ) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ማለታቸውን ዘግበዋል፡- ‹‹የከባዶች ከባድ የሆነውን ሀጢአት አልነግራችሁንም›› እኛም ‹‹አዎ! የአላህ መልዕክተኛ እንዴታ!›› አልን፡፡ እሳቸውም ‹‹በአላህ ማጋራት (ሽርክ) እና ወላጅን ያለመታተዝ ናቸው›› አሉና ተደላድለው ከተቀመጡበት ድንገት ተነስተው እንዲህ አሉ ‹‹አዋጅ! ውሸት መናገር እና በሐሰት መመስከ›› እያሉ የሚያቆሙት አልመስልህ እስኪለኝ ድረስ ደጋገሙት ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል፡፡

አላሁ አክበር!

 

አዲሱ መጅሊስ ሲጋለጥ ያንብቡት!!!

አዲሱ መጅሊስ ሲጋለጥ ያንብቡት!!!

ethiopian muslim new mejliss

በአንድ የግል ጋዜጣ የዘንድውን አወዛጋቢ የመጅሊስ ምርጫ አስመልክቶ የተመረጡትን ሰዎች ፕሮፋይል እየተመለከትኩ ነበር፡፡ ከጎኔ የነበረ ሰው የሙስሊም ኮፍያዬን ቀና ብሎ ተመልክቶ ከበፊቱ መጅሊስ የተሻለ ዓለማዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ዕውቀት እንዳላቸው ነገረኝ፡፡ በጋዜጣ መሸጫ ዙሪያ “ሲቪሎች” ስለሚበዙ እሱም መረጃ እየሰራ ይሆናል በሚል ግምት በአጭሩ ያለውን መስማማቴን በንቅናቄ ገልጬ ገጹን በመገልበጥ አባረርኩት (አባረረኝ)- ብቻ ያው ነው፡፡ ከዚህ ሰውዬ አስተያየት ጀምሮ እስከ ዛሬ ያማጥኩትን ለአንባቢያን ላበቃ ዘንድ እነሆ ብእሬን አነሳሁ፡ እኔ መሐመድ ካሊድ አዲሱ መጅሊስ  ባለስልጣናት /ፎቶ ምንሊክ ሳልሳዊ / ስለ ሰላማዊ ትግል በሚወራበትና ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለ 1 ዓመት ሙሉ ሕገ ወጡ መጅሊስ ይወገድ ከማለት ጀምሮ እስከ መሪዎቼ ይፈቱ ከዚያም ምርጫው ውድቅ ይደረግ ጥያቄ በአወሊያ ተጀምሮ እስከ ታላቁ አንዋር መስጂድ በዘለቀው የሰላማዊ ተቃውሞ የአንድ ዓመት ክብረ በዓል እየተከበረ ባለበት ወርሐ ታኅሳስ የመጨረሻ ሳምንት ስለ በግዱ መጅሊስ ማውራት ባይመስጥም ቢያንስ ውስጣዊ አሰራሩን ታነቡት ዘንድ ከትቤዋለሁ፡፡

አዲሱ መጅሊስ

በመጅሊሱ “የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ” በሚለው ይሁን የእውነት አምነውበትና በአላማው ተመስጠው አሊያም ካድሬነት በሀይማኖት ተቋም ብዙ ተሰላፊ ስለሌለውና ሕወሓቶች ስለማይበዙበት በቀላሉ ትልቅ ካድሬ ሆኖ ለመገኘት ሲሉ አለያም የሀጅ ቢዝነስ አሪፍ ነው ሲባል ሰምተው አላውቅም ብቻ ወንድሞቻቸው አደባባይ እየጮሁ አልፈው ጥቂቶች የተወዳደሩበት በግዴታ ምርጫ ተካሂዶ እነሆ  እንደገና ተዋቅሯል፡፡ (አህመዲን አብዱላሂንም እንደስም ይጠራበት የነበረውንና ጨርቅ ከመሆኑ በቀር የአጼ ምኒሊክን ዘውድ የሚመስለውን ጥምጣሙን ተገላግሎ በኮፍያና በሸሚዝ መሀል ቦሌ ፈታ ብሎ ሲሄድ ልናየው ችለናል፡፡)

አዲሱ መጅሊስ የመጣበትን የምርጫ ሂደት ከቀበሌ መጀመሩ በታሪክ የመጀመሪያ ነው፡፡ ይህን ምርጫ ለማስተባበርም የተሰጠውም የመንግስት ሚዲያ ሽፋን ከመቼውም የተሻለ ነው፡፡ ተቃውሞውም እንዲሁ ታላቅ ነበር፡፡ ለዚህም ይመስላል በመጅሊሱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በድግሪና በማስተርስ ድግሪ ደረጃ የተማሩ ሰዎች ለስራ አስፈጻሚነት ደረጃ መድረሳቸው፡፡ ስለነዚህ ጉዶችም ብናወራ የመጅሊሱን ሁኔታ ለመረዳት የሚረዳ ይመስለኛል፡፡

አዲሱ መጅሊስ በሸህ ኪያር ሙሀመድ ፕሬዝዳንትነት ይመራል፡፡ በዋናው የመጅሊስ ስልጣን ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት እና ለስላሳው ለውሳኔ የሚቸገሩት ሙሀመድ አሊ እንደ ዋና ጸኀፊ ተወዝተዋል፡፡ በምክትል ፕሬዝዳንትነት የህዋሃት አባል የሆኑትና የቀድሞ የትግራይ ክልል የሸሪዓ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣የክልሉ እስልምና ጉዳይ ፕሬዝዳንትነትና ሁሉንም ስራ አስፈጻሚ አባረው የሁሉም ዞኖች ተወካይ በመሆን ሁሉን ነገር የራሳቸው ጠቅለው በመያዝ ያላቸውን የአንባገነንነት አቅም ያስመሰከሩት ሼህ ከድር ማህሙድ ተሰይመዋል፡፡ ከዚህ ውጭ ሌሎቹን ስራ
አስፈጻሚዎች በሌላ ጊዜ አስተዋውቃለሁ፡፡

ይህ መጅሊስ በጎኑ እንዳይተኛ የሚያደርጉ ሀሳቦችን በመዳሰስ ትንሽ ልበል፡፡ መጅሊስ ማለት ሙስሊሙን ማህበረሰብ በሀይማኖታዊ ጉዳዩ የሚዎክል ተቋም እንደመሆኑ በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ብዙ ነገር አርፎ እንዳይተኛ ያደርገዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ የመጅሊሱን ፈተናዎች እና የፈተናውን ተዋናኞች ከዚህ በታች ባጭሩ እንዳስስ፡፡

1. የመጅሊሱ ቅቡልነት

መጅሊሱ ከድሮውም ለቅቡልነት አልታደለም፡፡ ይሁንና ያሁኑ ይባስ እንዲሉ ህዝበ ሙስሊሙ መጅሊሱን አንቅሮ ተፍቶታል፡፡በሙስሊሙ ማህበረሰብ አኳያ መጅሊሱ እመራዋለሁ የሚለው ህዝብ እየከሰሰውና እየገረመመው መኖሩ ጤናማ አይደለም፡፡  ይሁንና ያለፈው አልፏል እስኪ አንድ እድል እንስጣቸው ብሎ የሚነሳ ሙስሊም እንኳ ቢኖር በጥንቃቄ ካልተያዘ ያጡታል፡፡ ለዚህ ነው መጅሊሱ ለቅቡልነቱ የሚሰራውን ስራ ፈታኝ ነው የምለው፡፡ መጅሊሱ መልኩ ከፍቷል፡፡ ከሁሉ በፊት ፊቱ መዋብ አለበት፡፡ የመጅሊስን ክፉ ፊት ለማስዋብ ብዙ የመዋቢያ መሳሪያዎች (ኮስሜቲክሶች) የሚያስፈልጉት ሲሆን ምን ቢኳኳል ግን ፊቱ ላይ ያሉት ሁለት ቡጉንጆች ካልተወገዱ ሊዋብ አይችልም፡፡

እነዚህ ቡጉንጆች ኮማንደር ሙራድና ጀማል ሙሀመድ ሳሊህ ሲሆኑ እነዚህ እያሉ ገጽታን ማስተካከል የሚታሰብ አይደለም፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች የባለፈው ስራ አስፈጻሚ ይወገድልን ብሎ ህዝብ ሲጠይቅ አብሮ ፎቷቸው ተለጥፏል፡፡ ውሎ ማደሪያቸው ሳይቀር በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ተለቋል፡፡ ቀድሞም የመጅሊሱ ማንኛውም ውሳኔ የሚወሰነው በሰላም መምሪያ ጣልቃገብነት ነው፡፡ ትምህርት፣ቁርአን፣ልማት፣ሀጅ ወዘተ.. ብቻ ሁሉም ነገር ላይ የሰላም መምሪያ ጣልቃ ገብነት ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ኃላፊነት የስራ አስፈጻሚ ሲልም በየክፍሉ ያሉ የስራ ሓላፊዎች መሆን ሲገባው እንዴት ጠቅሎ ወሰደው? ብዬ ስጠይቅ ያገኘሁት መልስ ቢኖር መንግስት ነው የሚል ነው፡፡ ብዙዎች እነደውም የሰላም መምሪያው ፕሬዘዳንቱን ማዘዙ የአደባባይ ሚስጥር እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

አዲሱ መጅሊስ በኮከብነት የሚመሩት ሙስሊሙን ሲያተረማምሱ የኖሩት እነ ጀማል ሙሀመድ ሳልህ ( የእውነት ስሙ ገብሬና ለትግል ሲባል ስሙ ከነአያቱ የተቀየረ ተብሎ የሚታማ) በዲሲፕሊን ከጉለሌ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ የተሰናበተው ኮማንደር ሙራድ ፎቷቸው ከሌሎች ጋር በመሆን ለህግ እንዲቀርቡ በዚህ ሳምንት ዓመቱን በሚያከብረው ድምጻችን ይሰማ የፊስ ቡክ ገጽ የለጠፋቸው ናቸው፡፡

ይታያችሁ ኮማንደር ሙራድ የመጅሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆኖ ሲሾም ያለ ሀፍረት በሴትነታቸው የጠየቃቸው ሁለት ሴት ጓደኛሞች የመጅሊሱ ሰራተኞች ምን ይሰማቸዋል? ገብሬ እንደዱሮው ሁሉ ስራ አስፈጻሚውን አመራርና አመራር ያልሆነ ብሎ ከፍሎ ሀሳብ በማቅረብ የፈለገውን ስራ አስፈጻሚ ከስራ ሲያሳግድ ማየት እንዴት…..እንዴት….. እንዴት…ቅቡልነትን ያመጣል?

የፌደራል መጅሊስ 400 የሚሆን ሰራተኛ አለው፡፡ ይሄ ሰራተኛ ጉዳዬ ካማረው ለአደባባይ አሳልፎ ይሰጥሃል፡፡ በተለያዩ ጋዜጦች ላይ ካየናቸው የሂሳብ ሰነዶች ጀምሮ ለየመንግስት መስሪያ ቤቱ እስከገቡት ሰነዶች ድረስ ያለው ሚስጥር የወጣው በተለያዩ ሰራተኞች ነው፡፡  ባጭሩ የመጅሊሱ ሰራተኛ ማለት ወሳኝ ምስክር ማለት ነው፡፡ ምክር ቤቱ የስራ ባህሉ ክፉኛ የተጎዳ ከመሆኑ የተነሳ እድሜ ለነ እንቶኔ አብዛሀኛው ሰራተኛ ከስራ ይልቅ ወሬ ማቀበል እንደሚያሳድግ ገብቶት የነገር ማቀበል ሚና መጫወት ህሊናው የፈቀደ እያቀበለ ህሊናው ያልፈቀደው ደግሞ በስራ የሚመጣ ነገር እንደሌለ በመገንዘብ ቀኑ ሲመሽና ሲነጋ እየታዘበ ልጆቼን ላሳድግ የሚል ሆኗል፡፡

ከዚህ ባሻገር የአህሉሱና ወለወጀማአ እና ሱፊ ሰለፊ ጉዳይ ገና አነጋጋሪ ነው፡፡ የየእስልምና ምክር ቤቶቹ ምርጦች የመጡት በሱፊ መስፈርት ነው፡፡ ህዝቡ ደግሞ አንድነት እያለ ነው፡፡ የመጅሊሱ አመራሮች ቃለ መሃላ የፈፀሙትም በዚሁ መልኩ ነው፡፡ ሙስሊሙን ማህበረሰብ በአህሉሱና ወለወጀማዓ አስተምህሮ ለመምራት! ታዲያ የተመረጡበት መስፈርት ተቀይሮ አንድነትን ከግምት ውስጥ ያስገባ አካሄድ ቢሞከር ቅቡልነትን ለማግኘት ያግዝ ይሆናል፡፡

ሶስተኛው ጉዳይ የህዝብ ግንኙነት ስራ በአብዛሀኛው ቅቡልነትን ከመገንባት አኳያ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡ ይሁንና መጅሊስ ገብታችሁ የህዝብ ግንኙነት ክፍሉን ብትመለከቱ በሰው ሃይል ረገድ በእጅጉ ተጎድቷል፡፡ ለዚህ ይመስላል አዳዲሶቹ ስራ አመራሮች ውሉ ጠፍቶባቸው ቢሮዎችን በመቀላቀል ትላልቅ ቢሮዎችን በመፍጠርና ቀለም በመቀባት ስራ ላይ የተጠመዱት፡፡ አዲሶቹ መጅሊሶች ከገቡ ሶስት ቢሮዎች ፈርሰው አንድ ትልቅ ቢሮ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ሁለት የትውውቅ መድረኮች ተከፍተዋል፡፡ ……ወዘተ፡፡

2. የመጅሊሱ የውስጥ መዋቅር

መጅሊስ በውስጡ የተለያዩ የልማት ተቋማት ያሉት ሲሆን የአወሊያ ተቋማት እና የልማት ኤጀንሲ እንዲሁም በመጅሊሱ የተለያዩ ዘርፎች ስር ያሉ ክፍሎች ይገኛሉ፡፡ በነዚህ ተቋማት ስር ከ 400 በላይ ሰራተኞች ያሉ ሲሆን ከትምህርት ዝግጅትና ልምድ አኳያ ጥሩ ሊባል የሚችል አቅም ያላቸው ሰዎች አሉ፡፡ በዚህ ተቋም ያለፈ የስራ ሂደት ታዲያ ይህን የሰው ሀይል በአግባቡ ስራ ሊያሰራ የሚችል አደረጃጀትም ሆነ ህግና ደንብ የሌለው በመሆኑ ሰራተኛው በማያውቀው ምክንያት በዙሪያው ሲከናወን ቆይቷል፡፡ ይህ በዚህ ሂደት የተዳከመና የተሰላቸ ሰራተኛ ስለመጅሊሱ ከስራ አስፈጻሚዎች በላይ ያውቃል፡፡ መጅሊሱ ሲቋቋም ጀምሮ አዲሱን በመቀበል እና ነባሩን በመሸኘት ከ 15 ዓመታት በላይ ከመጅሊሱ ጋር የቆዩ ሰራተኞች ከ1987 ጀምሮ የነበሩ መጅሊሶችን ተመልክተዋል፡፡ በንግግር የተካኑ የነበሩት መጅሊስ ስራ አስፈጻማች በባዶ ተስፋ ሲደልሉት ቆይተዋል፡፡ በመሆኑም የመጅሊሱ ሰራተኞች ተጨባጭ ለውጥ በተግባር ካላዩ ለመጅሊሱ የኔነት ስሜት ፈጽሞ ሊሰጡት አይችሉም፡፡

የመጅሊሱ ነባር ስራ መረጃ አያያዝም ደካማ በመሆኑ የመጅሊሱ ስራ አስፈጻሚዎች በቀጥታ ወደ ስራ ለመግባት የሚችሉበት ሁኔታም አይኖርም፡፡ መጅሊሱ ያለው የስራ መመሪያም ሆነ መዋቅር በሰኔ 1993 ዓ.ም የተዘጋጀ ሲሆን አሁን ካለው መዋቅር ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው እስከሚመስል ድረስ በሂደት ተቀያይሯል፡፡ የመዋቅሩን ማርጀት ተከትሎም በርካት መደቦች በተፈለገው ጊዜ ሊቀጠር በተፈለገው ሰው ልክ ሲፈጠሩ ቆይተዋል፡፡በዚህ ሂደት የተጠራቀሙ ሰራተኞች ቀን አሳላፊ ሆነው ተቀምጠዋል፡፡ የስራ አስፈጻሚ ሚስት፣ልጅ፣እህት ባጠቃላይ ዘመድ አዝማድ ሆነው ግቢውን የረገጡና በዛው የቀሩትን ብዛት መጅሊሱ ይቁጠረው፡፡ ከእንግዲህ ይህን ሰራተኛ ነው ሁሉንም የሚመጥን የትምህት ዝግጅትና ልምድ ላይ ተመስርቶ ስራ ሰጥቶ ወደጤናማ ተቋም አካል መቀየር የሚቻለው፡፡

3. የውጭ እጆች

ሌላኛው የመጅሊስ ጣጣ ሆኖ የሚገኘው የውጭ እጆች  ልብ በሉልኝ ፡፡ ይህ ምክር ቤት በሀጅና ኡምራ ስራ ከብዙ ድርጅቶች ጋር ሲሰራ ቆይቷል፡፡ በዚህ አወዛጋቢ የሀጅና ኡምራ ስራ የመስራት አበሳ ከተቋሙ ጋር ያነካካቸው ሰዎች ሁሉ ምንጌዜም ስራ አይፈቱም፡፡ ከመጪው ስራ አስፈጻሚ ጋር ሲስማሙ አብረው በመስራት ሳይስማሙ ይሄኛውን ጥለው ለነሱ የሚመቸውን ለማስመጣት ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ ይሄ እጅ ምንጊዜም ስራ አይፈታም፡፡ ታዲያ ይህ እጅ አነዴ በጋዜጣ ሌላ ጊዜ በመጽሄት፤ ካልሆነም በተለያዩ የመንግስጥ የደህንነት መዋቅሮች ውስጥ አልፎ መምጣቱ ነው መከራው፡፡ አላሰርቅ ያለ ስራ አስፈጻሚ በሆነ ምክንያት አሸባሪ እንደማይባልና ከስራ እንደማይታገድ ምን ዋስትና አለን??

4. የመጅሊሱ የሰላም መምሪያ

ሌላኛው የመጅሊሱ ጣጣ የመጅሊሱ የሰላምና መረጃ መምሪያ ነው፡፡ የቀድሞ መጅሊስ አመራሮች መጅሊሱ በተለያየ ጊዜ ስልጣኑን ማቆየት ሲሳነው የዙፋኑ ጠባቂዎች እንዲሆኑ ለማድረግ ያመጣቸው የሚታወቅ ሙያም ሆነ ትምህርት የሌላቸው ሰዎችን ያቀፈ ክፍል ነው፡፡(ይህ ክፍል ከላይ የጠቀስኳቸውን ኮማንደር ሙራድን አቶ ገብሬ (ጀማል ሙሀመድ ሷሊህን) ጨምሮ 30 ሰራተኞችን የያዘ ነው፡፡ ይህ ቡድን በሀጅ ጉዞ 43434 ብር ተሸፍኖለትና ተጨማሪ 30000 ብር አበል ተሰጥቶት ሀጅን ሊቆጣጠር ሳይቀር ሳውዲ ይሄዳል፡፡ በመጅሊሱ ምርጫ ሂደትም በተለይም ዋና ጸኀፊ የነበረውን አቶ አልሙሀመድ ሲራጅን ለማስመረጥ እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ እንደነበረ በሰፊው ተወርቷል፡፡ ይህ ክፍል የመጅሊሱ ግል ማህደሩ ውስጥ የሁለተኛ ደረጃ መረጃ እንኳ የሌለው መሆኑን የሚያመለክተውን የመጅሊሱን ሰራተኛ በግጭት አፈታት ከአምስተርዳም ዩኒቨርስቲ ማስትሬት ድግሪ አለው ብሎ በኢትዮ ሙስሊም ጋዜጣ ሲያስነበበን ነው ተብሎም ይታማል፡፡

በአዲሱ የመጅሊስ ምርጫ የተመረጡት የመጅሊስ ፕሬዝዳንት የትምህርት ደረጃ ቀድሞ ተነግሮን ነበር፡፡ይህ በኋላ ላይ ሲጣራ ሃሰት ሆኖ የተገኘው ይህ የተመራጮች መረጃ የተቀነባበረው እና የሚነዛው በዚሁ ክፍል ስር ለዚህ ስራ በተሰማሩ ሰራተኞች መሆንም የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡

የፕሬዝዳንቱ ቤተሰቦች የጉዞ ወኪል ቢዝነስ ያላቸው ሲሆን ከድፍን ኦሮሚያ ይህን አይነቱን ሰው ማምጣቱ በአንድ በኩል ለሀጅ ሙስና የተመቻቸና በልቶ የሚያበላ ነው የሚል ሃሜት በአዲሱ አመራር ላይ በሰፊው እየተወራ ቢሆንም የሰላም መምሪያው የግልና  ተቋማዊ ድጋፍ አዲሱም መጅሊስ ከቀድሞው የተለየ እንዳልሆነ ያመለክታል፡፡ አዲሱ ፕሬዝዳንት ግቢ ከገባ ጀምሮም ከሰላም መምሪያ ጋር ጠንካራ ግንኙት እንዳለው መገንዘብ ተችሏል፡፡

እንደመውጫ

የሕዝብ ተሳትፎ ለልማት ወሳኝ እንደሆነ ሁሉ ለሀይማኖትም ወሳኝ ነው፡፡ እና እስኪ ትንሽ ቢያንስ የተማረውን ሙስሊም አሳትፉ፡፡ አቅጣጭ ቀይሱ፡፡ ለሀገር ልማት አጋዥ የሁኑ አያሌ ነገሮች መስራት ይቻላል፡፡ አዲሱ ስራ አስፈጻሚ ላይ ተስፋ መጣል የመጡበትን መንገድ መርሳት ቢሆንም ከድሮው አሰራር እቅፍ ለመውጣት መሞከር ከቻሉ አሁንም የሙስሊሙ እውነተኛ ተወካይ ለመሆን መሞከር ይቻላል፡፡ ብዙ የሀይማኖት እውቀት ባይኖረኝም በሰማይ ቤት አካውንት እንዳለን አምናለሁ፡፡ ተስፋ አልቆርጥም፡፡ ታሪክና ፈጣሪ መዝግበው እንደሚይዙንም አለመርሳት ነው፡፡

ውድ አንባቢያን የመጅሊሱ የቅርብ ሰዎች ብዙ ሳይዘጋጁና ሳይጨነቁ ይህን ሁሉ መረጃ ሰጥተውኛል፡፡ ለግል ደህንነታቸው ሲሉም የተወሰነውንም ዝርዝር ነገር እንደማይነግሩኝ ገልጸውልኛል፡፡ ይሁንና በሂደቱ ያወቅኩት ነገር ቢኖር በመጅሊሱ የተማሩ ሰዎች በዙሪያው እንዳሉትና ያሉትን ሰራተኞች በአግባቡ ቢጠቀም ውጤታማ የመሆን እድል እንዳለው ነው፡፡

ይሁንና ሰራተኞቹ  የሰላም መምሪያ ግን ለሰራተኛውና ለስራ አስፈጻሚ አለመገናኘት ብዙ ሚናዎችን ከመጫወት አይቦዝንም ብለው ያሙታል፡፡ አዲሱ ስራ አስፈጻሚ ይህን ሰላም መምሪያ ካለው ሚና ለማቀብ ደፍሮ ሊያፈርሰው ይችላል የሚል ተስፋም እንደሌላቸው ነግረውኛል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይህን ጽሁፍ ለሚያነብ ሙስሊምም ሆነ ሌላ ወገን የመጅሊስ ጉዳይ የሙስሊሞች ብቻ ሳይሆን የሁላችንም በመሆኑ ለመስተካከሉ የቻልነውን ሁሉ ጥረት እንድናደርግ እላለሁ፡፡

—–
ጸሐፊውን ለማግኘት በኢሜይላቸው  (mkahlid9@gmail.com) ይጻፉላቸው፡፡
የዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጂ በዞን ዘጠኝ እንዳይነበብ በታገደው የዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ይገኛል፡፡

  • facebook
  • twitter
  • rss
  • print
  • bookmark
  • email
 Abbay media.com

Civil Society Crackdown in Ethiopia

by Laetitia Bader

HRW_typo_logo650

Human Rights Watch | On 1 January 2013, Ethiopia took up its seat on the United Nations Human rights Council. The uncontested election – Africa put forward five countries for five seats – has raised some eyebrows, given the country’s own poor rights record. Elected member countries are obliged to ‘uphold the highest standards in the promotion and protection of human rights’. Yet, in Ethiopia, hundreds of political prisoners languish in jails where torture is common and a crackdown on the media and civil society is in full swing.

The blogger Eskinder Nega exemplifies the fate of those who dare to speak out. Eskinder was arbitrarily arrested and jailed following the controversial 2005 elections. After his release from prison two years later, he was placed under ongoing surveillance and banned from publishing. Then, in 2011, he was rearrested, convicted in an unfair trial under Ethiopia’s broad terrorism law, and sentenced to 18 years in prison.

Since the 2005 elections, the human rights situation in Ethiopia has progressively deteriorated: the government has shut down legitimate political avenues for peaceful protest; and opposition leaders, civil society activists and independent journalists have been jailed or forced to flee. Furthermore, state-driven development policies, including large-scale agricultural development and ‘villagization’ programmes, have seen communities forcibly relocated from their traditional lands, without adequate consultation or compensation, to villages that lack basic services

The ruling party has passed a host of laws attacking the media and civil society, including the Charities and Societies Proclamation that has made independent human rights work in the country almost impossible. The state has frozen the assets of the last two remaining groups – the leading women’s rights organization, the Ethiopian Women Lawyers Association EWLA) – which has provided free legal aid to over 17,000 women – and the Human Rights Council (HRCO).

Ethiopia’s security forces have in recent years been implicated in crimes against humanity and war crimes in the Somali and Gambella regions. But Ethiopia has not only succeeded in stemming criticism at the national level but also internationally. And the worsening human rights situation has not dampened donors’ enthusiasm, even when their assistance has harmed democratic institutions or minority populations. Ethiopia’s friends and partners in the region should use its three-year term on the Council to put its rights abuses under the international spotlight. They should use debates to urge the Ethiopian government to release all political prisoners, lift unlawful restrictions on civil society and the media, and stop blocking visit requests byUNhuman rights experts.

Laetitia Bader is a researcher for the Africa division at Human Rights Watch.

Source: Human Rights Watch

Abbaymedia.com

ጠ /ሚያችን ሃይለማርያም ራሳቸው እሰረኛ “እስረኛ የለም” ይላሉ

ጠ /ሚያችን ሃይለማርያም ራሳቸው እሰረኛ “እስረኛ የለም” ይላሉ

Hailemriam the puppetመቸም አገራችን ካለችበት ምስቅልቅል  የምትወጣ መስሎን  በትግሬ  ነጻ  አውጭ ግንባር  የሚመራው ኢህአዲግ  በጠመንጃ  ሃይል ስልጣን ከያዘበት ማግስት ጀምሮ “የዘመነ መሳፍንት” ጊዜ አስተሳሰቡን ትቶ አለም የደረሰበት ዲሞክራሲያዊና መልካም አስተዳደር  ደረጃ ላይ ባንደርስ እንኩዋ ጠጋ ብለን ለዘመናት ታፍኖና በችጋር ተቆራምዶ የኖረው ሕዝባችን የሚሰማውን አየተነፈሰ የለፋበት ሳይቀነስብት እየተቁኣደሰ ለመኖር የሚችልበት ስርእት እንዲዘረጋ ያልወተወትነው አልነበረም፡፡

ሰሚ ጠፋና አልሆነለንም፡፡ አምባገነኑ ወያኔ/ኢሀአዲግ እያድር ጥሬ እንጂ ሊበስል አልቻልም፡፡ ለውትወታችን  የስጠው ምላሽ ሲሻው በጡቻ፡ አላያም በጠመንጃ እንዲያም ሲል አይን ባወጣ ፍርደ-ገምድል ፍርድ ሕዝባችንን ማሰቃየት ብቻ ነው፡፡ ሕዝባችንንም ካለአንዳች እረፍት ሲያሰቃይ እነሆ ሁለት አሰርተ-አምታት አገባዶ ሶስተኛውን ተያይዞታል፡፡

መለስ በጌታ ፍርድ ከስልጣናቸው ሲወገዱ ግራ-ገቡን ሃይለማርያም ደሳልኝን ሳይወዱ ተክተው ሲሄዱ ነገሩ ሳይገባን ከእነበረከት ስምኦን ይልቅ ደስ ያለን እኛ ነበርን። የሁዋላ ሁዋላ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ በመንጣጣቱ”ፍዝዝ ብለን እያየን  መደነቅ ብቻ ሳይሆን የባሰ ግራ ተጋብትንም ነበር፡፡ ለካ  ነገሩ ወዲሀ ነው፡፡  እኛ ደስ ብሎን የነበር ሃይለማርያም ለዘመናት ተጨቁኖ ይኖር ከነበረው የደቡብ ክፍለ-አገራችን ከሆኑ ወገኖቻችን አብራክ ወጥተው ከፍተኛ የስልጣን እርክን  የደረሱ ስለመስለን ነበር፡፡ “ጉድ ወደ ሁዋላ ነው” እንዲሉ ሁዋላ ስንረዳው የእነ በረከት ደስታ ከኛ የተለየ ነው፡፡ እነርሱ የተደሰቱት ሙሽራው ሲወጣ ከተሻማው ዳቦ ባገኙት ጉራጅ ኖሮዋል። የተደበቀው በበለጠ የተከሰተልን ደግሞ ሃይለማርያም እራሳቸው በየመድርኩ እየወጡ የአምባገነኖቹ የእንግዴ ልጅ መሆናችውን  በጽናት ሲያረጋግጡ ነበር፡፡

ታዘው ይሆን ወይንም ወደው ባናውቅም   አንዴ ወጥተው የመለስ ተቀጥያ እንጂ ለኢትዮጵያ የራሳቸው ወጥ  የሆነ  የመልካም  አስተዳደር ራእይ እንደሌላቸው በገሀድ ነገሩን፡፡ አስተዳደራ ቸው የሚመራው በጀማ እንጂ እርሳቸው ከአፈ-ቀላጤነት በስተቀር ምንም ሚና እንደሌላቸው ሲያስታውቁን ደግሞ እንደዚሀ እራሱን ያዋረደ መሪ አይተን ስለማናወቅ  በጣም ደነገጥን፡፡  የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ተብለው የመጨረሻው የስልጣን ጣሪያ ላይ ሲቀመጡ ሚኒስትሮቻቸውን የማያስሾሙ የጦር መኮንንኖቻቸውን  የማያስመድቡ ከሆነ የእኝህ ሰው ጠቅላይ ሚኒስትርነት እምኑ ላይ ነው እያልን ተጨነቅን፡፡ ለመሆኑ አንድ ስህተት ቢፈጠር በህሊናችን ያሉበትን ሁኔታ እያወቅን በሃላፊነት ልንጠይቃቸው ነወይ?እያልን ዋለልን፡፡ በአጠቃላይ   በከፍተኛ የመንግስት አስተዳደር ደረጃ ለሚከስቱ ጉዳዮች ሁሉ በሃላፊነት የምንጠይቀው አሳጡን፡፡

የዚህ አይነቱ ክስተት ሲፈጠር በታሪካችን የመጀመሪያ ልዜ እይደለም፡፡ በቀዳማዊ ሃይለስላሴ  ካቢኔ ጠቅላይ ሚ/ር የነበሩት አክሊሉ  ሃብተወልድ የንጉሱ ልጅ የነበሩት ልእልት ተናኘ ወርቅ    የበላያቸው ድብቅ ጠቅላይ ሚ/ር እንደነበሩ የንጉስ ነገስቱ መንግስት በወሎ ሕዝባችን ላይ ባደረሰው ጥፋት የተነሳ  ሲጠየቁ በእየዬ ማጋለጣቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡  ያ እየዬ ጩኽታቸው ግን አምሽቶ የመጣ ስለነበር ከሞት አላዳናቸውም፡፡ ተረሽኑ፡፡ ችግራቸውን በወቅቱ ለሕዝብ አሳውቀው ዞር ብለው በነበር ምናልባት ከክሱ በዳኑ ነበር። አላደረጉትም። በዚህም የተነሳ እኛን የመሰል የነጻነት ታጋይና ያገር ባለውለታ ሳንቀብራቸው ቀረን፡፡ ታሪካችንም ተበላሽ፡፡ ጠቅላይ ሚ/ር እክሊሉ ችግራቸውን በወቅቱ ያልተጋፈጡት አንድም ከማን አለብኝነት እምበለ በለዚያም በስንት ርኩቻ ያገኙትን ሰልጣን ላለማጣት ይሆናል፡፡  ክቡር ልጅ ሚካኤል እምሩ ግን ይህን አላደረጉትም፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን በደርግ ካቢኔ ጠቅላይ ሚ/ር ሆነው ስርተዋል፡፡ ነገር ግን የደርግ አካሄድ አስቸጋሪና የማይታረም መሆኑን ሲረዱ በዘዴም ሆነ በልምምጥ ራሳቸውን አገለሉ፡፡ ስለሆነም ከሕረተስቡ ተቀላቅለው በክብር ኖሩ፡፡

እኛ ሃይለማርያምን ልናከብራቸው እንፈልጋለን። የጠቅላይ ሚ/ር አክሊሉ እድል እንዲገጥማቸው አንሻም። ልንቀብራቸው እንፈልጋለን። እርሳቸው ግን መንገዱን መምረጥ አለባቸው፡፡ የአክሊሉን ወይንም የሚካኤልን። የመለስን እመርጣለሁ ካሉ ግን ጠባቸው ከሕዝብም፡ ከእግዚአብሄርም ከራሳቸውም ጋር መሆኑን ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ ስለ ፓለቲካ እሰረኛም ስናነሳ ቁጥሩን ከራሳቸው አንድ ብለው ቢጀምሩ መልካም ነው። ሃይለማርያም “እራሳቸው የፖለቲካ እስረኛ ሆነው “የፖለቲካ እስረኛ የለም ይላሉ፡፡ ይህ የተለመደ የመለስ አባባል ነው፡፡ እንዴት ራሳቸውን ማወቅ ይሳናቸዋል? ይልቁንስ እውነታውን ከመካድ እራሳቸውን ከእስር ቢያስፈቱ ይሻላቸዋል።

ጸሃፊው ዘነበ ታምራት በኢሜይል አድራሻቸው ztamira@yahoo.com ላይ ይገኛሉ

 Abbaymedia.com

የፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም አዲስ መጽሀፍ ግምገማ

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ

ኢትዮጵያ ሀገሬ፣ ሞኝ ነሽ ተላላ፤ የሞተልሽ ቀርቶ፣ የገደለሽ በላ!

በሰሎሞን ተሰማ ጂ. (semnaworeq.blogspot.com)

በሐምሌ 1955ዓ.ም የወጣው መነን መጽሔት፣ (7ኛ ዓመት፣ ቁ.10 ዕትም፣ በገጽ 27) ላይ እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቶ ነበር፤ “እኚህ የ33 ዓመት ወጣትProfessor Mesfin Woldemari is an Ethiopian peace activist and philosopher በአባታቸው ጎንደሬ፣ በእናታቸውም ይፋቴ ሲሆኑ፣ በአማርኛ የበሰሉ በመሆናቸው የመናገርና የማስረዳት ስጦታ ያላቸው ትሁት ወጣት ናቸው፤” ሲል ይገለጻቸዋል፡፡ ለጥቆም የወጣቱን መስፍን ወልደ ማርያም ሦስት ሐሳቦች እንደሚከተለው አስፍሮት ይገኛል፡፡ “ማናችንም በዘመኑ የምንገኝ ትውልዶች በምናውቀውና በተማርነው ችሎታችን ተሽለን ተገኝተን፣ የዚህ ዕድል ተሣታፊ ለመሆን የሚጓጉ ወንድሞቻችንን ለመርዳት የምንቦዝንበት ትርፍ ጊዜ እንዲኖረን አያሻም፡፡ …. እኔ ካወቅሁ ሌላው እንዲያውቅ መድከም የለብኝም ማለት፤ በዚህ ዓለም ላይ ብቻዬን በአንድ እግሬ ቆሜ እኖራለሁ ብሎ እንደማሰብ የሚቆጠር ነው፡፡….የሰው ሁሉ የተፈጥሮ ባሕርዩ ለየቅል መሆኑ ሲታመን፤ ይህን የየግል የነበረውን መንፈስ ሰብስቦ ለማስተማር ያለው የመምህሮች ድካም በቀላሉ የሚገመት ባይሆንም፣ ይህን ከመሰለው ጋር መሰለፍም ለመምህራኖች የታሪክ ክብር ነው፡፡” ልብ በሉ ይህ ንግግር የታተመው የዛሬ ሃምሳ ዓመት ገደማ ነው፡፡ ወጣቱ መስፍንም የገባውን ቃል ለመፈጸምና ለዕውቀት “የሚጓጉትን ወንድሞቻችንን ለመርዳትና ለማስተማር” በወሰነውም መሠረት፣ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ቃልና ተግባር ተስማምተው ሲገኙ ሁሌም ያስመሰግናሉ፤ ያስከብራሉም፡፡

ከመጋቢት 2002 ዓመተ ምህረት ጀምሮ፣ ይኼንን መጽሐፍ ሲያሳትሙ አራተኛ ሥራቸው/መጽሐፋቸው ነው፡፡ በሠላሳ ሦስት/አራት ወራት ውስጥ አራት ደህና-ደህና መጽሐፍትን ጽፎ ማሳተም ከባድ ተግባር ነው፡፡ በተለይም ሩጫው ከዕድሜና እርጅና ይዞት ከሚመጣው ጫና ጋር ሲታሰብ ከባድ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል፡፡ ኧረ ለመሆኑ፣ ሰማኒያ ሲደመር (80+)….ምናምን ሆኖ በሣምንታዊ ወይም በየሁለት ሳምንቱ የሚወጣ ጋዜጣና መጽሔት ላይ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ማነው? ማነው ወቅታዊ ሁኔታዎችን ዕለት-በዕለት ተከታትሎ ከዕድሜና ከኑሮው/ከተሞክሮው እንዲሁም ከተማረው ትምህርት ጋር መርምሮና ፈትሾ ለሕዝብ እምነቱንና እውነቱን ባደባባይ የሚጽፈው? ማነውስ በጡረታ ዘመኑ፣ “አገዛዝን አልፈራም” ብሎ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ጉባኤ/ድርጅት ከተባባሪዎቹ ጋር አቋቁሞ ገዢዎችን የሚሞግተው? ብዙዎች፣ ገዢዎችን ፈርተው፣ በፍርሐትም ተሸብበውና በተስፋ መቁረጥ ተሰንገው ዳር ቆመው ሲመለከቱ (ይሳካም-አይሳካም) ከሕዝብ ጎን/ጋር ተሰልፎ በሦስቱም ሥርዓቶች የተገኘው ሊቅ ማነው?(ያ ሰው በሚያዝያ 16 ቀን 1922ዓ.ም እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ የተወለደው-ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ነው፡፡)

ፕሮፌሰር መስፍን ዋናው የጥናት መስካቸው ጂኦግራፊ ነው፡፡ በ1945ዓ.ም ወደ ሕንድ ሀገር ሔደው ከፑንጃብ ዩኒቨርሲቲ በፍልስፍናና በጂኦግራፊ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡ በ1948ዓ.ም ወደኢትዮጵያ ተመልሰው በትምህርት ሚኒስቴር-በጆኦግራፊና በካርታ አነሣሥ ኢንስቲቱት ውስጥ ለጥቂት ወራት ሢሠሩ እንደቆዩ፤ በዚያው ዓመት አሜሪካን አገር በሚገኘው የክላርክ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት ዓመታት ያህል በጂኦግራፊ ትምህርት የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡ በ1950ዓ.ም ወደኢትዮጵያም ተመልሰው፣ ወደአሜሪካን ከመሔዳቸው በፊት ይሠሩበት በነበሩበት መሥሪያ ቤት ተመድበው ለሁለት ዓመታት ያህል አገልግለዋል፡፡ ከዚያም፣ በ1952ዓ.ም ወደቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተዛውረው የጂኦግራፊና የካርታ አነሣሥ ትምህርን በማስተማርና በዚሁ ክፍል ኃላፊ በመሆንም እያገለገሉ ናቸው፤” ሲል ጅማሯቸውን ያትታል፡፡ በጣም ውሱን በሆነ አኳኋን የጻፉትንና መጠነኛ ማሳያ ተደርጎ ሊቆጠር የሚችለውን “አገቱኒ፡- ተምረን ወጣን (መጋቢት 2002ዓ.ም) የጻፉትን የራሳቸውን መጽሐፍ ማንበቡ የተሻለ መረጃ ስለሚሠጥ አንባቢያን እርሱን እንዲያነቡት ይመከራሉ፡፡

Mesfin Woldemariam (also spelled Mesfin Wolde Mariam; born 1930) is an Ethiopian peace activist and philosopher

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

ወደዋናው ጉዳያችን እንመለስ፤ ይኼኛው የፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም መጽሐፍ፣ “እንጉርጉሮ” ብለው (1967ዓ.ም) ያሳተሙትን የግጥም መጽሐፍ ሳይጨምር፣ በአማርኛ ከጻፏቸው መጽሐፍት ውስጥ ሰባተኛው ነው፡፡ በተመሳሳይም፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሰባት መጽሐፍትን በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ጽፈዋል፡፡ በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ አገር ጥናታዊ መጽሔቶች ላይ የታተሙ ከሃያ በላይ ጥናቶችን አሳትመዋል፡፡ እጅግ ብርቱ፣ ከማጥናትና ከመመራመር የማይታቀቡ አዛውንት ናቸው፡፡ በቀጥታ፣ ለግምገማ ወደመረጥነው እርዕሰ ጉዳይ እንግባ፡፡ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ፤(ኢትዮጵያ ሀገሬ፣ ሞኝ ነሽ ተላላ፤ የሞተልሽ ቀርቶ፣ የገደለሽ በላ!) ይሰኛል፡፡ በታኅሣሥ 2005ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሟል፡፡ ጠይቄ እንደተረዳሁት ከሆነ፣ መጽሐፉ በደርግ ዘመን ተጀምሮ በርካታ ጥናቶችና ምርምሮች ሲደረጉበት የቆየ መጽሐፍ ነው፡፡ ዋጋው ብዙ አይደለም፤ በ45.00 የኢትዮጵያ ብር ገዝቶ ቁምነገር መዝረፍ ያጓጓል፡፡ መጽሐፉ-ካርታዎችን፣ ፎቶዎችንና አባሪዎችን አጠቃሎ 238 ገጾች አሉት፡፡ ገጽ በገጽ ሲገልጡት በአዳዲስ ሃተታዎች የታጨቀ ነው፡፡ የተለየ ጥልቀትም አለው፡፡ (ምናልባትም፣ ይህንን መጽሐፍ በአንድ ክፍል ብቻ መገምገሙ በቂ ላይሆን ይችላል፡፡ እንዲያውም “ንፉግነት ነው!” ቢባል አያስገርምም፡፡)

ያም ሆኖ፣ የምንገመግመው መጽሐፍ እጅግ ከፍ ያለ ዋጋ የሚሰጠው፤ የፖለቲካ-ጂኦግራፊ፣ የታሪክ፣ የትምህርት፣ የማህበራዊ ሳይንስና የባህል/ስነ-ሰብዕ ይዘት ያለው ሥራ ነው፡፡ስመ-ጥር የጂኦ-ፖለቲካ ሊቅነታቸው ብቻ ሳይሆን፣ በተደጋጋሚ ያሳዩት አገዛዞችን የመዳፈር ችሎታቸው በዚህም መጽሐፍ ውስጥ ተንፀባርቋል፡፡ ስም እየጠሩና ማስረጃ እያጣቀሱ ብዙዎቹን የታሪክ “ሊቃውንት” እና “ታሪክ ሠሪዎች” ተችተዋል፡፡ ከታሪክ ሊቃውንቱ መካከል፣ ከፕሮፌሰር ስርግው ሐብለ ሥላሴ በስተቀር ከሠላ ትችታቸው ያመለጠ የለም፡፡ ፕ/ር ስርግውን ግን፣ “የኢትዮጵያን ታሪክ በዘመናዊ መልክ በኢትዮጵያዊ መሠረት ላይ ለመትከል ብዙ የሠራና እጅግ የሚጥርም ሰው ነበር፤” ሲሉ ያመሰግኗቸዋል (ገጽ 89)፡፡

ከታሪክ ሠሪዎቹም ነገሥታት መካከል በተራ አፄ ቴዎድሮስ፣ አፄ ዮሐንስና አፄ ምኒልክ ሚዛን አንስተዋል፡፡ አፄ ቴዎድሮስን “መድፍ የሠራ” ብቸኛ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ ካሉ በኋላ፣ “ያንንም መድፍ መቅደላ ተራራ ላይ ማውጣቱም ራሱ ሌላ ትልቅ ሥራ ነው፤” ሲሉ ይገልጧቸዋል(ገጽ 165)፡፡ አፄ ዮሐንስንም በተመለተ፣ “የቴዎድሮስን ፈለግ ተከትለው፣ ከውስጥ አምባ-ገነኖችና ከውጭ ወራሪዎች ጋር የመረረ ትግል እያካሔዱ፣ ከአፄ ቴዎድሮስ የተሻለ ውጤት አሳይተዋል፤” ሲሉ ተገቢውን ክብር ይሠጧቸዋል(ገጽ 166)፡፡ ስለአፄ ምኒልክም ሲያወሱ፣ ቄሣራዊያን ኃይሎች ኢትዮጵያን ሊቃረጧት ባሰፈሰፉበት በዚያን የመከራ ወቅት፣ የኢትዮጵያን ሀገረ-መንግሥት ከመደምሰስ “የረዳው የአፄ ምኒልክ አመራርና የዘመኑ የኢትዮጰያ ሕዝብ የመንፈስ ወኔና አልበገር ባይነት የሰጣቸው ኃይል ነው” ብለዋል(ገጽ 168)፡፡ አክለውም፣ “አፄ ምኒልክ በንጉሠ ነገሥትነት ዘመናቸው ሁለት ጠባዮችን በጉልኅ አሳይተዋል፡፡ አንደኛ፣ ለጎበዝና ለጀግና ክብርን የሚሰጡ በመሆናቸው ሁልጊዜም በጀግኖችና በታላላቅ ሰዎች የተከበቡ” መሪ ነበሩ-ይሏቸዋል፡፡ “ሁለተኛም፣ ከመቅደላ ወደሸዋ ሰመለሡ ከወጋቸው ከአቶ በዛብህ ጀምሮ እስከ እምባቦ ጦርነት ላይ ለንጉሥ ተክለ ሃይማኖት እስካሳዩት” የመንፈስ ልዕልና ድረስ፣ “የወጋቸውንም እንኳን በክብር የመያዝና በእርሳቸው አመራር አምኖ ጠቃሚ የሚሆንበት ዕድል የመስጠት ችሎታ ነበራቸው፤” በማለት ከፍ-ያለ ዋጋ ይሠጧቸዋል(ገጽ 166-7)፡፡

“አፄ ምኒልክ አጠፏቸው የሚባሉት ነገሮች በብዛት፣ አፄ ዮሐንስ ንጉሠ ነገሥት ሳሉ በአፄ ዮሐንስ ትዕዛዝና አውቅና የተፈፀሙ እንጂ በአፄ ምኒሊክ ጉልበተኛነት ወይም ግፈኝነት የተፈፀሙ አይደሉም!” ሲሉ ይከራከራሉ፡፡ “የደቡቡ፣ የምስራቁም ሆነ የምዕራቡ የአፄ ምኒሊክ ዘመቻዎች ያለአፄ ዮሐንስ እውቅናና ትዕዛዝ የተደረጉ አልነበሩም፡፡ ሆኖም ግን፣ ታሪክ ያላነበቡት ወያኔዎችና ሻዕቢያዎች፣ እንዲሁም የቄሣራዊያን የታሪክ ቅጥረኞች ሆን ብለው ታሪካችንን ለማክሸፍና ዋጋ ለማሳጣት ሲሉ፤ እየተቀባበሉ የደንቆሮ ለቅሷቸውንና ሙሾአቸውን ያወርወዳሉ፡፡” ይህንን የመሠለ መሰሪ የተቀነባበረ የፖለቲካ ቁማር የሚጫወቱ ሁሉም፣ ዞሮ-ዞሮ አንድ ዓላማና ግብ ያላቸው ኃይሎች ናቸው፤ እርነሱም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ለዘመናት የተገነባ የሕዝቦች ሕንፃ ለማፍረስ የሚፈልጉ-ከሐዲዎች ናቸው-ብለዋል (164-169)፡፡ ጀግናውን ራስ አሉላ አባነጋንም አውስተው፤ “የሥራቸውን ዋጋ ሳያገኙ ሞቱ፤” ሲሉ ይቆጫሉ(ገጽ 114)፡፡

ከነዚህ የታሪክ ሠሪዎችና ከፕ/ር ስርግው በስተቀር፣ ብዙዎቹን ኢትዮጵያዊያን በአራት ዓምዶች ስር ሰድረው ይተቿቸዋል፡፡ የመተቻ መስፈርቶቹንም ተጠቅመው የአንባቢያንን ሕሊና ለማንቃት ያደረጉት ጥረት የሚደነቅ ነው፡፡ እዚህም እዚያም ተሰባጥረው የሚገኙትን ነጥቦች “መክሸፍ፣” “ታሪክ”፣“ድንበርና-ወሰን”፣ እንዲሁም “ቄሣራዊ ኃይሎች” ባሏቸው አኃዞች አደላዳይነት “የኢትዮጵያን ታሪክና ደንቃራዎቹን”፣ በፈርጅ-በፈርጁ ሊያደራጁ ጥረት አድርገዋል፡፡ ሙከራቸውም ፈሩን ያለቀቀ ነበር፡፡…. የአንድ ትምህርት ዘርፍ ጥገኛ ለመሆን ስላልፈለጉም፤ ከታሪክም፣ ከፖለቲካም፣ ከስነ-ቃልና ከባሕላችንም ውስጥ ጠቃሚ የሆኑትን ሃሳቦችና ነጥቦች ተፈላልገው በማጠናቀር ከመጀመሪያው አስከ መጨረሻው የአንባቢን ቀልብ ለመግዛት ተፍጨርጭረዋል፡፡

ይሁንና፣ ምንም እንኳን የገለልተኛነት መንገድን ለመውሰድ ቢጥሩም፣ የስሜታቸው ተከታይ ከመሆን አላመለጡም፡፡ በገጽ-64 ላይ እንደጠቀሱትና ለስቬን ሩቢንሰን በ1969ዓ.ም እንደነገሩት፣ ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው “ኢትዮጵያ ስትደማ አብሬ እየደማሁ፤ እንዴትስ ስሜት አይኖረኝም?” በማለት ራሳቸውን ያጋልጣሉ፡፡ “የኢትዮጵያ ታሪክና ቄሣራውያን ምሁራን” የሚለው ምዕራፍ ሥርም፣ የደራሲውን የሃሳብ አካሄድና የአስተሳሰብ ፈለግ በይበልጥ የሚመሰክር ነው፡፡ “ታሪክ የሁነቶች ድርደራ አይደለም፤ የተዋናዮቹን ‘አስተሳሰብና ስሜት፤ ጨዋነትና ብልግና’ የሚሉትን፤ ‘ክብርና ውርደት’ የሚሆንባቸውንም የጨምራል፤” ይላሉ(ገጽ-63)፡፡ አያይዘውም፣ ታሪክ የሁነቶች ገለፃ/Descriptive/ ብቻ አይደለም፤ ስነ-ሰብዕ/Ethnographic/ ጭምርም መሆን አለበት-የሚሉ ይመስላል፡፡ የኢትዮጵያን ታሪክ ከውጭ ሆነው የሚያጠኑት የውጭ አገር ዜጎችም ሆኑ በውጭ አገር ዩኒቨርሲቲዎች መሽገው የሚያጠኑት ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን የታሪክ “ሊቆች!” – “ስለኢትዮጵያ ምንም ስሜት የላቸውም፡፡ ስለሆነም፣ ኢትየጵያ ስትደማ አብረው አይደሙም፡፡” በተለይ-በተለይ፣ “በአውሮፓም ሆነ በአሜሪካን የሠለጠኑት የታሪክ ባለሙያዎች፣ ለኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያውያን ቋንቋ ከመጻፍ ይልቅ፣ በባዕዳን ቋንቋዎች ለባዕዳን ነው የሚጽፉት” ብለዋል(ገጽ-65)፡፡ በዚህም አተያይ፣ እንደፕ/ር “ባሕሩ ዘውዴ ያለው፣ አንድ አስተማሪው ያስታጠቀውን ጉዳይ” ይዞ “የማያውቀውን ነገር ይጽፋል” ሲሉ አብጠልጥለዋል(ገጽ-8/9)፡፡ ቀጥለውም፣ “ዱሮም ሆነ ዛሬ የታሪክ ጸሐፊዎቻችን ትኩረታቸው በእንጀራቸው ላይ ነው፤” ሲሉ ዜና መዋዕል ጸሐፊዎቹንም ሆነ ዘመናዊዎቹን የታሪክ “ጸሐፊዎች” ያለርሕራሔ ተችተዋል (ገጽ-76)፡፡

ዘመናዊዎቹ ታሪክ ጸሐፊዎችና አስተማሪዎቻቸው የፈለጉትን ያህል ቢሳሳቱም እንኳን፤ በገጽ 54 እና 56 ላይ እንደገለጹት፤ “የኢትዮጵያ ታሪክ እየተጠናከረ መሔድ የጀመረው፣ ዋናዎቹ የኢትዮጵያ ታሪክ ጸሐፊዎችና አስተማሪዎች የውጭ አገር ሰዎች” መሆን ከጀመሩ በኋላ ነው-በማለት እውቅና ይሰጣሉ፡፡ ሆኖም ይላሉ መስፍን፣ “ለምን ነጮቹ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚያደርጉት ጥናት ስለዘር፣ ስለቋንቋና ስለባህል ብቻ ሊሆን ቻለ?” በማለት ይጠይቁና፣ ምክንያቱም ግልጽ ነው-ይላሉ፡፡ “እኛን እንደፈለጉ አድርገው ሊቀርጹን የሚያደርጉት” ቄሣራዊ ሙከራቸው አካል ነው፤ ሲሉ በአጽንዖት ይገልፃሉ፡፡ “እኛን እንደጥቁር ሰሌዳ፣ እነርሱንም እንደነጭ ጠመኔ ያለ ባሕርይ ሠጥተን መቀበላችንንም፤” በብርቱ ይቃወማሉ፡፡ ትልቆቹን ቄሣራውያን ምሁራን፣ ለምሳሌ እንደትሪንግሃምና ዶናልድ ሌቪን የመሳሱትን በስም ጠቅሰው፣ “ብዙ የመረጃ ምንጮቻቸውን ሳይመረምሩ፣ የፋሺስቶችን ትምህርትና ልዩ ቄሣራዊ ዓላማ አነግበው/ስላላቸው፤” የኢትዮጵያን ታሪክ አጎደፉ፤ ሲሉ አማረዋል(ገጽ-59-60)፡፡ በሶማልያና በቄሣራዊ ፓስፖርትና ቪዛ የሚምነሸነሹት እነበረከት-አብ ሀብተ ሥላሴም ኢትዮጵያን መካዳታቸው ሣያንስ፣ የሀሰት ታሪክ መጻፍን “የእንጀራቸው” መብያ አድርገውታል ሲሉ ይንገበገባሉ(ገጽ-179)፡፡

የፕ/ር ታደሰ ታምራትንና የፕ/ር መርድ ወልደ አረጋይንም ጥናቶች አንድ ባንድ አያወሱ፣ ከገጽ 90-103 ባሉት ሃተታዎች ውስጥ በእጅጉ ይሞግቷቸዋል፡፡ “ለኢትዮጵያ ልዩ ተፈጥሮና ባሕል፤ በተለይም የኢኮኖሚውና የኑሮው ሁኔታ የፈጠረውን የፖለቲካና የአስተዳደር ሥርዓት በመመርመር-ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ታሪክ የሚያገኙአቸውን የፖለቲካ ሁነቶች መሠረት አድርገው ባለመነሳታቸው፤ ስሕተት ላይ ወደቁ” ብለዋል(ገጽ-88)፡፡ በተለይም፣ ታደሰ ታምራት “ስቴትና ኢምፓየር (State and Empire) የሚሉትን ከአውሮፓ ባሕልና ታሪክ መድረክ የፈለቁ፣ ተለዋዋጭና የተወሳሰበ ታሪክ ያላቸው ሐሳቦች” ለኢትዮጵያ ተጠቅመው፣ ለቄሣራውያን አስተሳሰብ መሣሪያ ሆኑ-ብለው ተከራክረዋል(ገጽ-90)፡፡ በተጨማሪም፣ ፕ/ር ታደሰ መጽሐፍ “ከሣርና ከቅጠሉ በስተቀር፣ የኢትዮጵያን ሁኔታ ሁሉ በሃይማኖት ሚዛን ይለካል፤” ያም ስሕተት እንደሆነ አሳይተዋል(ገጽ-91)፡፡ ፕ/ር መርድንም አንስተው፣ ስለኢትዮጵያ ወሰንና ዳር-ድንበር ሲያጠና “አልቫሬዝ ስለደጋው የኢትዮጵያ ወሰን የጻፈውን “ተረት ነው” ብሎ አጣጥሎ፣ ለቆላማው ኢትዮጵያ ሲሆን ግን ያለማመንታት ይቀበለዋል፡፡ ያንንም የተዋሰው ከማርጀሪ ፐርሃም ሀሳብ ነው፡፡” በመሆኑም፣ ‘መርድ ሳያውቀው፣ ለቄሣራውያን ተንኮል የድምጽ ማጉያ ሆነ!’ ለማለት ይቃጣቸዋል(ገጽ-101/2)፡፡

ወደ“መክሸፍ”ና ስለኢትዮጵያ ታሪክ አከሻሸፍ ያወሱትን ለማጤን እንሞክር፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን “ከሻፋ” ነገሮች በሦስት ከፋፍለዋቸዋል፡፡ እነርሱም፤ ጨርሰው የከሸፉ(ገጽ-19)፣ በመክሸፍ ላይ-ያሉ(ገጽ 11-18)፣ እና እስከዘመናችን ድረስ ያለከሸፈ(ገጽ-10) በማለት፡፡ ያለከሸፈው “ለነፃነትና ለክብር በመስዋዕት” መሆኑ ብቻ ነው፡፡ በተረፈ፣ በገጽ-26 ላይ እንዲህ ይላሉ፤ “በኢትዮጵያ በኳስ ጨዋታው ሳይቀር መክሸፍ ጎልቶ ይታያል፤ በረጅም ርቀት ሩጫም ቁልቁለቱን የጀመርነው ይመስላል፡፡ ከባሕር ጠለል አካባቢ የሔደው ሶማሊያዊው ሞ ፋራህ፣ ደገኞቹን (ከደጋማው የኢትዮጵያ ክፍል የሔዱትን ሯጮች) ቀደማቸው፡፡ መክሸፍ ባህላችን መሆኑ ግዴታ ነው እንዴ?!” ለነገሩማ፣ “ከሸፈ ወይም እከሌ አከሸፈው እንላለን እንጂ፣ እኛ ራሳችን ከሽፈን-አከሸፍነው አንልም!” ሲሉ ይገሥፃሉ(ገጽ 29-31)፡፡

በመጨረሻም፣ ከበድ ያለና ተገቢ ማሳሰቢያ ለአንባቢያኑ ያቀርባሉ፡፡ በገጽ 104 ላይ ስለሦስቱ የቄሣራውያን ኃይሎች ግዛት ለማስፋፋት የሚጠቀሙባቸውን ዘዴዎች ተንትነው ሲያበቁ፤ በገጽ 145 ላይ ደግሞ ለምን ቄሣራውያን የኢትዮጵያን ለመግፋትና ወሰኗን ለመማጥበብም እንደፈለጉ የሚያሳዩ “ሦስት መሠረታዊ ጥቅሞቻቸውን” ከበቂ ማብራሪያና ማስረጃዎች ጋር ያቀርባሉ፡፡ እነዚህንም፣ የቄሣራውያንን ሴራዎችና ተንኮሎች ሳንረዳ የምንቀር ከሆነ፣ በውጫዊው የቄሣራውያን ግፊትና ሴራ መክሸፋችን እንደማይቀር ያስገነዝባሉ፡፡ “በመሆኑም፤” ይላሉ ፕ/ር መስፍን፣ “በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ መክሸፍ ለብዙ ምዕተ-ዓመታት” ቦታ የያዘ መሆኑን ገልጸው(ገጽ-8)፤ “ከ1928ዓ.ም ወዲህ ግን፣ የክሽፈቱ ዓይነት የተለየ ሆኗል፡፡ ስለዚህም፣ ማኅበረሰባዊ ችግሮችንና ለሥልጣን የመስገብገብ ጉዳዩንም አስከፊ አድርጎታል”(ገጽ-12) ይላሉ፡፡ ስለሆነም፣ “የሥልጣን ምንጭ ሙሉ-ለሙሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆኖ፣ ሰው ለሰው የሚገዛበት ሥርዓት እስካልፈረሰና፣ ዜጎች በሕግ ፊት እኩል መብትና እኩል ግዴታ ያለባቸው መሆኑ በተግባር እስካልተረጋገጠ ድረስ” መክሸፋችን አይቀሬ መሆኑን ጠቁመዋል(ገጽ-201)፡፡

እስቲ ደግሞ ስለመጽሐፉ የቋንቋ አጠቃቀም ጥቂት ነጥቦችን እናንሳ! “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ፤”፣ በቃላት አሰካክና አደራደሩ ስርዓትን የተከተለ ነው፡፡ ቃላቱ፣ ለአጫፋሪነትና ለአዳማቂነት ፈፅሞ ልሰፈሩም፡፡ ቀልብን ገዝተው መደመጽሐፉ ማብቂያ ያንደረድራሉ፡፡ ሆኖም፣ እዚህም-እዚያም የፊደል ግድፈቶች ታይተዋል፡፡ ለምሳሌም ያህል፣ በገጽ-53 ላይ “ሲጀምር” የሚለውን “ሺጀምር”፤ በገጽ-78 ላይ “ያተረፉ” የሚለውን “ያተረፋ”፤ በገጽ-88ም ላይ “ሁነቶች” የሚለውን “ሁነትች”፤ በገጽ-93 ላይም “አማርኛው” የሚለውን “አማራኛው”፤ በገጽ-127 ላይም “መሀከል” መሆን ሲገባው “በሀከል”፤ በገጽ-168ም ላይ “ኢትዮጵያ” የሚለውን “ኢጥዮጵያ”፤ እና በገጽ-194 ላይ ደግሞ “የሚተላለፍ” ለማለት “የሚታላለፍ” የሚሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከሁሉም-ከሁሉም ግን፣ በገጽ-9 ላይ የወጣው ስም ስህተት ሊታለፍ አይገባውም፡፡ ፊታውራሪ “ተክለ ሐዋሪያት ተክለ ማርያም” መባል ሲገባው፣ ልጅየው “ግርማቸው” ያለቦታቸው ተተክተዋል፡፡ ከገጽ-12 እስከ 14 ባሉት አንቀጾችም ውስጥ፣ ዓ.ም(ዓመተ-ምህረት)ና ምዕተ-ዓመት(ም.ዓ – የሚባል አጠቃቀም ካለም ነው፣) ተዛንቀዋል፡፡ መጽሐፉ በድጋሚ ሲታተምም፣ እነዚህን የፊደልና የስም ግድፈቶች አርሞ እንደሚወጣም እምነቴ ነው፡፡

ማጠቃለያ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገራት ላሉት አንባቢያን፣ መጽሐፉ እንደልብ ገበያ ላይ ይገኛል፡፡ ዋጋ የሚፍቁና የሚደልዙ ወገኖች እንዳያጭበረብሯችሁ፣ ዋጋው አርባ አምስት/45/ ብር ብቻ መሆኑን በድጋሚ ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡ በውጭ አገራትም ያላችሁ፣ በሃያ/20/ ዶላር ገዝታችሁ ለማንበብ ወደ ኢሳት-ስቶር http://ethsat.com/store/ ጎራ በሉ፤ ታገኙታላችሁ፡፡ መጽሐፉን “ይፋ ባልሆነው ማተሚያ ቤት” ያሳተሙትን, ፕ/ር መስፍንና ተባባሪዎቻቸውን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ እንዲሁም፣ መጽሐፉን በመተየብና የአርትኦቱም ስራ ያገዙትን ሁሉ፣ በአንባቢያኑ ስም “ክብረት ይስጥልን!” ልላቸው እመዳለሁ፡፡ (የሳምንት ሰዎች ይበለን!)

ሰበር ዜና – ዐቃቤ መንበሩ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ መጠየቃቸው ተሰማ

ሐራ ዘተዋሕዶ

  • ዕርቀ ሰላሙንና የፓትርያሪክ ምርጫውን በተጓዳኝ እንዲካሄድ ለማስወሰን ታስቧል
  • ‹‹ዕርቀ ሰላሙ ይቅደም›› የሚሉት አባቶች አቋምና ብዛት እየተጠናከረና እየጨመረ ነው
  • የሰላምና አንድነት ጉባኤው ለቅዱስ ሲኖዶሱ ደብዳቤ ጽፏል
  • ከ4ው ፓትርያሪክ ጋራ ፊት ለፊት መወያየት ቀጣይ የመነጋገሪያ ነጥብ ነው ተብሏል

ቅ/ሲኖዶስ በነገው ዕለት አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ለመቀመጥ በሚዘጋጅበት ዋዜማ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ መጠየቃቸው ተሰማ፡፡ ዐቃቤ መንበሩ ጥያቄውን ያቀረቡት ለመንግሥት አካል በጻፉት ደብዳቤ ነው ተብሏል፡፡ ደብዳቤው የተጻፈው ሁለት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት (አቶ ኣባይ ፀሃዬ እና ዶ/ር ሽፈራው ተክለ ማርያም) በሳምንቱ መጨረሻ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪኩ ቢሮ ተገኝተው ከተወያዩ በኋላ መኾኑ ተገልጧል፡፡

ጥያቄው ስለቀረበበት ምክንያት የዜናው ምንጮች ሲያስረዱ÷ ‹‹ቅድሚያ ለዕርቀ ሰላሙ›› በሚል ለስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ የሚደረገውን ዝግጅት በሚቃወሙ ብዙኀን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ‹‹ዕርቀ ሰላሙ ከፓትርያሪክ ምርጫው ጋራ ግንኙነት የለውም፤ ሁለቱም በተጓዳኝ/በትይዩ ሊከናወኑ ይችላሉ›› በሚሉ ጥቂት ነገር ግን ተጽዕኖ ፈጣሪ ናቸው በሚባሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በተያዘውና ከዕለት ወደ ዕለት እየተካረረ በመጣው ፍጥጫ ሳቢያ ነው ብለዋል፡፡

ከቅ/ሲኖዶስ አባላት አልፎ የአገልጋዩና ምእመኑ አጀንዳ የኾነው የቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት እንዲሁም ቀጣይ አመራር ጉዳይ ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ አቋም በማራመድ የሚታወቁትን ብፁዓን አባቶች (ለመጥቀስ ያህል÷ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልንና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን) ሳይቀር በተለያየ ጎራ ያሰላለፈ መኾኑ ለጉዳዩ ክብደት በአስረጅነት ተጠቅሷል፡፡

የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ ነገ፣ ጥር 6 ቀን 2005 ዓ.ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያሪኩ ሲጀመር የምልአተ ጉባኤው ቀዳሚ አጀንዳ የዕርቀ ሰላሙ ቀጣይነት እንደኾነ ተነግሯል፡፡ በነገው አስቸኳይ ስብሰባ ከኅዳር 26 – 30 ቀን 2005 ዓ.ም በዳላስ ቴክሳስ በተደረገው ሦስተኛው ዙር ጉባኤ አበው ላይ የተሳተፈው የዕርቀ ሰላም ልኡክ የደረሰበትን ‹‹የውሳኔ ሐሳብና ተያያዥ ጉዳዮች በሪፖርት መልክ አቅርቦ›› /የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ ለስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ እንደገለጹት/ መወያየትና ከጥር 16 – 18 ቀን 2005 ዓ.ም በሎሳንጀለስ ካሊፎርኒያ ለሚካሄደው አራተኛውና ወሳኙ ዙር ጉባኤ አበው ቀጣይ የመነጋገሪያ አቋሞችን ማስቀመጥ ዋነኛው ቁም ነገር ነው፡፡

የዜናው ምንጮች ባደረሱት ጥቆማ÷ በአንዳንድ የምልአተ ጉባኤው አባላት ሊነሡ ከሚችሉ የመነጋገሪያ አቋሞች መካከል÷ ‹‹ከአራተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ጋራ ገጽ ለገጽ ተገናኝቶ መወያየት›› እንደ ነጥብ ሊያዝ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ ‹‹በመንግሥት ጫና ከመንበረ ፕትርክና ተባረርኹ፣ ተበደልኹ ያሉ እርሳቸው ብቻ ናቸው፤ ድርድሩም መካሄድ የሚገባው ከእርሳቸው ጋራ ነው፤›› የሚሉ የቅ/ሲኖዶሱ አባላት÷ በውጭ የሚገኙ ሌሎች አባቶች በደል ደርሶብናል ባለማለታቸው ዋናው ድርድር ከአራተኛው ፓትርያሪክ ጋራ ብቻ መኾን እንደሚገባው ይከራከራሉ፡፡

በሹመት ቀደምትነት ያላቸውና በአምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የተሾሙት አባቶች በተደራዳሪነት የማይሳተፉበት የዕርቀና ሰላም ውይይት በዳላስ ቴክሳስ ለሦስተኛ ጊዜ ለማካሄድ ዝግጅት በሚደረግበት ሰሞን÷ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪኩ ወደ አሜሪካ ተጉዘው ከአቡነ መርቆሬዎስ ጋራ እንዲገናኙ ቀርቦ የነበረው ሐሳብ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ናቸው በሚባሉ የቅ/ሲኖዶሱ አባላትተቃውሞ የተነሣ ሳይሳካ መቅረቱ ታውቋል፡፡ ዐቃቤ መንበሩ ከአራተኛው ፓትርያሪክ ጋራ አድርገውታል የተባለው የስልክ ውይይት በይፋ መታወቁም ተጽዕኖ ፈጣሪዎቹን ደስ እንዳላሰኛቸው ነው የተነገረው፡፡

የዕርቀ ሰላም ልኡኩ ወደ አሜሪካ ከተጓዘም በኋላ የልኡካኑን አባላት በአካል ወይም በስልክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ጋራ ለማገናኘት በአቡነ መልከጼዴቅ ተደርጓል የተባለው ሙከራ ‹‹ከተልእኳችን ውጭ ነው›› በሚል ሳይሳካ መቅረቱ ተዘግቧል፡፡ በአንጻሩ አሁን ‹‹ጠባችን ይኹን ድርድራችን ከአቡነ መርቆሬዎስ ጋራ ብቻ ነው›› የሚለው የመነጋገሪያ አቋም ሐሳብ መነሻ የጉዳዩን ተከታታዮች አጠያይቋል፡፡ ጥቂቶቹም የሐሳቡ መነሻ የሰላምና አንድነት ጉባኤው መግለጫና እነርሱ ‹‹ወገንተኝነት ይታይበታል›› የሚሉት አካሄዱ እንደኾነ በመግለጽ ‹‹በዚህ አደራዳሪ አንቀጥልም፤ ከቀጠልንም ድርድሩ ከአቡነ መርቆሬዎስ ጋራ ብቻ ይኾናል›› መባሉን ይጠቅሳሉ፡፡

አነስተኛ ቁጥር ባላቸው ጳጳሳት የተደገፈውና በመንግሥትም ዘንድ ተይዟል የተባለው አቋም÷ ዕርቀ ሰላሙ ከፓትርያሪክ ምርጫው በተጓዳኝ እንዲካሄድሲኾን ይኸው አቋም የነገው አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ውሳኔ ኾኖ እንዲወጣ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ መኾኑ ታውቋል፡፡ ‹‹ዕርቀ ሰላሙ ተፈጽሞ በአንድነት ወደ ስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ እንሂድ›› አልያም ‹‹አራተኛው ፓትርያሪክ በሕይወት እያሉ መንበሩ በእንደራሴ ይጠበቅ›› የሚሉትን ‹‹የዕርቀ ሰላሙ ይቅደም›› ደጋፊዎች አማራጮች መንግሥት እንደማይቀበለው የገለጹት ምንጮቹ÷ የዕርቀ ሰላም ሂደቱ ሠምሮ ዕርቅ ከተፈጸመ በኋላ መንግሥት ዋስትና ወደ አገር ለሚገቡት አባቶች ደኅንነት ዋስትና እንዲሰጥ በውጭ ባሉት አባቶች ዘንድ በቀጣይ መደራደሪያነት ተይዟል የተባለውንም ሐሳብ እንደማይቀበለው ተናግረዋል፡፡ በምንጮቹ ግንዛቤ ይህ የመነጋገሪያ ሐሳብ ‹‹አጀንዳውን ከጳጳሳቱ ወደ መንግሥት ለማዞርና ውዝግቡን ለመቀጠል የታቀደበት ነው፡፡››

የሰላምና አንድነት ጉባኤውን ተሰሚነት ባላቸው ሽምግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች አጠናክሮ የዕርቅና ሰላም ሂደቱን መቀጠል ሌላው የአስቸኳይ ስብሰባው አጀንዳ ነው፡፡ የሰላምና አንድነት ጉባኤው ለቅ/ሲኖዶሱ ጽ/ቤት ደብዳቤ መላኩ የተገለጸ ሲኾን ስለ ደብዳቤው ዝርዝር ይዘት የተገለጸ ነገር ባይኖርም በምልአተ ጉባኤው ሊታዩ የሚገባቸውና ቀጣዩን የሰላም ጉባኤ የተመለከቱ ሐሳቦች ሊይዝ እንደሚችል ተገምቷል፡፡

የሰላምና አንድነት ጉባኤው የፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙን በመቃወም ላወጣው የቅ/ሲኖዶሱ የዕርቀ ሰላም ልኡካን ‹‹ይቅርታ እንዲጠይቅ›› መጠየቃቸውና ይቅርታ ካልጠየቀና አካሄዱን ካላስተካከለ በአደራዳሪነቱ አብረው እንደማይሠሩ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል፡፡ አሁን የሰላምና አንድነት ጉባኤው በላከው ደብዳቤ ስላወጣው መግለጫ ማብራሪያ የሰጠበት፣ ለዕርቅና ሰላሙ መልካም ፍጻሜ ሲባልም ቅ/ሲኖዶሱን ይቅርታ የጠየቀበት ሊኾን ይችላል ተብሏል፡፡ ወደ መንበረ ፓትርያሪኩ እንዳይገቡ የታገዱትንና ከአገር በግዳጅ እንዲወጡ የተደረጉትን ሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዓለማየሁንና ሌላውን ልኡክ የተመለከተ ጉዳይም ሊነሣበት እንደሚችል ተጠብቋል፡፡

ታኅሣሥ 8 ቀን መጽደቁ ተዘግቦ የነበረው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ ደንብ አከራካሪ አንቀጾችም በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ ዳግመኛ ለውይይት እንደሚቀርብ ተገልጧል፡፡ ‹‹ሕጉ መጽደቅ ያለበት ምልአተ ጉባኤው በአግባቡ በተጠበቀበት ኹኔታ ነው›› በሚል ለዳግመኛ እይታ ተጋልጦ ሳለ÷ ለዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ ከመስጠት አኳያ በአወዛጋቢ ውሳኔ እንደተሠየመ የተነገረለት የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ ቅቡልነት አከራካሪ ሊኾን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴው አባላት ጥር 8 ቀን 2005 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ተገኝተው ሥራቸውን እንዲጀምሩ ማሳሰቢያ የተሰጠበትን ደብዳቤ አግባብነት መፈተሽና የደብዳቤውን መሻር የሚያስከትል ውሳኔ እንዲወሰን መሟገት በጥብቅ የሚያስቡበት ብፁዓን አባቶች ቁጥር ጥቂት አለመኾኑም የስብሰባውን ሂደት ከባድ እንደሚያደርገው ተገምቷል፡፡

ECADF.COM

ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት በጀግናዉ አበበ ገላዉ ላይ በወያኔ ስርአት የተቃጣዉን የግድያ ሴራ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ጥር 10/2013 ዓ/ም (እኤአ)

Ethiopian National Transitional Councilበቅርቡ ጀግናዉ አበበ ገላዉን ለመግደል በህወሀት/ኢህአዴግ የተጠነሰሰ ሴራ በአሜሪካ በFBI መጋለጡንና ተጠርጣሪዎቹም መያዛቸዉንና ምርመራ ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል። ይህን እጅግ አሳፋሪ ተግባር የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት አጥብቆ ያወግዛል። የፋሽሽቱና ዘረኛዉ ህወሀት/ኢህአዴግ ስርአት ምርጫ 97ትን ተከትሎ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተረቆ በአዉሮፓ አሜሪካና በሌሎች ሃገሮች ለሚገኙ የኢትዮጽያ ኤምባሲዎች በሚስጢር የተሰራጨው ባለ 52 ገጽ በአለም ዙሪያ የሚገኙ ተቃዎሚዎችን ለመምታትና ለማዳከም ያወጣዉን እቅድና ዝርዝረ ጉዳዮችን የያዘ የስርአቱ ሰላዮች ሰነድ ሾልኮ በመውጣቱ ለኢትዮጵያኖችና ለአለም አቀፍ ህብረተሰቡ ይፋ መሆኑ የታወሳል። ስርአቱ በሀገር ውስጥ የሚያደርገውን የሽብርተኝነት ተግባራት በጎረቤት ሀገሮች በማስፋፋት በኬንያ፤ በሱዳን፤ በጅቡቲና ዩጋንዳ በሚገኙ ኢትዮጽያዉያን ስደተኞችና ተቃዋሚዎች ላይ የሚሰራቸዉ ያሸባሪነት፤ የገዳይነትና፤ ከስደተኞች ካምፖችና ከያሉበት አፍኖ በመዉሰድ በኢትዮጵያ እስር ቤቶች እንዲሞቱ የማድረግ ተግባራቶች ያለምንም ተጠያቂነት እየቀጠለ እያለ፤ በታላቋ አሜሪካን ሀገር እጅግ አሳፋሪና ፍፁም የአሸባሪነትና የእብሪት ተግባር ለመፈጸም ሙከራ አድርጓል። ይህም ተግባሩ የስርአቱን ማንነት በገሀድ ያጋለጠ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ሽፋን በቢሊዮኖች የሚቆጠር የግብር ከፋዮች ገንዘብ ለሚያፈስለት የአሜሪካን ሀገር መንግስት ያለዉን ንቀት በተግባሩ ያረጋገጠ ነው። ለነገሩ ወያኔ/ህወሃት በግድያና፤ የዘር ማጥፋት ፤ እኩይ ተግባሩ በአሜሪካን መንግስት እኤአ ከ 1975 እስከ 1991 ዓ/ም ድረስ በአለም አቀፍ የሽብርተኛ ድርጅትነት መመዝገቡን ለምናስታዉስ ይህ አጸያፊ ተግባሩ ሊገርመን አይገባም።

ስለነጻነት የጻፉ ጋዜጠኞችን ሽብርተኛ ናቸዉ በማለት ለረዥም አመታት ያሰረ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ለመብታቸዉ የሚታገሉትን የሙሰሊም ወገኖቻችንን በሽብርተኝነት ከፈረጀ፤ በደቡብ፤ በአኝዋክ፤ በኦሮሞና በአማራ ህዝብ ላይ የእልቂት ተግባሮችን እራሱ ፈጽሞ የገደላቸዉና ደማቸዉን ያፈሰሰዉ በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ኢትዮጵያዉያንን ሽብርተኞች እያለ ከሚፈርጅና ህጻን ልጆችን ከሚገድል ስርአት ምን የተሻለ ተግባር ይጠበቃል? ዋናዉ ቁም ነገር ይህ በአሜሪካን ሀገር የተቃጣዉ የንቀት እኩይ የግድያ ሙከራ የአሜሪካን መንግስትን ሰለወያኔ ስርአት ያለዉን አመለካከትና ፖሊሲውን እንደገና በጥሞና እንዲያጤን ማስገደድ አለበት በማለት ባፅንኦት እንለምናለን። ሁላችንም ተቃዋሚ ሀይሎችና በዉጭ ሀገር የምንገኝ ሀገርና ወገን ወዳድ ዜጎችም ይህንን አለም አቀፋዊ የሽብርተኝነት ተግባር የአሜሪካን መንግስት ከስር መሰረቱ በማጣራት አስፈላጊዉን እርምጃ እንዲወስድ ያላሰለሰ ግፊትና ጫና እንድናደርግና የስርቱን ሰላዮች በማጋለጥ መረጃዎችን ለሚመለከተው ከፍል እንድናስተላልፍ እንጠይቃለን። በዚህ አጋጣሚ ከጀግናዉ አበበ ገላዉ ጋር የምንቆምና ለእሱ ያለንን ክብር በድጋሚ በማረጋገጥ ለወያኔ ስርአት የምናስተላልፈዉ ግልጽ መልእክት በአበበ ላይ የተቃጣዉ የፈሪዎች እኩይ ተግባር ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ጀግና አበበዎችን በቅርቡ በመፍጠር ይህንን ጨካኝ ስርአት ጠራርጎ ከሀገራችን ለማስወገድ በቆራጥነት እንደምንታገል እናረጋግጣለን።

በጋራ ትግላችን ገዳዩንና ዘረኛዉን ስርአት እንስወግዳለን።

የሽግግር ም/ቤቱ አመራር

የተቃዋሚዎቻችን አበሳ (ከፋሲል አያሌው)

ከፋሲል አያሌው

የአንድ ሃገር ህዝብ በራሱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ ፣ተፈጥሮዋዊም ሆነ በሌሎች አዊዎቹ ላይ የተሰማውን፣ የታየውን፣ ቅር ያለውን፣ እንዲሁም ያደነቀውን ነገር ያለምንም Ethiopian flag (Alemayehu G. Mariam)ተጽዕኖና ፍራቻ መግለጽ ካልቻለ ሰው በመሆኑ ብቻ የተፈቀደለትን በነጻነት የማሰብ፣ የመጻፍና የመናገር ተፈጥሮዋዊ መብቶቹ የተነፈጉት ብቻ ሳይሆን በተለይም በዚህ በሃያ አንደኛው ክ/ዘመን የሰው ልጆች ከደረሱበት ዲሞክራሲያዊ መብቶች አንጻር ሲምዘን በከፍተኛ የነጻነት እጦት ከሚሰቃዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ እንዲመደብ ያደርገዋል:: ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች መከበር ዙርያ (ደረጃው በተለያየ መልኩ ይገለጽ ይሆናል) ለረጅም ጊዜ ያደረገችው ሙከራና አሁን ያለችበትን የዲሞክራሲና የሰብአዊ መብቶች ነጻነት ላስተዋለ ሲደረጉ የነበሩ ሙከራዎች ሁሉ በተለይም ሲፈራረቁባት የኖሩት ገዢዎቿ ሲተገብሩት የኖሩት ድንጋጌዎችና መመሪያዎች  በርግጥም ለህዝቦቿ ዘለቄታዊ የዲሞክራሲያዊ ጥቅም የቆሙ ሳይሆኑ ለገዚዎቿ የስልጣን ጥቅም ማስጠበቂያ መሳሪያ ሆነው ሲያገለግሉ የኖሩ ናቸው::

አሁን በስልጣን የሚገኘው የወያኔው ስርአት ላለፉት 21 አመታት የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ እያለ ጆሮአችንን ቢያደነቁረውም እሱ የሚለው የዲሞክራሲ ስርዓትና ትክክለኛው ዲሞክራሲያዊ ስርአት አራምባና ቆቦ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲያዊ ስርአትን በገመድ ለክቶና መጥኖ የናንተ መብትና ነጻነት እስከመጨፈር እንጂ የኔን ስልጣንና ጥቅም የሚነካ ከሆነ ቢላ ባንገቴ ካለን ሰነባበተ:: ለዚህም ይመስላል በተለይም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው የተቃውሞ  ድምጻቸውን ለሚያሰሙ ጋዜጠኞችም ሆነ  ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንም አይነት መፈናፈኛ እንዳያገኙ ሌት ተቀን ደፋ ቀና የሚለው::

ከዚህም የነጻነት እጦት እና ፍጹም አምባገነናዊ አፈናዎች መካከል እንደ አንድ ማሳያ የሚሆነው በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚያደርሰው ቅጥ ያጣ አፈናና በደል ሲሆን ዛሬ በወያኔው ስርዓት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚታዩት እንደ ተፎካካሪ ፓርቲ ሳይሆን ሃገርን ለማፍረስ እንደተዘጋጁ አሸባሪዎች ተደርገው ነው:: በጣም የሚያሳዝነውነና  አደገኛው አካሄዱ ደግሞ  ይህን እምነቱን ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያምንና እንዲቀበል ፍጹም ህገወጥ በሆነና ከዕውነት በራቀ ውንጀላ ተቃዋሚዎችን ለማጠልሸት የሚያደርገው እልህ አስጨራሽ ትግሉ ነው::

ስርዓቱ በተለይም ከ1997 ዓ.ም ወዲህ ተቃዋሚዎችን ለማዳከምና ለማጥፋት ፍጹም ኢ-ፍትሃዊና ህገወጥ በሆነ መልኩ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በሁለት ስትራቴጂዎች የተዋቀረ ነው::

የመጀመሪያውና  ቀጥተኛው ስትራቴጂ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን አሸባሪና እሱ ራሱ አሸባሪ ናቸው ብሎ ከፈረጃቸው ድርጅቶች ጋር ማያያዝ (ማዛመድ) ነው:: ይህንንም ለማሳካት የተቃዋሚ ድርጅት አባሎችን ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል የፈጠራ ክስ መወንጀል ሲሆን በጣም በሚያሳፍርና በሚያሳዝን መልኩ በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ ይቃወሙኛል ብሎ  ያሰባቸውን የነጻው ሚዲያ ጋዜጠኞችንም ይጨምራል:: እንግዲህ ይህ ስትራቴጂ የተወሰኑ ግለሰቦችን በአሸባሪነት ክስ ወደ  ዘብጥያ በማውረድ ብቻ የተገታ ወይም የተቋጨ ነው ብሎ  የሚያስብ የዋህ ይኖራል ብዬ አላስብም ዋናው አላማ አማራጭ ሚዲያና እውነተኛ መረጃ የተነፈገው  ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ በፍርሃት ውስጥ እንዲሸማቀቅና ለትክክለኛ የዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የሚኖረውን የጋለ የህዝብ ስሜት ጥቁር ጥላ እንዲያጠላበት የሚያደርግ እንጂ::

በዚህ ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔውን ስርአት የሃሰት ውንጀላ ጠንቅቆ የሚያውቅ ቢሆንም ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል እንዲሉ አንድ ለናቱ በሆነው የገዢው ስርአት ሚዲያ በየቀኑ የሚቀርበው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ  ህዝቡ ለተቃዋሚዎች፣ ለገዢው ፓርቲም ይሁን ለጠቅላላ የፓለቲካው ድባብ የሚኖረው ስሜት በፍራቻ፣ በጥርጣሬና ቀላል በማይባል ሁኔታ በፓለቲካው ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ውስጥ እንዲገባ የማድረግ ሃይሉ እጅግ ከፍተኛ  ነው::

ከዚህም በተጨማሪ ይህንን አደገኛ  አካሄድ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ተቃዋሚዎች ምንም አይነት ሃሳባቸውን የሚገልጹበት ነጻ ሚዲያ ሰለሌላቸው (ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ እንኳን እንደታፈነች ነች)በፈጠራ ክስ ለታሰሩ አባሎቻቸውም ሆነ ለደረሰባቸው የመልካም ገጽታ (Good Will) መበላሸት ማስተባበያ የመስጠትም ሆነ የመከላከል አቅሙ የሌላቸው መሆኑ ነው::

ሁለተኛውና ቀጥተኛ ያልሆነው ስትራቴጂ ከመጀመሪያው ስትራቴጂ ጋር የሚያያዝ ሲሆን ተቃዋሚዎች የመሰብሰብ፣ የመደራጀት ከህዝቡና ከደጋፊዎቻቸው ጋር የመገናኘትና የመቀስቀስ ስራዎቻቸውን እንዳይሰሩ በእጃዙርም ይሁን ባስ ሲልም በቀጥታ  የማፈንና የማሰናከል ተግባር ነው::

ይህንን እቅዱን እውን ለማድረግም ተቃዋሚዎች የመሰብሰቢያ አዳራሾችን እንዳያገኙ የተለያዩ  መሰናክሎችን መፍጠር፣ ራሳቸውን በገቢም ይሁን በተለያዩ ነገሮች ለማጠናከር የሚደረጉ ዝግጅቶችን ማስቆም፣ ማሰናከል፣ ተቃዋሚዎች የሚጠሩትን ሰላማዊ ሰልፎች አለመፍቀድ ወይም መሰረዝ፣ ምንም አይነት ነጻ ሚዲያ እንዳያገኙ መዝጋትና ሌሎችንም ዘዴዎች ይጠቀማል:፡

ሌላውን ሁሉ ትተን ዛሬ በጣም በሚሳዝን ሁኔታ በሃገራችን ለተቃዋሚዎች አንዱ ከባዱ ስራ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ማግኘት ነው:: ከተወሰኑ ጊዚያቶች በፊት ሰማያዊ ፓርቲ የመመስረቻ ጠቅላላ ጉባኤውን የሚያደርግበት አዳራሽ አጥቶ  ምን ያህል እንደተቸገረ  የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው::ዛሬ ለአንድ ህጻን ልጅ ልደት ለማክበር እንኳን አዳራሽ በሽ በሆነበት ሃገር ተቃዋሚዎች መሰብሰቢያ አዳራሽ አጥተው በሰው ቤት ጓሮ ዳስ እየጣሉ ግማሹ ተሰብሳቢ ጸሃይ እየበላው ነው ስብሰባቸውን የሚያካሂዱት:: የሆቴል ቤት ባለቤቶችና አዳራሽ አከራዮች በወያኔው ስርዓት በሚደርስባቸው ከባድ ተጸዕኖ ለተቃዋሚዎች አዳራሾቻቸውን ለማከራየት ፈቃደኞች አይደሉም::

የሃገሪቷ ሃብት በወያኔዎች እጅ በወደቀበት በዚህ ሰዓት ኣንድ የሆቴል ቤት ባለቤት አዳራሹን ለተቃዋሚዎች ቢያከራይ በህብረተሰቡ ውስጥ በዘሩት የተቃዋሚዎችን ስም በሀሰት የማጠልሸት ተግባር፣ ፍራቻና የስጋት ድባብ እንዲሁም ወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው በሆቴሉ ላይ በሚጀምሩት የሃሰት አሉባልታ ሆቴሉ ቀስ በቀስ ከገበያ ውጭ ሊሆን ስለሚችልና ምናልባትም ካስፈለገ ሆቴሉን እስከማሳሸግ ሊደርሱ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ነው ( በ1997 ዓ.ም ምርጫ ወቅት የመርካቶው ምዕራብ ሆቴልና ሌሎችም ሆቴሎች ተቃዋሚዎችን ትረዳላቹ ተብለው ታሽገው እንደነበር አይዘነጋም::)

እንግዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ በተቃውሞው ጎራ መሰለፍ እንደ ሃገር ጠላት የሚታይበት ደረጃ  ላይ መድረስ ብቻ ሳይሆን ባስ ካለም አሸባሪ የሚል ታርጋ አስለጥፎ ወህኒ ሊያስወረውር የሚያስችልበት ሁኔታ ኢትዮጵያውያኖችን በነጻነት የሚፈልጉትን ደግፈው ወይም ተቃውመው መኖር እንዳይችሉ ብቻ ሳይሆን በፍርሃት እንዲሸማቀቁና እንዲሰጉ ምክንያት ሆኗል:: ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የወያኔን ስርዓት መቃወም ስትጀምር በዚያውም ወደ እስር ቤት መቃረብህን ትረዳለህ:: አንተን ለመክሰስ የማስረጃ ጉዳይ ብዙም አያስጨንቅም በኢ- ማይልህ ላይ አንዳንድ መረጃዎችን ወይም ሞባይልህ ላይ ጥቂት መልእክቶችን መላክ (SMS) ማድረግ አንተን ዘብጥያ ለማውረድ በቂ ናቸው:: ( ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከወንድሙ ጋር በኢ-ሜይል ስለአባታቸው የህክምና ኦፕሬሽን (Operation) የተጻጻፉትን ኦፕሬሽን የሚለው ቃል ሌላ አላማ ተብሎ እንደማስረጃ የቀረበበት ሁኔታን ልብ ይሏል::)

በተጨማሪም እስር ቤቶቻችን ጥፋተኛን ወይም ወንጀል የሰራን ጸባዩን ከማረም ይልቅ በፓለቲካ አቋማቸው በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችንን ቅስምና ሞራል ለመስበር በእስረኞች ላይ የሚደረገው ግፍ ለማመን የሚከብድ ነው:: ለዚህም ይመስላል ሁለቱ ስዊድናውያን ጋዜጠኞች እንዲህ ያለ የእስር ቤት ግፍ በአሜሪካዊው ፊልም ዳይሬክተር ስቴቨን ስፒልበርግ ፊልሞች ላይ እንጂ በእውን በዚህ ምድር ላይ ያለ አይመስለንም ነበር ያሉት::

ቸር ያሰንብተን

Fasil_ayal@yahoo.com

ECADF.COM

የFBI መርማሪዎች አበበ ገላውን ለመግደል የታቀደ ሴራ አከሸፉ – በሴራው የተሳተፉ የህወሃት ሰላዮች ምርመራ እየተደረገባቸው ነው

ታህሳስ  ፴(ሰላሳ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ሰሞኑን አንድ የአሜሪካ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ (FBI) ግበረሃል ባለፈው ወር መባቻ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ወደ ቦስተን ለኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅትOne of TPLF spies who involved in Abebe Gellaw assassination attempt. በተጓዘበት ወቅት የግድያ ወንጀል ለመፈጸም በመዶለትና በማስተባበር ተግባር ላይ ተሰማርቶ የነበረና ለህወሃት መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚሰልል የሚጠረጠር ግለሰብ እና በግብረአበሮቹ ላይ ከፍተኛ ምርመራ መክፈቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጡ።

በአሜሪካ ሀገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ የሚኖረውና እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ የዘር ድርጅት አባል እና ሰላይ እንደሆነ የሚታመነው ግኡሽ አበራ በመባል የሚጠራው ይሄው ግለሰብ ጋዜጠኛውን ለመግደል በማሴር ሶስት የወንጀሉ ተባባሪ የሚሆኑ ግለሰቦችን  መመልመሉ ንና ድርጊቱን ለመፈጸም መሰናዶ ማድረጉን የFBI መሪማሪዎች  ደርሰውበት ሴራውን በግዜ ማክሸፋቸው ተረጋግጧል።

ግለሰቡ ወንጀሉን ከመፈጸሙ በፊት የተለዋወጣቸው መልእክቶች የFBI ወንጀል መርማሪዎች እጅ በመግባታቸው ሳቢያ እርሱና አብረው የሚኖሩ ሌሎች አራት ግለሰቦች ላይ ክትትልና ምረመራ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል። ከተባባሪዎቹ ጋር  የተለዋወጣቸው መልእክቶች ጋዜጠኛ አበበ ገላው ወደቦስተን የመሄዱን አጋጣሚ በመጠቀም በመሳሪያ ተኩሶ የመግደል እቅድ አውጥቶ ድርጊቱን ለመፈጸም ወይንም ለማስፈጸም ይንቀሳቀስ እንደነበር በግልጽ እንደሚያሳዩ ታውቋል።

የቦስተን ቅርንጫፍ FBI ቃል አቀባይ እና ልዩ መርማሪ ( special agent) የሆኑት ግሬግ ኮምኮዊች በምርመራው ሂደት  ላይ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ቢቆጠቡም፣ FBI እንዲህ አይነት ወንጀሎችን በ ቸልታ እንደማያልፍ ገልጸው በውጭ መንግስታት ሰላዮችም ሆነ ተወካዮች የሌሎችን ሰብአዊ መብቶችን በሚገፍ ህገወጥ ወንጀል የተሰማሩ ካሉ ኢትዮጵያዊያን በቸልታ ማልፍ እንደማይገባቸው እና በአካባቢያቸው ለሚገኙ የFBI  ቅርንጫፎች ጥቆማ እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበዋል። መርማሪው አክለውም FBI እንዲህ አይነቱን ጥቆማ በአግባቡ ትኩረት እንደሚሰጠው ገልጸዋል። “

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን የሰብአዊ መብት ረገጣ በመተቸት የሚታወቁት የጄኖሳይድ ወች ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ግሪጎሪ ስታንተን የግድያ ሴራውን ያከሸፉትን የFBI መርማሪዎች አድንቀው ፣ ህወሃት አሸባሪ ድርጅት መሆኑ ታውቆ ከኢትዮጵያ አልፎ በአሜሪካን ሀገር እንዲህ አይነት ወንጀል ሊፈጽም መንቀሳቀሱ በችልታ አይታይም ብለዋል።

በካምቦድያ በሰው ልጆች ላይ አስከፊ ሰቆቃና ጭፍጨፋ የፈጸሙ የካሜሩዥ ባለስልጣናትን ለፍርድ በማቅረብ አለማቀፍ እወቅና ያገኙት ፕሮፌሰር ስታንተን እንዲህ አይነቱ ወንጀል ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ለማድረግ ጥረት እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

ግኡሽ አበራን በቅርብ የሚያውቅ አንድ ኢትዮጵያዊ የቦስተን ነዋሪ፣ ግለሰቡ ከከፍተኛ የህወሃት ባልስልጣናት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለውና የቀድሞው አምባገነን መሪ የመለስ ዜናዊ አምላኪ እንደነበር፣ የእርሱ መዋረድና መሞት በጣም ካበሳጫቸው በአሜሪካ የሚኖሩ በርካታ የህወሃት ጀሌዎች አንዱ መሆኑን ገልጿል። በማከልም “ከሁሉ የከፋው ግለሰቡ በዘረኝነት ዛር የተለከፈ ስለሆነ ህወሃቶች እንዲህ አይነቱን ሰው ለእኩይ አላማቸው መጠቀማቸው የተለመደ ነው፣”  በማለት አስረድቷል::

ጋዜጠኛ አበበ ገላው “ህወሃት አሸባሪ የማፊያ ድርጅት መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት የነበሩብኝን የጽጥታ ስጋቶች ችላ ባለማለት ለሚመለከታቸው የህግ አስከባሪ አካላት ከማመልከት አልፌ የቤተሰቤንም ሆነ የራሴን ደህንነት ለማረጋገጥ ቀደም ብዬ እርምጃ ወስጃለሁ ወደ ፊትም እወስዳለሁ” ብሏል።

የFBI መርማሪዎች ወንጀሉ እንዳይፈጸም አስቀድመው እርምጃዎችን የወሰዱ ሲሆን ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ቦስተን ውስጥ ሮክስቤሪ በመባል በሚጠራው አካባቢ የሚገኘውን እና ግኡሽ አበራ ከሌሎች አራት ኢትዮጵያዊን ጋር በጋራ ይሚኖርበትን ቤት የበረበሩ ሲሆን፣  ወደ ሁለቱ የቤቱ ነዋሪዎች ስራ ቦታ ድረስ በመሄድ ምርመራ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።

የዳዉሮ ህዝብ አመጽ እንደገና ሊያገረሽ ነው

“እውነትና ፍትህ በሌለበት ሀገር ኑር አትበሉኝ!”

ረ/ሳጅን ሽታዬ ወርቁ ሺበሺ
የዳውሮ ዞን ፖሊስ ባልደረባ
(ዋካ ከስዊድን)

መግቢያ

የዳውሮ ሕዝብ የደረሰበትን የመልካም አስተዳደር እጦት፤ በአቅራቢያው ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት አለመቻል፤ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ሕዝቡ ለሚያቀርበው የመብትA memorial service for Yenesew Gebre የፍትህና የዴሞክራሲ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ያለመስጠት፤  በየወቅቱ በሚፈራረቁ የሥልጣን ተረኛ በሆኑት የህወሐት/ ደኢህዴን ካድሬዎች የግል ፍላጎትና ውሳኔ ብቻ የወረዳ ማዕከል እየተወሰነ ከመንደር ወደ መንደር በመዘዋወሩ የተነሳ ማሕበራዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት አለመቻል አበሳጭቶት ወደ አምጽ ማምራቱን በመዘርዘር ከዚህ በፊት በሦስት ክፍሎች ያዘጋጀሁትን ጽሑፍ ማስነበቤ ይታወሳል።

አሁንም በሕወሃት/ ደህዴን ካድሬዎች ተንኳሽነት የተነሳ የሕዝቡ ቁጣ እንደገና እያገረሸ መጥቷል። እስሩ ማንገላታቱ ከሥራ ማባረሩ ተጀምሯል። የሕዝቡ ጥያቄ የሚታወቅና ግልጽ ነው። ከሚዲያና ከካድሬዎች የሚነገረውን የሀገሪቱን  የኢኮኖሚ የልማትና እድገት ፕሮፓጋንዳ ባሻገር ድርሻውን ማግኘት ቀርቶ በአይኑ ለማየት አለመቻል፤ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለማግኘት ያለመቻላቸውና የሥራ አጥ ወጣቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እየናረ መምጣት፤ አንድ አርሶ አደር ወደ ወረዳ ማዕከል ለመድረስ ከአንድ ቀን በላይ ለሚፈጅ ጊዜ በእግሩ መጓዝ የግድ እየሆነበት ስለመጣና ይህም ስላሰለቸው፤ ያላግባብ እንዲርቀው የተደረገው የወረዳ ማዕከል በሚፈልገውና ወደ ሚቀርበው ሥፍራ እንዲዛወርለት ያቀረበው ተደጋጋሚ አቤቱታ ሰሚ ሊያገኝ አለመቻሉ፤ ጥያቄውን ለመንግሥት በየደረጃው  በተደጋጋሚ አቅርቦ መፍትሄ አለማግኘቱ ሕዝቡን በጣም አሳዝታል። በዚህም የተነሳ የዳውሮ ዋካን ሕዝብ ጥያቄ ያነገበው ጀግናው ሰማዕት መምህር የኔሰው ገብሬ በህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና የመልካም አስተዳደር እጦት በመቃወምና ድርጊቱን በማውገዝ ራሱን በእሳት በማቃጠል መስዋዕትነት መክፈሉ ይታወቃል። ይህም ሆኖ የዳውሮ ሕዝብ በደል መፍትሄ እስካሁን ሊያገግኝ አልቻለም።

የተቃውሞው እንደገና መቀስቀስ ምክንያት

ህወሐት/ ደኢህዴን በደቡብ ክልል በአንዳንድ ዞኖች ውስጥ በተደጋጋሚ የሚነሳበትን የህዝብ ተቃውሞ መቀነስ ስለሚችልበት ሁኔታ ተወያይቶ ነበር። በዚህ ውይይት ላይ በዋናነት የተነሳውና የታመነበት ነጥብ የተጨማሪ ወረዳ ጥያቄና የወረዳ ማዕከል ጉዳይ ሆኖ በውይይቱ ጎልቶ ወጣ። በመቀጠልም እንዴት አድርገው የህዝቡን ቁጣ ማርገብ እንደሚቻልና ምንም ተጨማሪ ወረዳ ሳይሰጥ ሕዝቡን የማሳመን ሥራ መሥራት እንደሚገባ ታምኖበት ለአፈጻጸም ለሚመለከተው የፖለቲካ ኃላፊዎች እንዲያስፈጽሙት ስልጠና ተሰጥቶ ወደ ሕዝቡ እንዲወርዱ ተደርጓል።

በውይይቱ ላይ በአንክሮ የተነሳው የቀድሞው ሰሜን ኦሞ ዞን ሥር የነበሩት ዞኖች መካከል የጋሞጎፋና የዳውሮ ዞኖች ህዝብ ጉዳይ ነበር። በዚህ መነሻነት የዞን አመራሮች ሕዝባቸውን የማሳመን ሥራ እንዲሰሩ የሚያስገድድ መመሪያ ለዞኑ የፖለቲካ አመራርች ይወርዳል። አመራሮቸ እንዲያስፈጽሙ ታዘዙ። በዚህ መነሻነት ነው እንግዲህ   በእስርና በእንግልቱ ሳቢያ ዝም ያለና ጊዜ የሚጠብቅ፤ ግን ውስጥ ውስጡን እየፋመና እየጋመ የነበረን የህዝብ ብሶት እንደገና ቀሰቀሱት።

የዳውሮ ህዝብ ያቀረበው የፍትና የመብት ጥያቄ በመሆኑ ከዛሬ ነገ ይመለስልኛል ብሎ በሚጠበቅበት ወቅት  መንግሥትና ገዢው ፓርቲ ጥያቄውን ለማድበስበስና ከሕዝቡ የተሻለ ለሕዝቡ አሳቢ በመምሰል ወረዳ ምን ያደርግላችኋል? ልማት ነው የሚያስፈልጋችሁ! ከልማትና ከወረዳ ምረጡ! ተጨማሪ ወረዳ አይጠቅማችሁም! የወረዳ ርእሰ ከተማ ቢርቅባችሁም ራቀብን አትበሉ! ዝም በሉ! እንዲያውም ፍትህ ፍለጋ ስንቅ ተሸክማችሁ በእግራችሁ ረጅም ሰዓት በመጓዛችሁደስ ደስ ሊላችሁ ይገባል! የሚል ስሜት ያዘላ አድራቂ ፕሮፓጋንዳ ሕዝቡን ለማወናበድ እየተሞከረ ይገኛል። የመንግሥት ሠራተኛው የህዝብ ልጅ እንዳልሆነና የሕዝብ በደልን የማይረዳ በማስመሰል ከሕዝቡ ሓሳብ በተቃራኒው ከአመራሮች ጎን እንዲቆም ለማድረግ በየወረዳው ካድሬ ተመድቦ ተግቶ እንዲሰራ ይደረጋል።

ካድሬዎች በሕዝቡ መካከል እጅግ የሚገርምና ፍጹም ኃላፊነት የጎደለው ሥራ ጀመሩ። የማረቃ ዋካ ወረዳ ዋና ከተማ ዋካ ይሁንልን የሚልን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የማይቻል መሆኑ ግልጽ ነው። በማሰር በማፈን በሐሰት በመክሰስና በመወንጀል በማስፈራራት ጥያቄውን ምላሽ እንዳያገኝ ማድረግ አምና ተችሏል። ይህ ማለት ግን ሕዝቡ ጥያቄውን ትቶታል ወይም መልስ አግኝቷል ማለት አይደለም። የወረዳው ማዕከል አያማክለንም የሚለውን የሕዝብ ጥያቄ ለማፈንና ምላሽ ላለመስጠት ሲባል ለዘመናት አብሮ የኖረንና ቤተሰብ የሆነውን የማሪና አካባቢውን ሕዝብ በመቀስቀስና በዋካ ከተማ ሕዝብ ላይ ለማነሳሳት መቀስቀስ ቀጠሉ።

የማረቃ ወረዳ ሕዝብ ከቆዳ ስፋቱና ከሕዝብ ቁጥር አንጻር እንዲሁም ጂኦግራፊያዊ አቀማመጡ የተነሳ ሁለት ወረዳ ሊሆን ይገባል የሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢነት ያለው ነው። በዚህ የተነሳ ዋካና ማሪ ሁለት የተለያዩ ወረዳዎች መሆን ይገባቸዋል የሚል ሐሳብ ይዞ መነሳት ነው የተጨማሪ ወረዳ ጥያቄ ማለት። ነገር ግን ቀድሞ የነበረን ወረዳ የወረዳው ማዕከል ይርቀናል አያማክለንም የሚልን ጥያቄ ለማፈን ሌላ ተገቢ ያልሆነ ቅስቀሳ ሕዝብ ውስጥ መርጨት ተጀመረ።

በምንም ዓይነት ሁኔታየኢትዮጵያ ዋና ከተማ ኬንያ ጠረፍ የሚገኝ ቀበሌ ሊሆን አይችልም። የትግራይ ክልል ዋና ከተማ ደሴ አልተደረገም። ዳውሮ ውስጥ ብትመለከቱ ግን ሁኔታው የተለየ ነው። የሎማዲሳ ወረዳ  ዋና ከተማ ገሳ ጨሬ ይባላል። ይህ አዲስ የተቆረቆረ ከተማ ያለው በአጎራባቹ የጌና ቦሳ ወረዳ ውስጥ ነው። የሎማ ዲሳ ወረዳ ሕዝብ የጠየቀው የወረዳችን ዋና ከተማ ከአጎራባች ወረዳ ወጥቶ ቢያንስ እንደቀድሞው ወደ ወረዳችን መሐል አካባቢ ተመልሶ በሚያማክለን ሥፍራ ይደረግልን ነው። ይህንን ጥያቄ አይቶና ሰምቶ መፍትሔ የሚሰጥ አመራር የለም።

በመንግሥት ውሳኔ የተጣመሩ ወረዳዎች ዳግም በመንግሥት ውሳኔ ተለያይተው ቀድሞ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሲደረግ የወረዳው ማዕከል ጉዳይ ወደ ሕዝቡ ወርዶ ውይይት ተደርጎበት ሊወሰን ሲገባ ይህ ሳይሆን ቀርቷል። ታዲያ ይሄ ስህተት የማነው? የሕዝቡ ነው ወይስ የአመራሩ ነው? ከዲሳ አካባቢ ለምሳሌ ቃኢ ጌሬራና ከዚያ ርቆ የሚኖር አንድ አርሶ አደር የወረዳውን አስተዳደር ፍለጋ አንድ ቀንና ከዚያ በላይ መጓዝ አለበት የሚል የወረዳና የዞን አመራር እውነት ለህዝቡ የቆመ ነው? አመራሩ ለምንድነው የሚመራውን ሕዝብ  የማይሰማው? እውነት አሁን የዲሳ አካባቢ ህዝብ ወደ ገሳጨሬ እንዲመላለስ ተገቢ አይደለም ያለ የመንግሥት ሠራተኛ ሊዋከብ ሊታሰርና ከሥራ ሊታገድ ተገቢ ነው?

የዳውሮ ህዝብ የወረዳ ማዕከል ለአቤቱታ ሲሄድ እንደ ዘመነ ምንሊክ ከቤቱ ስንቅ ቋጥሮ በእግሩ ከአንድ ቀን በላይ በመጓዝ ላይ ይገኛል። በሎማ ወረዳ ዲሳ አካባቢ አገልግሎት ማለት ጋሞ ጎፋ ዞን አዋሳኝ አካባቢየሚገኝ ቀበሌ ማለት ነው። ከዚያ ተነስቶ አንድ አርሶ አደር የወረዳው ማዕከል ወደተሰደደበት ሌላ ወረዳ ማለትም ጌና ቦሳ ወረዳ ከአንድ ቀን በላይ መጓዝ ግድ ይለዋል። ከዚያ በኋላ ተጨማሪ የመኪና ጉዞ አድርጎ ነው ገሳ ጨሬ የሚደርሰው። ይህ ነው እንግዲህ እውነቱ። ልዩነቱ ጥቂት የእግር ጉዞ ሰዓታት ልዩነት ካልሆነ በስተቀር ችግሩ በቶጫም ሆነ በማረቃ ወረዳዎች ተመሳሳይ ነው።

የሎማን ወረዳ ምሳሌ አነሳሁ እንጂ የቶጫ ወረዳም ቢሆን ተመሳሳይ ነው። ተርጫ አጠገብ ዋራ አካባቢ የሚኖርን አንድ አርሶ አደር ከጪ ድረስ ተጉዞ ፍትህ እንዲያገኝ ማስገደድ ምን ይባላል? ከጪ ኢሰራ ወረዳ አጠገብ ነው። ቀደም ሲል ኢሰራና ቶጫ ወረዳዎች እንዲጣመሩ በተደረገ ጊዜ ሁለቱን ወረዳዎች እንዲያማክል በሚል የተመሰረተ ከተማ ነው። ወረዳዎች ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሲወሰን የኢሰራ ወረዳ ከተማ ወደ ቀድሞው ማዕከል ሲመለስ ቶጫ ወረዳ ግን ቀደም ሲል ወደ ነበረበት ሥፍራ ሳይመለስ እዚያው እንዲቀጥል ተደረገ።

ይህ የሕዝብ ጥያቄ ሕብረተሰቡን ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ያስተባበረና እያጠናከረው የመጣ ሲሆን በገዢው ፓርቲ  ላይ ያለው ጥላቻ እያደገና እየከረረ መጥቷል። ለዚህ አስተዋጽኦ ያደረጉት ካድሬዎች ናቸው። ጀግናው የነጻነት ታጋይና ሰማዕት የሆነው መምህር የኔሰው ገብሬም “ የወረዳና የልማት ጥያቄ በማቅረቡ ወህኒ ቤት ሲያስሩት ጤነኛ የነበረ፤ ሲፈቱት ያልታመመና በሳምንቱ ራሱን በብሶት በቤንዚን አቃጠለ። በተቃጠለ በሦስተኛው ቀን ሞተና ከሞተ በኋላ ደግሞ ፖለቲከኞቹ እንዲሉት ታዘውና ተገደው እብድ ነበር አሉት።  የከፈለው መስዋዕትነት የዚሁ ትግል አካል ነበር።  ሌሎችም ለሚዲያ ያልበቁ በየወረዳው ፍትህና መልካም አስተዳደር እጦት ለችግራቸው መፍትሄ የሚሰጥ አካል አጥተው በተለያየ መንገድ ራሳቸውን ያጠፉ ሰዎች ቁጥራቸው ጥቂት አይደለም። ጊዜና ወቅት ሲፈቅድ የሚታወሱበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል።

እኛ አመራሮቹ የምንፈልገውን አስተጋቡልንም? የወረዳ ጥያቄ ለህዝቡ አይጠቅምም እያላችሁ ሕዝቡን ቀስቅሱልን! የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን ከገዢው ፓርቲ ጋር ሁሉም የመንግሥት ሠራተኛ መተባበር ግዴታው ነው! ይህን ካላደረግህ ጥገኛ ነህ!  በሌላ አባባል ህዝቡን ለማፈን መብቱን ለመንፈግ ተነስተናልና የመንግሥት ሠራተኛውም ከእኛ ይተባበር የሚል አስገዳጅ ውሳኔ ወስነው ለመንግሥት ሰራተኛው ጥሪ አደረጉ። ለዚህ ያልተባበረውን የመንግሥት ሠራተኛ ከሥራ በማገድ በማባረር በማሰር ወዘተ ለማስገደድና አንገቱን ለማስቀርቀር ብሎም ዝም ለማሰኘት ይቻላል በሚል እርምጃ መውሰድ ጀመሩ።ይህም የሕዝቡን ቁጣ እየቀሰቀሰው ይታያል። ረዳት ሳጅን ሽታዬ ወርቁም ታህሳስ 17/ 2005 ዓ.ም በገሳ ጨሬ ከተማ የተደረገው የመንግሥት ሠራተኞች ስብሰባ ላይ አካሄዱን ያወገዘው። ሕዝቡን ማፈን ተገቢ አይደለም ያለው።

የረዳት ሳጅን ሽታዬ ወርቁ ጥያቄና ላቀረበው ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ የተሰጠው ምላሽም የዚሁ ውሳኔ አካል ነው። በደረሰበት ጫናና እስራት የተነሳ ነው ነጻነት በሌለበት ሁኔታ ለመኖር መቸገሩን ያስታወቀው። ይህንን የሚያደርጉ ካድሬዎች ነገ ከሕዝቡ ጋር የሚኖሩ ናቸው ወይስ አይደሉም? እያልኩ ራሴን ስጠይቅ ምላሽ አጣለሁ። መንግሥትም የዳውሮ ሕዝብ ችግርን በመናቅ ጉዳዩ ለስልጣኑ ምንም የሚያሰጋው ስላልሆነ ይመስላል እስከዛሬ እያስለቀሰው ይገኛል።

ይህንን የዳውሮን ሕዝብ በደል ለማስቆም ትልቁ ጉልበት ያለው በመንግሥት እጅ መሆኑ ግልጽ ነው። መንግሥት ግን ስለ ሕዝቡ መበደል አልተገነዘበም ወይም ንቆታል አሊያም ከአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝና ዳውሮ ውስጥ ከፈጠራቸው አሽከሮቹ የሚቀርበውን የሐሰት መረጃ በመቀበል ሕዝቡን እንደጠላቱ ፈርጆታል ብዬ እገምታለሁ። በመሆኑም ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመለወጥና የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ የሚመለከታችሁ የሕብረተሰቡ አካላት የየድርሻቸውን መወጣት እንደ አለባቸው በማመን መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።

መልዕክት ለሕወሀት አመራሮች

የዳውሮ ሕዝብ በደል እጅግ ተባብሷል። ለመንግሥት ያቀረበው ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ያገኛል ብሎ ተስፋ ያደርግ ነበር። የሕዝቡ ጥያቄ በአጭሩ፤ የወረዳ ማዕከል ቦታ እንዲሆን የተመረጠው ሥፍራ የወረዳውን ሕዝብ አያማክልም፤ የወረዳ ዋና ከተማ ዝውውር የተወሰነውና የተከናወነው በአንድና ሁለት ካድሬዎች የግል ፍላጎትና መነሻነት ነው፤ ስለዚህ በሕዝቡ ፍላጎትና ሕዝቡን በሚያማክል ሥፍራ ይደረግልኝ ነው። ቅን መሪ ቢኖርና የመወሰን ኃላፊነት ከተመጣጣኝ ሥልጣን ጋር የተሰጠው ዜጋ ይህን ጥያቄ ለመመለስ እንደማይቸገር ግልጽ ነው። ይህ ባለመሆኑ ሕዝቡ ተበደለ።

የሕወሀት/ ደህዴን ኃላፊና የአሁኑ “ ጠቅላይ ሚንስትር ” የሆኑት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሰሩትና የሚያከናውኑት ድርጊት የዳውሮ ሕዝብ ጥላቻቸው እስካሁን እንዳልበረደላቸው ያሳያል። የዳውሮ ሕዝብ እምነት ያለውን ጠንካራ አመራር ጠራርገው አስወግደው፤ በቀጣይም ሌላ የተሻለ መሪ እንዳይፈጠር አምክነው በግል አሽከሮቻቸው ተክተውታል። እሳቸው በስልጣን እስካሉ ድረስ የዳውሮ ሕዝብ ለማንኛውም ፍትሐዊ ጥያቄው ምንም ምላሽ እንደማያገኝ እሳቸውም ያውቃሉ፤ አሽከሮሻሸውም ለዚሁ ሳይታክቱ ይሰራሉ፤ የዳውሮ ሕዝብም ይህንኑ በሚገባ ያውቃል። ይቃወሙናል በሚል የዳውሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች በተለያየ ሰበብ ከሥራ ገበታቸው እየተወገዱ ይገኛሉ።

የእርሳቸው ዓላማ የዳውሮ ሕዝብን ጥቅም ሥልጣናቸውን ተጠቅመው ነጥቀው የራሴ ነው ለሚሉት ብሔር አሳልፈው የመስጠትና የመጥቀም ራዕይ ነው። ለምሳሌ ያህል በዳውሮ ውስጥ የተካሄደውን የሰፈራ ፕሮግራም የሥራ ክንውን፤ በግልገል ግቤ ቁጥር ሦስት የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ምንጭ ግንባታ ሥራ ከባለሙያና ከአስተዳደር ሠራተኞች ቅጥር ጀምሮ ከኃይል ማመንጫው ሥራ ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ የተከላ ሥራ እንቅስቃሴዎች ድርጊቱን መመልከት በቂ ማስረጃ ነው። በወላይታ በኩል ብቻ ግንኙነት እንዲኖረው በማሰብ የዳውሮ ጠንባሮን የገጠር መንገድ ፕሮጀክት ሥራ ሥልጣናቸውን ተጠቅመው አስዘግተውበታል። የዳውሮ ሕዝብ የወረዳ ጥያቄም እስከ አሁን መፍትሔ እንዳያገኝ ያደረጉ እሳቸው ለመሆናቸው የዳውሮ ሕዝብ ጥርጥር የለውም።አሽከሮቻቸውም ለሚቀርባቸው ሁሉ ይህችን ለሕዝቡ አረጋግጠዋል።አቶ ሺፈራው ሽጉጤ የደቡብ ክልል አስተዳዳሪ በዋናነት በዳውሮ የወረዳ ጥያቄ ጉዳይ አቶ ኃይለማርያም ያሳረፉትን በደል ጠንቅቀው ያውቃሉ። ለሕዝቡ ወረዳ በመስጠት ችግሩን ለመፍታት እንኳ እንዳይችሉ ተደርገዋል።

ህወሀቶች ከአቶ ኃይለማርያምና ከግል አሽከሮቻቸው ጡጫና በደል የዳውሮን ሕዝብ ታደጉ አላቅቁትም። ታግላችሁ የደማችሁት እናንተ ናችሁና እናንተው ብትበድሉት ይሻላል እሳቸው ከሚበድሉት። በደልን ማንም በደለ ያው ነው። ግን የእሳቸው በደል ባሰበትና ነው። እርሳቸው እንደሚሉት የዳውሮ ሕዝብ አሸባሪ፤ ጥገኛና ጸረ ልማት አይደለም። የሚጠቅመውንም የማያውቅ ሕዝብ አይደለም። የወረዳና የልማት ጥያቄን ልዩነትና አንድነት ጠንቅቆ ያውቃል። ለወላይታ ሕዝብ አምስት ተጨማሪ ወረዳ ሲሰጡት አቶ ኃይለማርያም የወላይታን ሕዝብ ጥገኛ ነው አላሉም። ጭቁን ሕዝብ ነው ብለው ነበር የሰጡት። ዛሬ የዳውሮ ሕዝብ የወረዳ ጥያቄ ከወላይታ ሕዝብ ቀድሞ ያቀረበ መሆኑን እያወቁ የተዛባ ሥም ሊሰጡት አይገባም። ይህንን ለምን ታደርጋለህ? የሚል ሰው የለም! እርሳቸውና የአሽከሮቻቸው የግፍ አገዛዝ ዘመን በዳውሮ ምድር ሊያበቃ ይገባልና የዳውሮን ሕዝብ ከእሳቸው ጡጫ አውጡት።

የወረዳ ጥያቄን ለማምከን ሲባል ወረዳውን በሁለትና በሦስት መንደር ከፋፍሎ የአንዱን መንደር ሕዝብ በሌላኛው ላይ ጥገኛ ሕዝብ ነው ታገሉት ብሎ መቀሰቀስ ፍጹም ኃላፊነት የጎደለው አካሄድ ነው። ሕዝብ ሁልጊዜ አብሮ የሚኖር ነው። መንግሥት እንደነባራዊ ሁኔታው ሊቀያየር ግድ ነው። የሚቀየርና የሚያልፍ መንግሥትና ገዢ ፓርቲ ለዘመናት የኖረንና ወደፊትም አብሮ የሚቀጥል ሕዝብን ጥገኛ ነው፤ የጥገኛ ሐሳብ ተሸካሚ ነው፤ ጠላትህ ነው! ወዘተ በሚል ሕዝብን በጥላቻ እንዲተያይ ማድረግ አይጠቅምም። ይህንን ኃላፊነት ለጎደላቸው ከፍተኛ አመራሮች ንገሯቸው።

መልዕክት ለዳውሮ ዞንና ለየወረዳዎቹ ካድሬዎች

የዳውሮ ወረዳዎች የማዕከል ጥያቄ የተነሳው አሁን በእናንተ ዘመነ ሥልጣን አይደለም። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት አመራሮችም ሆኑ ካድሬዎች ለችግሩ መነሻዎች እንዳይደላችሁ እረዳለሁ። የችግሩ ምንጭ ቀደም ሲል የወረዳዎች መታጠፍና እንደገና መዘርጋት ጥሎ ያለፈው ችግር እንደሆነም አስተውላለሁ። ችግሩን ለመፍታት ከጪ፤ ገሳ ጨሬና ተርጫ ቤት የሠሩና የንግድም ሆነ ሌሎች የግል ድርጅቶችን የመሰረቱ ከፍተኛ ካድሬዎች የሚያሳርፉት ቀጥተኛ ያልሆነ ግፊትና ጫናም እንዳለ ይሰማኛል። በየወረዳው ማዕከል የተሰሩ የአመራሮችና የካድሬዎች የግል መኖሪያ ቤቶች፤ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ለዚህ የወጣው ወጪ ወዘተ ቀላል እንዳይደለም አልዘነጋም። ይህ ሁሉ ግን ከምንመራው ህዝብ መብት የሚበልጥ አይደለም።ተጠቃሚው ሕዝብ አይመቸኝም ሲል ያለው አማራጭ መቀበልና በሕዝብ ውሳኔ መገዛት ይገባችኋል።

ይህንን የቤት ሥራና የዳውሮ የወረዳዎችን የማዕከል ጥያቄ በቀላሉ መመለስ ሲችል የሰሜን ኦሞ ዞን መዋቅር ፈርሶ በ1993 ዓ.ም መግቢያ አካባቢ ዳውሮ እንደ ዞን ሲዋቀር በወቅቱ የነበሩ የፖለቲካ አመራሮች ይህንን ችግር በሚገባ አስተውለው መወሰንና በቀላሉ ማስተካከል ሲገባቸው ይህንን ችግር ተክለው እንዳለፉ ይሰማኛል። ይህ የዛሬው የዳውሮ የአያማክለኝም ጥያቄና ችግር በሂደት ሊመጣ እንደሚችል አስቀድመው ማየት የቻሉ የዳውሮ ምሁራንና ባለሙያዎች ነበሩ። አስተያየታቸውን አቅርበው እንደነበር አውቃለሁ። ወረዳዎች እንዴት በአዲስ መልክ ቢካለሉ የተሻለ ሊሆን እንደሚችል አጥንተው ያቀረቡት ነገር ነበር። ይህንን ጥናት አስፍቶ ሕዝብን ማወያየትና የተሻለ መፍትሄ ማምጣት አልተቻለም። የዚያኔ  አስፈላጊ የነበረው ወረዳና የወረዳ ማዕከል ጉዳይ እንደተራ ነገር ታይቶ መፍትሄ ሳያገኝ ቀርቷል። ሕዝብ ተንቋል።

የቶጫ ወረዳ ሕዝብ የመኪና መንገድ በመቆፈር ግንኙነት መቁረጡን አትዘነጉትም። ይህን  ያደረገ ህዝብ አቅም ቢኖረው ኖሮ ለደረሰበት በደል የተሻለ እርምጃ አመራሩ ላይ ይወስድ እንሰነበር ለመገመት የሥነ ልቡና ትምህርት አይጠይቅም። ተቃውሞውን አሳይቷል። በተመሳሳይ የዋካንና አካባቢውን  ሕዝብ የወረዳ ማዕከል ጥያቄ ባለፈው ዓመት አይታችሁታል። የዲሳን ሕዝብ ብሶት ደግሞ ሰሞኑን እያያችሁት ነው።

ጋሞ ጎፋና ዳውሮ የተለያዩ ናቸው። አቶ ታገሰ ጫፎ ወደ ደጋማው የጋሞ አካባቢ ተንቀስቅቅሶ የሕዝብ ፍላጎት የነበረውን የተጨማሪ ወረዳ ጥያቄ ለማምከን ባደረገው ጥረት ውጤታማ ሥራ ሰርቷል በሚል ተሞክሮ ይህ ሂደት በዳውሮ ሕዝብም ላይ ይሞከር በሚል የዳውሮ ሕዝብ እንደላቮራቶሪ እንዲሞከርበት አሥራ አንድ ገጽ ወረቀት ለውይይት የቀረበ ሰነድ በሚል ተዘጋጅቶ ተሰጥቷችሁ የሕዝቡን ጥያቄ ለማፈን እየሰራችሁ ትገኛላችሁ። ለዚሁም አፈጻጸም እንዲመች አስተያየት እንዲሰጥ የመናገር ዕድል ለማን እድል መስጠት እንዳለባችሁ ጭምር ተነግሯችሁ በነጻነት መናገር ለሚችሉ አርሶ አደሮች የመናገርና ሀሳባቸውን መግለጽ እንዳይችሉ በሕዝብ ስብሰባው ላይ እድል በመከልከል፤ እንቢ ብለው ከተናገሩ አቅራቢያችሁ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ በማሰር ማፈን፤ የመንግሥት ሠራተኛ ከሆነ ደግሞ በተጨማሪ ማስፈራራት ከሥራ ማገድ እንዲሁም ከሥራ ማባረር ወዘተ ተግባራዊ በማድረግ የህዝብን ጥያቄ መቀልበስ እንደሚገባ ከሰነዱ ላይ ሰፍሯል። እየሰራችሁ ያላችሁትም ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ነው። በዋናነት የጋሞጎፋ ሕዝብ ጥያቄ የተጨማሪ ወረዳ ጭምር እንጂ በጉልህ የወረዳ ማዕከል ጥያቄ አልነበረም።

ባለሙያዎች የሆናችሁ አመራሮችና ካድሬዎች በሙያችሁ ሰርታችሁ በቀላሉ መኖር የምትችሉት ዜጎች ናችሁ። እውነትን ሰርቶ ማለፍ የህሊና ቁስል የለውም። እስቲ የሚከተሉትን ጥያዌዎች ልጠይቃችሁ። ሲዳማ ዘጠኝ፤ ወላይታ አምስት፤ ቤንች ማጂ ሦስት፤ ስልጢ ሁለት፤ ጎፋም እንደዚሁ አዳዲስ ወረዳዎች ለሕዝቡ ሲሰጥ ለምን የነዚህ ዞንና ወረዳዎች አመራሮች ህዝቡን ወረዳ አያስፈልገውም ልማት ይጠቅመዋል ብለው ወረዳውን ያላስከለከሉትና ሕዝባቸውን ያልቀሰቀሱት ለምንድነው? ምናልባት አመራሩ ጥገኛ ስለሆነ ነው ትሉኝ ይሆናል። ለሲዳማ አቶ ሺፈራው፤ ለወላይታ አቶ ኃይለማርያም፤ ለስልጢ አቶ ሬድዋን፤ ለቤንች ማጂ አቶ ጸጋዬ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች የነበሩት ለሕዝባቸው አዳዲስ ወረዳዎችን ሰጧቸው። እርግጠኛ ነኝ እነዚህን አመራሮች ጥገኛ ናቸው እንደማትሉ! ታዲያ ዳውሮ ውስጥ ተጨማሪ ወረዳ መጠየቅ ይቅርና የወረዳ ማዕከል ይስተካከልልኝ ብሎ ማሰብ መናገርና መጠየቅ ምነው ጥገኝነት በሚል ፍረጃ ውስጥ የሚያስገባ ሆነ? የዳውሮ የወረዳ ማዕከል ጥያቄ ለምን ከልማት ጋር ይያያዛል? እናንተ ለህዝባቸው ወረዳ ከሰጡት ባለስልጣናት የምታንሱት ሕዝባችሁን ስለማትወዱና ራሳችሁንና የሥልጣን ዘመናችሁን ለማስረዘም ብላችሁ ነው የሚል ጥያቄ ቢነሳባችሁ መልሳችሁ ምን ይሆን? ቀድሞውኑ ማን ጠይቋችሁ!

በቀድሞዎቹ የንጉሡና የደርግ መንግሥታት ዘመን ያገለገሉትና ሕዝብን በድለዋል ተብለው ብዙ ባለስልጣናት ታስረዋል ተቀጥተዋል። እነዚህ ባለሥልጣናት አብዛኛዎቹ ያገለገሉበት መንንግሥት የሰጣቸውን ሥራ በሕዝቡ ላይ አስገድደው አስፈጽመዋል። ትልቁ በደላቸውና ስህተታቸው ይህ እንደሆነ ሲገለጽ ሰምተናል። የመንግስትን ዕቅድና ፍላጎት በጉልበት ማስፈጸም፤ የግለሰብን የመናገርና የማሰብ ነጻነት መንፈግ፤ ያለምንም ጥፋትና በደል ሰውን በመናገሩ ብቻ እንደወንጀለኛ ማሰር ማንገላታት ከሥራ ማባረር ወዘተ ማድረግ ከቻላችሁ ታዲያ እናንተ ከእነርሱ የምትለዩት በምንድነው? እናንተስ ነገ ተመሳሳይ ጥያቄ እንደማትጠይቁ እርግጠኞች ናችሁ?

አትቀበሉኝ ይሆናል ግን ልምከራችሁ።‘‘ጻድቃን ሥልጣን ሲይዙ ሕዝብ ሐሤት ያደርጋል፤ ክፉዎች ሲገዙ ግን ሕዝብ ያቃስታል፡፡’’ ምሳሌ 29፡2  እናንተንን ክፉዎች ናችሁ ለማለት ባልደፍርም የዳውሮ ሕዝብ እያለቀሰ ነው። እውነቱን ደግሞ ውስጣችሁ ያውቀዋል። እናንተም ነገ ታልፋላችሁ። ለሚያልፍ ሥልጣን ብላችሁ የማያልፈውን ወገናችሁን በዋናነት ዳውሮንና ሕዝባችሁን አትበድሉ። የመሰለውን ስለተናገረ ሰውን አላግባብ ጎትታችሁ አትሰሩ። የደርግ ባለሥልጣናት እንኳን እንደናንተ ለሕዝብ እንዲዋሽ ትብብር ጠይቀው እንቢ አልተባበርም ያላቸውን ግለሰብ ስለማሰራቸው እርግጠና አይደለሁም። የእናንተ ባስ እኮ!

የመንግሥት ሠራተኛ የግል ሠራተኛችሁ አይደለም። እንደእናንተ ሕዝብን አልዋሽም ስላለ ከሥራም አንዲባረር እንዲጎሳቆል አታድርጉ። ቢቻላችሁ የህዝቡን ጥያቄ በምትችሉት ሁሉ መልሳችሁ ምኑም ቀርቶባችሁ በሰላምና በፍቅር ከወገኖቻችሁ ጋር ብትኖሩ ይሻላችኋል። ነገ ከስልጣን ስትወርዱ የምትኖሩት ከዳውሮ ሕዝብ ጋር ነው። ብትሞቱ የሚቀብራችሁ ይህ ህዝብ ነው። ቃሉን አክብራችሁ ብትሰሩ ይጠቅማችኋል። ወደዳችሁም ጠላችሁ የህዝብ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱ አይቀርም። አሁን በሥልጣን ያላችሁት ግለሰቦች የሕዝቡን ጥያቄ በተገቢው መልሳችሁ ምርቃቱ ቢቀርባችሁ እንኳ ሳትረገሙ ብታልፉ ይሻላችኋል። ነገ ከነገወዲያ እግዚአብሄር ሲፈቅድለት በእናንተ ማግስትም ቢሆን የህዝብ ጥያቄ በተገቢነት መመለሱ እንደማይቀር ለማየት ዕድሜ ያድላችሁ!

ለመንግሥት ሠራተኞች

ረዳት ሣጅን ሽታዬ ወርቁ በሎማ ዲሣ ወረዳ አካባቢ የዲሣ ከተማ ፖሊስ በመሆን ለዓመታት ማገልገሉንና በቅርቡ ወደ ሎማ ገሣ መዛወሩን፤  በዲሣ አካባቢ ቆይታዉ ወቅት የዲሣን ወረዳ ጥያቄ የሚያንቀሳቅሱ ሦስት ግለሰቦችን እንዲያስር ከዳዉሮ ዞን የፖለቲካ ጉዳዮች ሀላፊ መመሪያ ተሰጥቶት ያለ አንዳች በቂ ማስረጃና ጥፋት ሰዉ እንዲሁ ከሜዳ አላስርም በማለቱ በዞኑ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሁኔታው አልተደሰቱም ነበር፡፡ የዲሣን ወረዳ ጥያቄ ያንቀሳቅሳሉና መታሰር አለባቸዉ ተብለዉ ከዞኑ ፖለቲካ ኃላፊ ትዕዛዝ የተላለፈባቸዉ ግለሰቦች አቶ አባቴ አሰፋ የትምህርት ባለሙያ፤ አቶ መስፍን ማሞ አርሶ አደር፤ እና አቶ ደስታ ቶልባ የግብርና ባለሙያ ነበሩ። አሁን እዚህ ላይ የፖለቲካ ኃላፊውንና ፖሊሱን አወዳድሩ። የትኛው ነው ለሕዝብ የቆመውና እውነተኛ የህዝብ ጥቅምና መብት የታገለው? ልዩነቱን ተመልከቱ።

ይህንን ያነሳሁት በየወረዳው እየተደረገ ያለው  የሕዝብን እውነተኛ የተጨማሪና የወረዳ ማዕከል ይስተካከልልኝ ጥያቄ የመንግሥት ሰራተኛው እንዳይደግፈው ለማድረግ እየተካሄደ ያለውን ሁኔታ ለማመላከት ነው። የመንግሥት ሠራተኛው የራሱም ሆነ የቤተሰቡ ህይወት መንግሥት በሚከፍለው የወር ደመወዙ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ካድሬዎች ይህችን እንጀራውን እንደማስያዣ ዕቃ ቆጥረው አንድን የመንግሥት ሠራተኛ እነርሱ የፈለጉትን እንደ ቴፕሪከርደር ሲዲ ያሻቸውን ሞልተው ለማናገር የወሰኑ ይመስላል።ልጅን በአባቱና በቤተሰቡ ላይ ለመቀስቀስ እየሰሩ ነው።

ኃላፊነት የጎደለው ሥራ እያተሰራ ይስተዋላል። የህዝብን ጥያቄ ለማፈን ለመንግሥት ከባድ አይደለም። እንደተለመደው ማሰር ማንገላታት ማስፈራራትና ጥያቄህን አንመልስም እንቢ ምን ታመጣለህ? በሚል በተለመደው መንገድ ማስቆምና መግታት ይቻላል። ተችሏልም። ነገር ግን አንድ ወረዳ ውስጥ ያለን የኖረንና የሚኖርን ሕዝብ እርስ በራሱ ለማጋጨት በአንድ ወረዳ ውስጥ የዋካንና ዙሪያውን ህዝብ ጥያቄ የማሪ ዙሪያ ህዝብ እንዲቃወመው ሕዝብን ማነሳሳትና መቀስቀስ፤ የዲሳን አካባቢ ሕዝብን የወረዳ ማዕከል ጥያቄን ለመቀልበስ የገሳጨሬ አካባቢ ሕዝብን መቀስቀስ፤ የቶጫ አካባቢን ሕዝብ ጥያቄ ለማፈን የከጪ አካባቢ ሕዝብን መቀስቀስ የዛሬን የሕዝብን የወረዳ ጥያቄ ለመግታት እየተሰራ ያለው ኃላፊነት የጎደለው ሥራ ለነገ አብሮነታቸው የሚያሳድረው የነገር ቁርሾ እንዳይኖር በተማሩትና አርቀው ማስተዋል የሚችሉት የሕብረተሰቡ ወገኖች ሊያስቡበትና ሊነቁበት ይገባል። ካድሬዎቻችን ምን እንደነካቸው አላውቅም። እኛ በስልጣን ላይ ዛሬን እንቆይ እንጂ የሕዝብ ጉዳይ የነገ ጉዳይ ወዘተ አያገባንም ያሉ ይመስላልና እንድናስብ አደራ እላለሁ። እነርሱ ለሕዝባቸውና ለዳውሮ ጥሩና የሚችሉትን አድርገው ለማለፍ የታደሉ አይደሉም።

በ1998 ዓ.ም እና በ1999 ዓ.ም የሌሎች አካባቢዎች የዞንና የክልል አመራሮች የነበሩ ለህዝባቸው ልማትና ዕድገት ሲሉ የራሳቸውን ጥቅም የማያስቀድሙ፤ ህዝባቸውን የሚወዱና የሚያከብሩ፤ በተሰጣቸው የስልጣን ክልል የህዝባቸውን የልማትና የወረዳ ጥያቄ አንግበው የታገሉና ጸንተው የቆሙ፤ የወከለኝ ህዝብ ጥያቄ የእኔም ጥያቄ ነው ያሉ አመራሮች በሌሎች ዞኖችና አካባቢዎች በተለያየ ቦታና ደረጃ አሉ። የሲዳማን የስልጢን የጎፋን የቤንችንና የወላይታ አመራሮችን የሥራ ተግባር ማየት እንችላለን። እነዚህ ህዝባቸውን ጠቅመዋል። የወከላቸውን ሕዝብ ጥያቄ በሆዳቸው አልለወጡትም። በዚህ የተነሳ ከፍተኛ የሞራል የበላይነት ሊሰማቸው ይገባቸዋል። ሕዝባቸውና አካባቢያቸው ሲዘክራቸው ይኖራል።

ለጊዚያዊ የግል ጥቅማቸው የቆሙ፤ ነገ ሳያውቁትና ሳይመሰገኑበት አሊያም ታስረው ወይም ተባርረው ለሚጥሉት ሥልጣን ትኩረት የሰጡ፤ ለጊዜው  የያዙትን ሥልጣን ማጣት የሚያስጨንቃቸው፤ ራስ ወዳዶች፤ ጥሩ ነገር ለህዝባቸው ሰርተው ለማለፍ ያልታደሉና አድርጉ የተባሉትን ለማድረግ ተሽቀዳድመው ከመሮጥ ባሻገር ቆም ብለው ይህ ሕዝባችንን አካባቢያችንን ይጠቅማል ወስ አይጠቅምም? ሕዝቡስ ምን ይላል ማለት የማይችሉ የህዝብ ተቃራኒዎች ደግሞ አሉ።። የዳውሮ ዞን አመራሮችን በዚህ ቡድን አስገብቶ መውቀስ ተገቢ ነው። ጠንካራ አመራሮች ለህዝባቸውና ለዞናቸው ተጨማሪ ወረዳ ታግለው አስገኙ። እኛ ለህዝብ የቆመ አመራር በዞን ደረጃ ስላልነበረን የዳውሮ ህዝብ እያነባ እያለቀሰ ይገኛል። ከእሱ የተሰበሰበው ግብርና ታክስ እየተከፈለው የሚሰራ አመራርና ካድሬ ህዝቡ ወረዳ አያስፈልገውም አልጠየቀም እያለ እየዋሸ እኛም የሱን ግጥምና ዜማ ተቀብለን እንድናዜም ሊያስገድደን ይታገለናል። አለመታደል እኮ ነው ወገኖቼ! በፍጹም እንቢ ልንል ግድ ይለናል። ተቃውሟችሁን በግልጽ አድርጋችሁ ጥቂቶችን ሰለባ ማድረግ ባያስፈልገንም የሕዝብ አጋርነታችንን በምንችለው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተቃራኒ መግለጽ የሞራል ግዴታችን ነው።ይህ አመራር ጥቅሜ ከሚጓደልና የመኪና ጋቢና ከሚቀርብኝ ከዳውሮ ሕዝብ ምኑም ይቅርበት ብሎ የወሰነ ይመስላልና ያቅማችንን የማበርከት ግዴታ ይጠብቀናል።

ለዳውሮ አርሶአደሮች፤ ነጋዴዎችና ሌሎች የየከተማው ነዋሪዎች

ለዳውሮ ዞን ሕዝብ መንግሥት ተገቢውን  ምላሽ እንደሚሰጣችሁ በተስፋ ስትጠብቁ ቆይታችኋል። ነገሩ መፍትሄ ሊሰጠው እንደሚገባ የሚታወቅ ቢሆንም የህዝቡ ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል የሚል የፖለቲካ አመራር በየደረጃው ባለማኖሩ እስካሁን ተገቢውን ምላሽ ማግኘት አልተቻለም። እንዲያውም እያደር ጥያቄው የጥገኞች ነው፤ የጥቂቶች ነው፤ የብዙኋኑ የዳውሮ ሕዝብ ጥያቄ አይደለም፤ ሕዝቡ ልማት እንጂ ወረዳ አይጠቅመውም በሚል የሕዝቡን ጥያቄ ለመቀልበስና አቅጣጫውን ለማስቀየር ብሎም ህዝቡ ተጨማሪ ወረዳ እንዲያጣና የሚሻውን የወረዳ ማዕከል ወደሚቀርበው ሥፍራ የማዛወር መብት እንዳይኖረው ለማድረግ ተግተው እየሰሩ ይገኛሉ።

የገዛ ልጆችህ ናቸው ጥያቄህን ለመድፈቅ አሲረው አንተን ለማፈን ተግተው እየሰሩ የሚገኙት። የሚናገረውን ለማስፈራራትና እንዳይናገር በማድረግ እድል በመከልከልና በማሸማቀቅ፤ ለምን መብታችንን ትነኩብናላችሁ ብለው የሚጠይቁ ከተገኙ ለማስፈራሪያነት በማሰር ለማስፈራራት ዕቅድ ተሰጥቷቸው ይህንን ለመተግበር ይሰራሉ። በመንደርና በአገልግሎት በመከፋፈል ጥያቄህን ለማሳነስና የጋራ ጥያቄ አይደለም የጥቂቶች ነው ለማለት እየተባበሩ ነው። ስለዚህ በአገልግሎትና በመንደር መከፋፈል አያስፈልግህም። ልማትና ወረዳ አይነጣጠልም።

አንድ ምሳሌ ላንሳላችሁ። የወረዳ ማዕከል ጥያቄ የእኛ አይደለም የጥቂቶች ነው እኛ ወረዳ አንፈልግም በሉ፤ እንቢ ካላችሁ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቱን ከዚህ እናነሳለን፤ የጤና ጣቢያ ሥራ አይከናወንም ወዘተ የሚል ተራ ማስፈራሪያ አንድ ሆድ አደር ካድሬ ሲናገር ሰምተው ከተሰብሳቢዎቹ መካከል አንዱ አርሶ አደር (በማረቃ ወረዳ ጌንዶ አገልግሎት አካባቢ ውስጥ ነዋሪ ናቸው ) ካድሬውን በሚያሳዝን መልኩ ረግመውት አሁን የእኛን ወረዳ ጥያቄ ለማስጨንገፍ ብለህ ለሆድህ አድረህ ህሊናህን ሽጠህ በል የተባልከውን እያልክ ነው ብለዉት ይህንን ተራ ወሬ ይዞ ወደ መጣበት እንዲመለስና እሳቸውም ሆነ ሕዝቡ የሚሻለውን ጠንቅቀው የሚያውቁ መሆኑን አስተምረውት አሳፍረውት መልሰውታል።

ይህንን የተናገሩት አርሶ አደር በፖለቲካዊ ንቃተ ህሊና አንጻር ከካድሬው ጋር አነጻጽራችሁ የቱ የተሻለ ደረጃ ላይ እንዳለ አስተውሉ። ማነው የህሊና ነጻነት ያለው? ልማትና ወረዳ አይነጣጠሉም። ወረዳ ሲመጣ ከወረዳው ጋር አብሮ ልማትም ይመጣል። ዳውሮ ዞን ባይሆን አሁን የደረሰበት የልማት ደረጃ ላይ ይደርስ ነበር የሚል ካድሬ ሊመጣ እንደሚችል አትጠራጠሩ ግን አትመኑት። የሰሞኑ ካድሬ ድንጋይ ዳቦ ነው ለማለት የሚታቀብ ስለመሆኑ ያጠራጥራል። እያከናወነ ያለው ክብሩን ህሊናውን ሞራሉን ሁሉ ትቶት ነው።

የዳውሮ ሕዝብን የወረዳና የልማት ጥያቄውን ለመቀልበስ የሚሰሩ ሁሉ የዳውሮ ልማትና የዳውሮ ህዝብ ጠላቶች ናቸው! ሕዝብ የሚበጀውንና የሚሻለውን ያውቃል። የካድሬ ሰበካና የሐሰት ቀላጤ አያስፈልገውም። የካድሬው ዓላማ የህዝብን ጥያቄ ወደ ጥቂቶች ጥያቄነት ለመቀየርና ጥያቄውን ለማምከን ነውና ሁላችንም በምንም ሳንከፋፈል አብረን ቆመን ጥያቄያችንን በጋራ በአንድ ድምፅ ማስተጋባት ይጠበቅብናል።

የዳውሮ ምሁራን የሆናችሁ በሙሉ!

ከላይ በዝርዝር ያስቀመጥኩትን እውነታ ተመልክታችኋል። የዳውሮ ዞን አመራሮች ከክልል አመራሮች ተጭነው የመጡትን የሕዝቡን የወረዳና የወረዳ ማዕከል ጥያቄ ለማምከን ምን ያህል ተግተው እየሰሩ እንዳለ ተመልከቱ። ከራሳቸው አልፈው የወረዳ አመራሮችንና ካድሬዎችን አስገድደው የተጫኑትን መልሰው ጭነውባቸው ከህዝቡ ጋር እያላተሟቸው ይገኛል። እኔ በግሌ የወረዳ አመራሮች ላይ ብዙ አልፈርድም። ለአብዛኛዎቹ የእንጀራ ጉዳይም ሆኖባቸው ሳይወዱ በግድ የተጫኑትን ማራገፊያ አጥተው እንደሚሰቃዩ ይሰማኛል። ከሕዝቡም እየደረሰባቸው ያለው ነገር እያሰቃያቸው ነው። በድርጊቱ ከዞን ጀምሮ ያለው አመራር በሕዝባችን ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም በደልና እንግልት ተጠያቂ መሆናቸውን ልብ ልንል ይገባል።

ምሁሩ የሕዝብ ወገን አመራሩ ለምንድነው እንዲህ የሚያደርጉት? ምን ይሻሻል? ከእኔ ምን ይጠበቃል? በሚል ማሰብ እንደሚገባችሁና እንቅስቃሴውንም በአንክሮ መከታተል እንደሚጠበቅባችሁ አሳስቤ ጽሁፌን በዚሁ እቋጫለሁ።

“አይን እያላቸው የማያዩ ፤ጆሮ እያላቸው የማይሰሙ”

በዳዊት መላኩ ሞገስ (ከጀርመን)

ወያኔ/ኢህአዴግ የተፈጥሮ ባህሪው በሰዎች መካከል ጥርጣሬና ጥላቻን በዝራት በመሆኑ በማናኛውም ቦታ ረጅም እጁን በማስገባት መፈትተፍ የዘወትር ተግባሩ ሁኖ ቆይቷል፡፡ላለፉት 11 ወራት

የእስልምና እምነት ተከታዮችን የሀባሽ አስተምሮን በግድ ለመጫን በፈጠረው ጣልቃ-ገብነት በሺ የሚቆጠሩትን ለስደት ፤በርካቶችን ለእስራት እና ለሞት ሲዳርግ የቆየውና አሁንም ድረስ መቋጫ ያልተገኘለት ውዝግብ ውስጥ የገባው ወያኔ/ኢህአዴግ አሁን ደግሞ የጥፍት ቀስቱን በክርስትና እምነት ተከታዮች እና በቤተ-ክርስቲያን ላይ አነጣጥሯል፡፡

ወያኔ/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን በመጣ ማግስት ጀምሮ ለአገዛዙ  አይመቹኝም ብሎ የተጠራጠራቸውን ሁሉ በማስወገድ ህዝባዊ ተቋማትን፣የእምነት ተቋማትን፣ የትምህርት ተቋማትን እንዲሁም በሀገሪቱ ያሉ መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በወያኔ ካድሮዎች እንዲመሩ በማድረግ የፖለቲካ አቋማቸው እንጂ የትምህርት ዝግጂታቸውና የስራ ልምዳቸው  ፈጽሞ  የማይምጥናቸው አቅመ-ደካሞችን በማስቀመጥ የሀገሪቱን እድገት ቁልቁል እንደካሮት እንዲሆን አድርጎታል፡፡የዚህ ችግር የመጀመሪያ ገፈት ቀማሽ የሆነችው ደግሞ ቅድስት ቤተክርስቲያንና   በውስጧ ያሉት አማኞች ናቸው፡፡በዚህም የተነሳ ቤተክርስቲያን ወደ ሶስት እንድትከፈል በርካታ አባቶችም ሀገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እና ክርስቲያኖችም እርስ በርስ በጥርጣሬ እንዲተያዩ አድረጎ ቆይቷል፡፡የአቡነ ጳውሎስን ሞት ተከትሎ የቤተክርስቲያንን አንድነት ለማስመለስ በተለያዩ ሰላም ወዳድ እና የቤተክርስቲያን ተቆርቃሪ ወገኖች ብዙ ሲደከም ቢቆይም ወያኔ/ኢህአዴግ ይቅርታና እርቅ ለባህሪያቸው ስለማይስማማ እና የሰላምን ዋጋ የሚያዩበት አይናቸው ስለተሰወረ የእርቀ-ሰላሙን ገመድ ለመበጠስ ጫፍ ደርሰዋል፡፡በክልሎችና በእምነት ተቋማት በህጋዊነት ሽፋን  ስም ጣልቃ ለመግባት ያቋቋመው የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አቡነ ጳውሎስ ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ በጋራና በተናጠል የቤተክርስቲያኒቱን አባቶች በማነጋገር ለስውር አላማው መጠቀሚያ ሊያደርጋቸው ሲነቀሳቀስ ቆይቷል፡፡የሚኒስትር መ/ቤቱ በዚህ ብቻ ሳይወሰን  አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸውንናበእስራኤል ነዋሪ ሆኑትን አባት  ጳጳስ ለማድረግ ልኡካን በመላክ  አላማየን ሊስፈጽሙልኝ  ይችላሉ በማለት  ያመነባቸውን በቤተክርስቲያኒቱ ላይ  ለመጫን ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡  ለቤተክርስቲያን አንድነት ሲደክሙ ከቆዩት አባቶች መካከልም ሊቀካህናት ሀይለስላሴ አለማሁን መንግስት ለመገልበጥ እንጂ ለማስታረቅ አልመጡም በማለት በሚታወቅበት ጥላሸት መቀባት ተግባሩ ጥላሸት ቀብቶ ወደመጡበት አሜሪካ አስሮ መልሷቸዋል፡፡

ወያኔ/ኢህአዴግ በየቤተክርስቲያኑ የሰገሰጋቸው ካድሬዎችም ከቤተክርስቲያንና ከምእምናኑ ጥቅም ይልቅ ቅደሚያ ለወከላቸው መንግስት ስለሚሰጡ ሰበብ በመፈለግ እርቀ-ስላሙ የሚቋረጥበትን መንገድ እየጠረጉ ገይኛሉ፡፡ለዚህም ተግባራቸው ማሳያ የሚሆነው አሰታራቂ ኮሚቴው ገለልነኛ አደለም፤ይቅርታ ካልጠየቀ አንደራደርም በማለት የማደናገሪያ መግለጫዎችን በመስጠት ለመለያቱ በር እየከፈቱ ይገኛሉ፡፡ በተቃራኒው ሊቆሙለት የሚገባውን የቤተክርስቲያንን አንድነት የማስጠበቅ አና የእምነት ነጻነትን የማስከበር ጉዳይ ወደጎን በማሽቀንጠር ለግል ጥቅማቸውና ስልጣናቸውን ለማቆየት ከአጥፊወች ጎን ተሰልፈዋል፡፡

ከወያኔ ያለፉት ልምዶችና ከተፈጥሮ ባህሪው ለመረዳት የሚቻለው በሀይል እንጂ በድርድር፣በእርቅ፣ስጥቶ የመቀበል መርህ የመሳሰሉት ተግባሮች ስለማይገቡት ከሚወደው ስልጣን ኮርቻ እስካልወረደ ድረስ የፈጠራቸው ዘርፈ ብዙ ችግሮች ከኢትዮጵያውያን ጫናቃ ላይ በቀላሉ ሊወርዱ አይችሉም፡፡ወያኔ/ኢህአዴግ እርቀ-ሰላሙን ከልብ ይቀበላል ማለት “ከእባብ እንቁላል የዶሮ ጫጩት እንደመጠበቅ ይቆጠራል፡፡”ይህን ለመገመት የግድ ነብይ መሆን አይጠይቅም፡፡ ወያኔ/እህአዴግ በርካታ ጊዜያት ብሄራዊ እርቅ እንደወርድ በተለያዩ ሀይሎች ለበርካታ ጊዜ ጥያቄ ቀርቦለታል፡፡ነገር ግን የተፈትሮ ባህሪያቸው የህን ለማስተናገድ አይስማማውም፤አይናቸውም ሰላም ሰፍኖ  ለመየት ፤ጆሮዋቸውም የሰላም ድምጽ ለመሽማት አይፈልግም፡፡መፍትሄው አንድ እና አንድ ብቻ ነው፡፡ኢትዮጵያውያን  በጋራ በሀይል የተነፈግናቸውን መብቶች ሁሉ ማስከበር፡፡

እግዚያብሄር ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ይባርክ!

ECADF.COM

Ethiopian court finds 10 guilty of terror charges

ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Ten men were found guilty Tuesday by an Ethiopian court of plotting terror attackswith Islamist extremist rebels from neighboring Somalia.

 

Judge Bahiru Darecha said the group was making plans and getting supplies to attack political and economic targets in Ethiopia. Eleven men were originally charged with the terror-related crimes but the judge acquitted one person. Six of the men found guilty were charged in absentia. Sentencing will be carried out on Jan. 15.

 

Prosecutors said the suspects, who include one Kenyan national, formed a cell that worked with Somalia’s Islamist radicals, al-Shabab. Al-Shabab is affiliated with al-Qaida.

The verdicts come amid signs of increasing militancy in the East African nation. Ethiopian troops moved into Somalia last year to fight al-Shabab.

Among those convicted is a Kenyan national, Hassan Jarso. When first charged in May, Jarso pleaded guilty to the charges but protested the assertion that he is a senior leader of the group.

“We did plan the attacks and to open the (training) camp but none of it was realized,” Jarso had told the court.

He added that he was waiting for money from al-Qaida agents to establish the camp and start a militant group, based in Ethiopia’s Oromia region.

The other three convicts denied the charges. They are all religious teachers. In their defense they alleged that they were beaten by police to confess and sign documents and that exhibits were planted in their houses.

Ethiopia’s late Prime Minister Meles Zenawi in April told parliament that militants had formed al-Qaida cells in the country’s southern Arsi and Bale areas.

Ethiopia’s military campaign against militants in Somalia from 2006-2009 angered al-Shabab.

There are signs of rising Islamist militancy in Ethiopia. In late April four demonstrators were killed in a clash, after security forces arrested a Muslim religious leader in the Oromia region.

Ethiopia’s Federal Ministry on May 3 issued a statement accusing an unnamed group of trying to declare jihad against the government and working to incite violence in a number of mosques across the country. The statement said a dozen suspects were recruited by the group from the country’s Oromia, Tigray and Amhara regions to carry out illegal activities.

The government also expelled two Arabs who flew in from the Middle East on May 4. The government said the pair went to a mosque and tried to incite violence.

ETHIOMEDIA.COM

 

የማለዳ ወግ . . . አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ የተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች ጥሪ . . .

ነቢዩ ሲራክ

አሮጌው የፈረንጆች አመት አልፎ በአዲስ አመት ከመግባቱ አስቀድሞ በዋዜማው ያየን የሰማነው በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩት የኮንትራት ሰራተኞች ውሎ አዳር ደስ አይልም ፡፡ በያዝነው ወርማ በተለያዩ የሳውዲ ጋዜጦች ሳይቀር የተዘመተብን ይመስላል ፡፡ የኮንትራት ሰራተኞች ተከላካይ ጠበቃ አጥተው ፤ በአሰሪዎች ሲባረሩ ፤ ሲደፈሩና አደጋው በርታ ሲል ተፍተው በኢንባሲና በቆንስል መስሪያ ቤቶች ጥገኝነት ይጠይቃሉ፡፡ ግፉአን ፍትህ ተነፍጓቸው ሲንገላቱ፤ ሲያብዱ ሲታመሙና በሃይል እርምጃ ነፍሳቸው ስትጠፋ ለመክረማቸው ምስክሮች ብዙ ነን ! እርግጥ ነው ለነፍስ ግድያ ተይዘውና ተወንጅለው ዘብጥያ የወረዱ እህቶችም አሉን ፡፡የማለዳ ወግ . . . አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ የተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች ጥሪ

ወንጀሉና ግድያውን በምን ሰበብ አስባብ እንደፈጸሙት ግን ለእኛ የሚነግረን ፤ ለዜጎች ጠበቃ ሆኖ የሚሰማቸውና የሚከራከላቸው ያገኙ አይመስሉም፡፡ በእድሜ ያልበሰሉት እህቶች ነፍስ ለማጥፋት ያደረሳቸው ምን ሊሆን እንደሚችል ለመገመት ሳይሆን ለመረዳት በመጠለያ ያሉ እህቶች ማነጋገር ይበቃ ይመስለኛል፡፡ እህቶች ተፈጸመብን የሚሉትን ግፍና የመደፈር ጥቃት አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ለመፈጸም የሚሰጥ ምክንያት ሊሆንና ወንጀልን መፈጸም አይገባም፡፡ ያም ሆኖ ሊገል የመጣን ገዳይ ለመከላከል አስበውትም ሆነ ሳያስቡት መግደል ራስን ከጥቃት ለመከላከል የሚደረግ እንቅስቃሴ እርምጃ መሆኑን ከህግ አንጻር የሚያስረዳ የመንግስት ተወካይ ያስፈልገናል፡፡

እንደ ዜጋ የተበዳዮችን ህመምና በደል ” እህ ” ብለን በማድመጥ ህግና ስርአትን ተከትለን መፍትሔ ልናፈላልግ ይገባል፡፡ ከምኖበት የቅርብ ርቀት ተፈጽሞ ግርግሩን በወቅቱ ዜናውን በጋዜጦች አንብቤያለሁ ! “ገደሉ” የሚባለውን ያህልም ባይሆን “ተገደሉ ” የሚለው አይነገርም ! ሲላቸው ራሳቸውን በራሳቸው አጠፉ ይሉና ” ሬሳቸውን ውሰዱ!” ይሉናል ! ለምን ራሳቸውን ገደሉ ብሎ ማን ይጠይቅልን ? !ራሳቸው ገደሉ እንኳ ቢባል ሌላን ሰው ከመግደል ራስን መግደል የመክበዱን ያህል ለዚህ ዜጎቻችን ለዚህ ያደረሳቸው ምክንያቱ ምን ይሆን ብሎ የሚያጠይቅልን አጥተናል ! ይህ ሁሉ እየሆነ አንድ የሳውዲ ጋዜጣ ባሳለፍነው ሳምንት አጋማሽ ይፋ ያደረገው ሰነድ በጂዳ በሁለት የግድያ ወንጀል ፤ በያንቡ በግድያ ፤ በአልዘልፊ በደቡብ የሃገሪቱ ጠረፍ ፤ በአፈር አልበጠል ፤ በመካ በረፋዕና በተለያዩ የገጠርና ትላልቅ ከተሞች ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች በከባድ የግድያና የመሳሰሉት ወንጀሎች እንደተያዙ አልመዲና የተባለው ጋዜጣ አትቷል፡፡

እንደ ጋዜጠኛነቴ የዜጎችን ጉዳይ ለመከታተልና መረጃ ለማግኘት ወደ ቆንስሉ ብቅ ባሉኩበት አጋጣሚ ወደ ግቢው ለመግባት ስሞክር ቁም ስቅሌን የሚያሳዩኝ የቆንስሉ ዘበኛ በክብር ጎበስ ብሎ ያስገባቸው የሳውዲ አል መዲና ጋዜጠኞች የጅዳ ቆስንል ሃላፊዎችን አነጋግረው ያወጡትን መረጃ ማንበብ ሆድ አያሞላም፡፡ ልተወው . . .ብቻ የሳውዲ ጋዜጦች የሌለብንን እየለጠፉ ነፍስ ማጥፋታችን አግንነው የኮንትራት ስርራተኛ እህቶቻችንን ነፍስ በስነ ስርአት አልበኛነት እየኮነኑ የስራት አልበኛ ዜጎቻቸው ጥፋትና አሰቃቂ አያያዝ አኩስሰው ስለ መግደል ሙቅ ውሃ መቸለሳቸው ሰፊ ዘገባን እየሰሩ ይነግሩን ይዘዋል !

ከሁሉ በፊት ለዛሬው ድጋሜ የማለዳ ወጌ መነሻ ስለሆነኝ አፋጣኝ ትኩረት ወደ ሚሻው ጉዳይ ላምራ ! ከቆስንሉ አዲስ መጠለያ በቅርቡ እንዲገቡ ከተደረጉት ውጭ ያሉት 16 ተፈናቃዮች ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን ያገኘኋቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በቆንስሉና ከዚህ በፊት በርካታ ተፈናቃዮች በነበሩበት “መዲናተል ሃጃጅ” ከሚባለው መጠለያ አከራዮች መካከል በክፍያ የተነሳው ውዝግብ እልባት ባለማግኘቱ እዚያው ተጠልለው የነበሩ እህቶቻችን ለከፋ መከራ መዳረጋቸውን እውነትነት ከተለያዩ ምንጮች ማረጋገጥ ችያለሁ ፡፡

በመጠለያው የሚገኙ 6 የዓዕምሮ ህሙማንና ጨምሮ አስር ያህል እህቶች ከአስር ቀናት በላይ መብራትና ውሃ ተቆርጦባቸው በበራሪ ተባዮች እየተነደፉ እየገፉት ያለው የለት ተለት ኑሮ ሊናገሩት ይከብዳል ሲሉ ምንጮቸ ምስክረናተቸውን ሰጥተውኛል. . . የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ለእኒህን ተፈናቃይ ግፉአን ነፍስ አድን ጥያቄ መልስ ሲሰጡ መስማት ናፍቆኛል ! እኔ እጽፋለሁ ! እናንተ አንብቡ ! የመንግስት ሃላፊዎቻችን አፋጣኝ ትኩረት ለሚሻው የተፈናቃይ የኮንትራት ጥሪ ጀሮ ሊሰጡ ይገባል ! ጀሮ ያለው ይስማ . . .

የመሰንበቻውን የተፈናቃይ ኮንትራት ስራተኞች ውሎ ተጽፎ የሚገለጽ ብቻ አይደለምና ለህዝብ መብት ማስጠበቅና ለሰብ አዊ መብት ማስከበር የቆመ የመንግስትም ሆነ ገለልተኛ አካል ካለ በቃል ከመናገር ምስሎችና ተንቀሳቃሽ ምስሎች ለሚያይ ለሚሰማ የችግሩን ክፋት ማሳየት ይችላሉና የጀመርኩትን እቀጥለዋለሁ ! በኮሚኒቲው አዳራሽ አጠገብ የተሰራችው ጠባብ መጠለያ የተጠለሉት ግፉአን እህቶች ቁጥር ወደ ሰላሳ ሲጠጋ አምስት ያህሉ ዓዕምሯቸው ተነክቷል ! . . .አንዷ ተረጋግጣ ጋዜጣ ስታነብና ከራሷ ጋር ስታወራ ፤ ሌላዋ ግቢውንና ካፍቴሪያውን እየገባች እየወጣች ትረብሻለች፤ ስላት ከግቢው መካከል ካለችው አደባባይ ቁጥጥ ብላ በመውጣት ትደንሳለች ፤ትጫወታለች . . .ከግቢው ወጥታ በአስፓልቱ መሃል ቆማ መኪና እንዲገጫት ስትታገልና ሲመልሷት ተመልክቻለሁ ! መናገር መጋገር የማትፈልገው ሌላዋ ዘርፈጥ ብላ ተቀምጣና ነሁልሳና በራሷ አለም የነጎደቸው እህት ልብን በሃዘን ትሰብራለች፡፡

በሌላኛው መጠለያ ያሉትን ጨምሮ ዓዕምሯቸው የተነካና ያበዱትን እህቶች ቁጥር ከአስር በላይ እየሆነ ሲመጣ ጤነኞችና ህሙማኑ በአንድ ላይ ባሉባት መጠለያ ያበዱት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ያላበዱት ለእብደት መዳረጋቸውንና እንባቸውን እያዘሩ የገለጹልኝ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ነው ፡፡ በሪያድ ያለውን ሁኔታ ያጫዎተኝ ወዳጀ ከጅዳው በከፋ ሁኔታ ዜጎች ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን ያመላክታል፡፡ እንዲያው በአጠቃላይ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች ስለ ዜጎች መብት ገፈፋ በመረጃ እየተደገፈ ሲነገር የሆነ ያልሆነውን መረጃ ከመስተት ተቆጥበው በትክክል በዜጎች ላይ ለሚደርሰውና በአስፈሪ ሁኔታ እየተጋረጥነው ያለውን ችግር ለመመከት ህዝብ ተጠርቶ የሚመክርበት መንገድ አለያም ማዕከላዊ መንግስት የጉዳዩን አሳሳቢነት እንዲረዳና በዚህ ረገድ እርምጃ እንዲወሰድ ጠንከር ያለ ትክክለኛ መረጃ ሊሰጥ ይገባል፡፡

አዲሱ አመት ነጋ ጠባ የምናነሳ የምንጥለው የኢዮጵያውያን መከራ የሚቀልበት ያደርገው ዘንድ ምኞቴ ደግሜ በመግለጽ የዛሬውን ወግ ላብቃ !

ቸር አሰማን !

ነቢዩ ሲራክ

ECADF.COM

የዘመኑ ፖለቲካ አስቂኝ –ብዙ ያልተነገረለት የኢህአዴግ ራዕይ

ምኒሊክ ሳልሳዊ

የዘመኑ ፖለቲካ አስቂኝ ነገር ይመስለኛል(ደንበኛ ኮሜዲ!) አስቂኝነቱ ግን ለፖለቲከኞቹ አይደለም፤እነሱማ ስራቸው ነው (ማን ነበር ንጉስነት እንጀራዬ ነው ያለው?) አስቂኝነቱ ለእኛ ነው- ለተደራሲያኑ!!(በጥበብ ቋንቋ መግለፄ እኮ ነው) ፖለቲካን እንደ ኮሜዲ ቲያትር አስባችሁት ታውቃላችሁ? (የምርም እኮ ኮሜዲ ነው!) መቼም የፖለቲካ ኮሜዲው ደራሲያንና ተዋንያን ማን እንደሆኑ አይጠፏችሁም ብዬ አስባለሁ፡፡ ፖለቲከኞቹ ናቸዋ! ተደራስያኑ ደግም ምስኪኑ ህዝብ! (“ልማታዊ ህዝብ” ይባላል እንዴ?) ለነገሩ “የበይ ተመልካች” ወይም ታዛቢ ብንባልም አይከፋንም (ሃቅ ነዋ!) እናላችሁ —- ፖለቲከኞቹ ይበላሉ፤ እኛ ኩራዝ እንይዛለን፡፡ ፖለቲከኞቹ ይወስናሉ፤ እኛ እንሰማለን፡፡ ምን ይደረግ … እጣ ፈንታችን እኮ ነው፡፡ (ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም!) ለነገሩ ተሰጥኦ ከሌለን ቀሽም ኮሜዲ ነው የምንሰራው (አያስቅ አያስለቅስ!) አያችሁ የፖለቲካ ኮሜዲ ችሎታ ይጠይቃል – ልዩ ተሰጥኦ!

እኔ መቼም የፖለቲካ ኮሜዲ ዘመን መሆኑ በጣም ነው ደስ ያለኝ (ምርጫ የለኝማ!) ግን እኮ በምናብ ባቡር (እውነተኛው ባቡር እስኪጀመር–) ወደ ኋላ ሸተት ብላችሁ የ60ዎቹን የፖለቲካ ተውኔቶች ብትመረምሩ የአሁኑን የፖለቲካ ኮሜዲ “ተመስገን!” ማለታችሁ አይቀርም፡፡ መቼም ከፖለቲካ ትራጄዲ የፖለቲካ ኮሜዲ ይሻላል፡፡ እኔ በበኩሌ ከምናዝን ቢቀለድብን እመርጣለሁ (Choosing the lesser evil እንደሚባለው!)

አንዳንዶች የቀድም ጠ/ሚኒስትር “ግልባጭ” የሚሏቸው (እሳቸውም የእሱ “ግርፍ” ነኝ ብለዋል እኮ) የኢፌዲሪ ጠ/ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ ከኢቴቪ ጋር የመጀመርያውን ቃለምልልስ ሲያደርጉ፤ አገራችን ከባለ ሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ ዕድገት ባሻገር፣ በመንገድ ግንባታና ማስፋፊያ ሥራዎችም ከአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌላት ቀዳሚዋ አገር መሆኗን ሲገልፁ፤ (ሲያበስሩ በሚል ይተካልኝ!) ነፍሴ እንዴት በደስታ ጮቤ እንደረገጠች አልነግራችሁም፡፡ ከምሬ እኮ ነው! (ካልማልኩ አታምኑኝም?) ወዲያው ግን … አንድ “ነገረኛ ጥያቄ” ከአዕምሮዬ ጥግ ብቅ አለና ደስታዬን ነጠቀኝ። በቃ በጣፋጭ ህልም ከተሞላ የጥጋብ እንቅልፍ ላይ የተቀሰቀስኩ ነው የመሰለኝ፡፡ “በመንገድ ግንባታና ማስፋፊያስ ቀዳሚ ሆንን … በዲሞክራሲ ግንባታስ? በመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ምስረታስ? በነፃና ፍትሃዊ ምርጫስ? በፕሬስ ነፃነትስ? የህዝቦችን ሰብአዊ መብት በማክበርስ?–” ደህና የነበርኩት ሰውዬ የነፃነት ታጋይ ሆኜላችሁ ቁጭ አልኩ፡፡ አይገርማችሁም? ያለ ዕቅድና ያለ ፍላጐቴ እኮ ነው በእነዚህ ሁሉ የጥያቄዎች ጐርፍ የተጥለቀለቅሁት፡፡ ታዲያ ምን እንደቆጨኝ ታውቃላችሁ? ያንን ጠ/ሚኒስትሩን ኢንተርቪው ያደረገ የኢቴቪ ጋዜጠኛ ባገኝ ኖሮ “ጠይቅልኝ” ብዬ እማፀነው ነበር (ለእኛ እስኪገኙ ልማታዊ ጋዜጠኛ ልጠቀም ብዬ እኮ ነው!)

በነገራችሁ ላይ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ቶፕ 10 ውስጥ መግባቷን ሰምታችኋል አይደል? (ሪፖርቱ ኢህአዴግ አይልም – ኢትዮጵያ እንጂ!) ከዓለም ጋዜጠኞችን በብዛት በማሰር ቁጥር አንድ አገር ማን መሰለቻችሁ? ቱርክ ናት ይላል- ሪፖርቱ። 49 ጋዜጠኞቿ ቤታቸው ወህኒ ሆኗል፡፡ ኢራን 45 ጋዜጠኞችን አስራ በሁለተኛነት ትከተላለች፡፡ ቻይንዬ ደግሞ 32ቱን የፕሬስ ሰዎች ሸብ አድርጋ ሶስተኛ ደረጃ ይዛለች፡፡ አራተኛዋ አገር ዘመዳችን ኤርትራ ስትሆን 28 ጋዜጠኞችን ዘብጥያ አውርዳለች፡፡ ኢትዮጵያ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች – ጋዜጠኞቿን በማሰር፡፡ በነገራችሁ ላይ መንግስታት ምን እንደነካቸው አይታወቅም ጋዜጠኞችን እንደጦር መፍራት ጀምረዋል፡፡ እናም ዘንድሮ ከ1990 ዓ.ም ወዲህ በመላው ዓለም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞች መታሰራቸውን ነው ሪፖርቱ ይፋ ያደረገው – በጠቅላላው በ27 አገራት ውስጥ 232 ሪፖርተሮች፣ የፎቶ ጋዜጠኞችና ኤዲተሮች ለእስር ተዳርገዋል (ስልጣን ሳይሆን መረጃ ጠይቀው!)

እኔ የምላችሁ ግን … ኢቴቪ የሚዲያ ዳሰሳ የሚለው ፕሮግራሙ ላይ የስያሜ ለውጥ አደረገ እንዴ? የሚዲያ ዳሰሳው ቀርቶ የኒዮሊበራል አቀንቃኝ አገራት የተራራቁበትን “ልማታዊ መፃህፍት” እያስኮመኮመን እኮ ነው፡፡ እኔ ግን አንድ ሃሳብ አለኝ – ስለ ፕሮግራሙ፡፡ ሃሳቤ በይዘቱ ወይም በአቀራረቡ ላይ አይደለም፡፡ በፕሮግራሙ ርዕስ ወይም ስያሜ ላይ ብቻ ነው! እንደኔ እንደኔ የሚዲያ ዳሰሳም ሆነ የመፃህፍት ዳሰሳ የሚለው ስያሜ ፈፅሞ ፕሮግራሙን አይመጥንም፡፡ እውነቴን እኮ ነው … ጋዜጠኞቹ የሚያቀርቡልን እኮ ዳሰሳ ሳይሆን የስብከትና የፕሮፓጋንዳ ቅይጥ ነገር ነው (ሚስቶ እንደሚሉት) ስለዚህ ለምን በኢቴቪ የፕሮፓጋንዳና የቅስቀሳ ዲፓርትመንት ሥር “የልማታዊ አስተሳሰብ ማስፋፊያ ፕሮግራም” አይባልም? የሚል ሃሳብ አለኝ (ዲፓርትመንቱ ከሌለ ይቋቋማ!) ልብ አድርጉ! እንዲህ ያሻኝን የምናገረው ኢቴቪ የእኛ የሰፊው ህዝብ ሃብትና ንብረት ነው ብዬ ነው (ለግል ባለሃብት ተሸጠ እንዳትሉኝ?)

አንዳንዴ ተቃዋሚዎች፤ “ኢህአዴግ ሚዲያውን በሞኖፖል ተቆጣጥሮታል” ሲሉ እሰማና እኛ ሳናውቅ ንብረታችን ተሸጠ? ብዬ እደነግጣለሁ (ኢህአዴግ ገዝቶት እንዳይሆን ብዬ እኮ ነው!) አለዚያማ ማን የማንን ንብረት ይቆጣጠራል? ወይም ደግሞ እንደ መሬት “የህዝብና የመንግስት” ነው ይበሉንና አርፈን እንቀመጥ፡፡ እኔ የምለው ግን —- የፖለቲካ ምህዳር የማን ንብረት ነው? “የህዝብና የመንግስት” ነው እንዳትሉኝና እንዳታስቁኝ (የዘመኑ ፖለቲካ ኮሜዲ ነው አልተባባልንም?) ኢህአዴግ ግን አንዳንዴ ያበዛዋል፡፡ ምናለ እቺን እንኳ ለተቃዋሚዎች ቢለቅላቸው (የፖለቲካ ምህዳር መሬት መሰለው እንዴ?)

በነገራችሁ ላይ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ምስጉን ሠራተኞች ሰሞኑን መሸለማቸውን ስሰማ እንዴት ደስ እንዳለኝ አታውቁም፡፡ የህዝብ ሽልማት ቢቀርባቸው የድርጅቱን እንኳን ያግኙ እንጂ! (ከሁለት ያጣ ሆኑ እኮ) ይሄን ደስታዬን ለአንዱ “ሟርተኛ” ወዳጄ ሳጋራው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ? (“ደርግም እኮ “ኮከብ ሠራተኞች” እያለ ይሸልም ነበር!”) ምኑ ጨለምተኛ ነው ባካችሁ?

እናንተ— ሰሞኑን የሰማኋት አንዲት ዜና እንዴት ያለች የፖለቲካ ኮሜዲ መሰለቻችሁ! የዜናዋን ፍሬ ነገር ልንገራችኋ — ባለፈው ሳምንት ወደ ሩዋንዳ የተጓዙት ጠ/ሚኒስትራችን፤ ከሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ጋር መወያየታቸውን የዘገበው ኢቴቪ፤ ፓርቲያቸው ኢህአዴግ ከሩዋንዳዉ ገዢ ፓርቲና ከሌሎች ተራማጅ አስተሳሰብ ያላቸው የአፍሪካ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁሟል (ዘይገርም ነገር!) የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን የህይወት ታሪክ በሚተርከው “የነጋሶ መንገድ” የተሰኘ መፅሃፍ ላይ ያነበብኩትን አንድ መረጃ ካልነገርኳችሁ የዚህን ዜና አንደምታ ልታገኙት አትችሉም፡፡ ኢህአዴግ ገና ድሮ በትግል ላይ ሳለ (ከስልጣን ጋር ሳይተዋወቅ ማለት ነው) ስለነበረው ራዕይ ነጋሶ ሲናገሩ፤ “ኢህአዴግ በአፍሪካ ግዙፍና ተፅዕኖ ፈጣሪ ገናና ፓርቲ የመሆን ራዕይ” እንደነበረው ገልፀዋል፡፡ አሁን ትንሽ ተገለጠላችሁ? እኔ ሳስበው ኢህአዴግ ሩዋንዳ ድረስ ሄዶ ከባዕድ ፓርቲ ጋር ተስማምቶ የተመለሰው እቺን የጥንት ራዕይ ለማሳካት ይመስለኛል፡፡ አንዳንዶች “እዚህ መዲናዋ እምብርት ላይ 34 ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንደራደር እያሉ ሲማጠኑት ሩዋንዳ ተሻግሮ መደራደር ምን ዓይነት ንቀት ነው?” ሊሉት ይችላሉ (ሲሰማቸው አይደል!)

አያችሁ — ኢህአዴግ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መስራትን በተመለከተ ሁለት ራዕዮች እንዳሉት የደረስኩበት ሰሞኑን ነው – አገራዊና አህጉራዊ ይባላል። ቅድም እንደነገርኳችሁ አህጉራዊ ራዕዩ በአፍሪካ ገናና ፓርቲ መሆን ነው – ተፅዕኖ ፈጣሪ ግዙፍ ፓርቲ! አገራዊ ራዕዩስ? እንግዲህ ራዕይ ይሁን አይሁን አላውቅሁም እንጂ ከ2002 ምርጫ በኋላ “አዲስ ራዕይ” በተሰኘው የራሱ ልሳን ላይ እንዳሰፈረው ተቃዋሚዎች እንዳያንሰራሩ ለማድረግ በርትቶ እንደሚታትር ጠቁሟል (ጨለምተኛ ራዕይ ይሏል ይኼ ነው!)
አህጉራዊ ራዕዩን በተመለከተ ትንሽ የሚያሰጋኝ ምን መሰላችሁ? ኢህአዴግ ከአፍሪካ ልማታዊ ፓርቲዎች ጋር ጥምረት ወይም ግንባር ከመሰረተ በኋላ እዚህ አገር እንዳደረገው “ገናና ፓርቲ ነኝ” ብሎ ሸብ ለማድረግ እንዳይሞክር ነው (እነሱስ በእጃቸው ሙቅ ይዘዋል እንዴ?) ለነገሩ ኢህአዴግም ቢሆን አብዛኞቹ የአፍሪካ ገዢ ፓርቲዎች እንደሱው የነፃነት ታጋዮች እንደነበሩ የሚዘነጋው አይመስለኝም (ሁሉም በልቡ ገናና ነኝ ባይ እኮ ነው!) ምናልባት ዘንግቶት ችግር ላይ ከወደቀም የሚያዝንለት የለም፡፡ “የአገሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጡር ነው” እየተባለ መሳለቂያ ነው የሚሆነው፡፡

እኔ የምለው ግን— ከአገሩ አልፎ በአህጉር ደረጃ ገናና የመሆን ህልም ያለው ፓርቲ እንዴት የኮሙኒኬሽን አቅምና ብቃት አይኖረውም? ኢህአዴግ እኮ በኮሙኒኬሽን “Poor” ነው (ድክም ያለ!) አንዴም እንኳ የመግባባት ብልሃቱን ሳያሳየን ይኸው 21 ዓመት ሞላው። እንኳንስ “ጠላቴ” ብሎ ከፈረጃቸው ተቃዋሚዎች ጋር ቀርቶ ከእኛ ከህዝቦቹ ጋር እንኳ ሁሌ አይደል የሚላተመው? (ደግነቱ አጥፍቻለሁ ማለት ይወዳል!) እውነቴን ነው የምላችሁ —- ኢህአዴግ ከአገር በቀሎቹ ፓርቲዎች ጋር እንዲህ ዓይንና ናጫ ሆኖ አህጉራዊ ራዕዩን ለማሳካት ቢነሳ ፈፅሞ አይሳካለትም፡፡ ለማንኛውም ግን ያስብበት ለማለት ያህል ነው፡፡

መንግሥትና ቤተ ክህነቱ፣ በሁለቱ ሲኖዶሶች መካከል የቀጠለው ድርድር፣ የፓትርያሪክ ምርጫ ውዝግቡ ወዴየት እያመራ ይሆን!?

 

Abuna Merkorios Patriarch of the Ethiopian Orthodox Church

እሁድ ታህሳስ 21 ቀን በቶሮንቶ በተከበረው አመታዊው የታህሳስ ገብርኤል በዓለ ንግስ ላይ ፓትሪያርክ መርቆሬዎስ ለህዝቡ ቡራኬ ሲሰጡ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በብዙ ሚሊዮን ሚቆጠር ምእመናን እንዳላት ይታመናል፡፡ ይህች አንጋፋና ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ታሪክ፣ ታላቅ ሥልጣኔ፣ ባህልና ቅርስ መሠረት ለመሆን የቻለች የሃይማኖት ተቋም ናት፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ ለኢትዮጵያ ነፃነት፣ ሉዓላዊነትና አንድነት የነበራት ሚና እጅግ የጎላ ነው፡፡ ይኸው ሚናዋ ከአፍሪካ እስከ አሜሪካ፣ ጃማይካና ካረቢያ ድረስ ተሻግሮ ለብዙ ሚሊዮን የምድራችን ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ትግል ፋና ወጊ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሆና ለመቆጠር የበቃችበትን ልዩ ታሪካዊ ክብርና ሥፍራን ለመጎናጸፍ አስችሏታል፡፡

ይህን ቤተ ክርስቲያኒቱ ለነፃነት፣ ለፍትህ እና ለሰው ልጆች እኩልነት መስፈን የነበራትን ታላቅ የሆነ መንፈሳዊና ታሪካዊ የሆነ ጉልህ ሚና በተለይ በደቡብ አፍሪካውያን የጸረ-ባርነትና የጸረ-አፓርታይድ ትግል ወቅት ለጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን የነፃነት ፋኖዎች እንደ ትልቅ ስንቅና ወኔ ሆኖ አገልግሏል፡፡

ይህን ታሪካዊ እውነታ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት ታቦ ኢምቤኪ እ.ኤ.አ በ2010 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሕግ የክብር ዶክትሬት በሰጣቸው ወቅት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግራቸው እንዲህ በማለት ነበር በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ራሳቸውን ጨምሮ፣ አፍሪካውያንና መላው ጥቁር ሕዝብ የሚሰማውን ክብርና ኩራት በእንዲህ መልኩ የገለጹት፡-

…Thus would the authentic African Church serve as a repository of the aspirations of all Africans for freedom and respect for their cultures, their identity and their dignity.

The African National Congress of South Africa, the oldest modern national liberation movement on our continent, was born out of our country’s Ethiopian Churches. Indeed the African nationalism which drove our national liberation movement was described as Ethiopianism.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ጥንታዊ የሆነ እምነቷ፣ ሥርዓቶቿና ትውፊቶቿ እንደ ሌሎች አፍሪካ አገራት የምዕራባውያን ቀኝ ገዢዎች አሻራ ያለረፈበት በመሆኑ Reconciliation within the Ethiopian Orthodox Tewahedo Churchአፍሪካዊት እናት ቤተ ክርስቲያን (An Independent African Mother Church, African Indigenous Church)የሚል ክብርና ቅጽል እንድትጎናጸፍ አድረጓታል፡፡

የክርስትና ሃይማኖት ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ወቅት ኢትዮጵያውያኑ ነገሥታትና ሊቃውንት ክርስትናውን ከሕዝባቸው ታሪክ፣ ባህል፣ ቅርስ፣ ልማድና ትውፊት ጋር በማጣመር ውብና ማራኪ እንዲሆን አድርገው እንዳቆዩት በርካታ መርጃዎችን መዘርዘር ይቻላል፡፡

ዛሬ በሌላው ክርስቲያን ዓለም የማናየውን ይህን ጥንታዊና ሐዋርያዊ የሆነ ክርስቲያናዊ ባህልና አምልኮ ምዕራባውያኑ ቱሪስቶችና ተጓዦች ብዙ ሺህ ዶላራቸውን ከስክሰው ሊያዩት በየዓመቱ ወደ ኢትዮጵያ ይጎርፋሉ፡፡ ይህ ልዩ የሆነው የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊው ሥርዓቷ፣ የወንጌል መሰረት ያለው ክርስቲያናዊ ባሕሏ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ምእመኖቿ እና ተከታዮቿ የኢትዮጵያዊ ማንነትና ብሔራዊ ኩራት መገለጫ ሆኖ የመዝለቁ ምስጢር ይኸው ይመስለኛል፡፡

በተመሳሳይም የእስልምና ሃይማኖትም ብንመለከት ምንም እንኳን ከሌሎች አገራት ቀድሞ ወደ አገራችን የመጣ ቢሆንም ሃይማኖቱ ልክ እንደ ክርስትናው ሁሉ በኢትዮጵያዊ ታሪክ፣ ባህል፣ ቅርስ፣ ወግና ትውፊት ላይ ውብ የሆነ ጥምረትን ፈጥሮ ነው እዚህ የደረሰው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ ‹‹የሃይማኖቶች መቻቻል ምድር›› ተብላ እንድትጠራ ያደረገውም እነዚህ ሁለት አንጋፋ ሃይማኖቶች በማይበጠስ የኢትዮጵያዊነት ፍቅር፣ አንድነት፣ የጋራ ታሪክ፣ ባሕልና ቅርስ ላይ የተሳሰሩ በመሆናቸው ይመስለኛል፡፡

ከዚህም የተነሳ ኢትዮጵያያን ሙስሊሞች እንደ ሌላው ዓለም ወይም በታሪክ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ልዩ ትስስርና ቅርበት ካለን ግብፅም ሆኑ ሌሎች ጎረቤቶቻችን አፍሪካውያን አገሮች የእስልምና ሃይማኖቱን ብቻ እንጂ የዐረባዊነትን ቋንቋና ባህል ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሊለብሱትና ሊወርሱት አልፈቀዱም፡፡ ይኽም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን የተለዩ ያደርጋቸዋል፡፡

እንደ እስልምና ሃይማኖት ምሁራን አገላለፅ (Ethiopians only Islamized but not Arabized) በማለት በአጭር ቃል ታሪካዊ እውነታውን ይገልጹታል፡፡ ይህም ሕዝባችን ስላለው ጠንካራ ብሔራዊ ማንነትና ኩራት እንዲሁም ዘመናት ያላደበዘዙት የጋራ ታሪክና ቅርስ ያለው ኩሩ ሕዝብ እንደሆነ ትልቅ ማሳያ እንደሆነ እገምታለሁ፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም ዓይነት ሃይማኖት ቢኖረው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅርና በእግዚአብሔርም ላይ ያለው እምነት ጠንካራ ነው። የበርካታ ተጓዦችና አጥኚዎች በጥናታቸው ‹‹ኢትዮጵያውያን ሃይማኖተኛ ሕዝቦች የሚበዛባት አገር ናት፡፡›› ወደሚለው ድምዳሜ የሚያደላ ነው፡፡

ይህ ሕዝብም በታሪኩ ሃይማኖቱን የራሱና የግሉ አድርጎ በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር ተዋዶና ተከባብሮ የኖረ ሕዝብ ነው፡፡ በዚህም ከራሱ አልፎ ለሌላው ዓለም ተምሳሌት የሆነበትን እርስ በርስ ተዋዶና ተከባብሮ የመኖርን አንጸባራቂ ታሪክ የፃፈ ሕዝብ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ይህ የምንኮራበት የሁለቱ አንጋፋ የሃይማኖት ተቋማት ታሪክ ሙሉ በሙሉ አልጋ በአልጋ ነበር ብለን እንዳንደፍር የሚያደርጉ በተለያዩ ዘመናት በሁለቱ ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የተከሰቱ መለያየቶች፣ ግጭቶችና ጦርነቶች በአገራችን ታሪክ መዛግብት ውስጥ ተመዝግቦ አለ፡፡

በሃይማኖትና በፖለቲካ አላቻ ጋብቻ፣ የተፈጥሮ ሀብትና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ምክንያት ያደረጉ በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖቶች ሕዝቦች መካከል የተነሱ ጦርነቶችና ግጭቶችም እንደነበሩ ማስታወስም ግድ ይለናል፡፡ እነዚህን በአገራችን ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው የተነሱ ግጭቶችንና ጦርነቶችን መንስዔያቸውን፣ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤታቸው ለመተንተን የሚሞከር አይሆንም፡፡

አነሳሴም በኢትዮጵያ ውስጥ አንጋፋ ስለሆኑት ስለ ክርስትና እና እስልምና ሃይማኖት የአብሮነት ታሪክና ግጭት ለመተንተን አይደለም፡፡ ለመግቢያ ያህል ስለእነዚህ ሁለት አንጋፋ ሃይማኖቶች የጠቀስኩት ለጽሑፌ ጥሩ መንደርደሪያ፣ ግልፅና መጠነኛ የሆነ ታሪካዊ እይታን ይሰጠናል በሚል ቅን ግምት ነው፡፡

የዛሬው ጽሑፌ ዋና ማጠንጠኛ አሳብ የሚከተሉት ናቸው፡-

  • የመንግሥትና የቤተ ክህነቱ ጋብቻና ፍቺ ምን መልክ ነበረው፣ አሁንስ የሁለቱ ተቋማት ግንኙነት ምን ይመስላል? የነገይቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ቤተ ክርስቲያን የመምራት ኃላፊነት የማን ይሆናል?
  • ለቤተ ክርስቲያኒቱ ለሁለት መከፈል ምክንያት ናቸው የተባሉት የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን እልፈት ተከትሎ በስደት ከሚገኙት አባቶች ጋር የተጀመረውን ድርድር ወደ ፍፃሜ ለማድረስ እየተደረጉ ያሉ ውይይቶችስ ምን ፋይዳ ሊኖራቸው ይችላል?
  • እንዲሁም የቀድሞው ፓትሪያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው ይመለሱ፣ ወይስ ሌላ ፓትርያሪክ ይመረጥ በሚሉትና፤ በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያኒቱ የነገ ዕጣ ፈንታ ዙሪያ እየተናፈሱ ያሉ ስጋቶችና ፍርሃቶች መነሻቸው ምን ሊሆን ይችላል?
  • በፓትርያሪክ ምርጫው ላይ አንዳንዶች ስውር የሆነ የመንግሥት ጣልቃ ገብነትና ጫና አለ በሚል እየተንሸራሸሩ ባሉ አሳቦችና ስጋቶች ዙሪያ እኔም የበኩሌን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የትናንት በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ከሚጠቀሱ ታሪኮቿ በመነሳት በቅን መንፈስ ላይ የተመረኮዘ ጥቂት የውይይት አሳቦችን ለማጫር ነው፡፡

የቤተ መንግስቱና የቤተ ክህነቱ ጋብቻና ፍቺ ከትናት እስከ ዛሬ

የክርስትና ሃይማኖት ወደ አክሱም ግዛት ከገባ በኋላ በወቅቱ ከነበረው የክርስትና መስፋፋት ባህርይ ጋር በተቃራኒው መልኩ የመንግሥት ሃይማኖት የመሆን ዕጣ ፈንታ ነበር የገጠመው፡፡ በአራተኛው መቶ ክ/ዘመን መባቻ ጀምሮ የተጀመረው የቤተ መንግሥትና የቤተ ክህነት ታሪካዊ ግንኙነትና ዝምድና ውሉ የሚመዘዘውም ከዚሁ ታሪካዊ ክስተት ጀምሮ ነው፡፡

ከዛን ጊዜ ጀምሮ በቤተ መንግሥትና በቤተ ክህነት መካከል የነበረውን ግንኙነት ለመተረክ የሚቻል አይደለም፡፡ ስለዚህም በተቻለኝ መጠን ወደ ተነሳሁበት ዋና የጽሑፌ አሳብ የሚያደረሰኝን የቅርቡን ዘመን ብቻ ታሪክ በማንሳት ጽሑፌን ልቀጥል፡፡

የመንግሥትና የሃይማኖት ጋብቻ እስከ 1966ት የደርግ ወደ ሥልጣን መምጣት ድረስ መሪዎች/ነገሥታቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባል መሆን እንዳለባቸው በሕገ መንግሥት ጭምር የተደነገገ ነበር፡፡

ይህ የቤተ ክህነቱና የቤተ መንግሥቱ ጋብቻ በደርግ ዘመን መንግሥት በግልፅ መፍረሱ ቢገልፅም፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በአገሪቱ ሕዝቦች ታሪክ፣ ባሕል፣ ሥልጣኔና ቅርስ እንዲሁም የዕለት ተዕለት የማኅበራዊ ኑሮ መስተጋብር ውስጥ ካላት ሰፊ ድርሻና አሻራ የተነሣ መንግሥትና ቤተ ክህነቱ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ በሆነ መንገድ የመሳሳቡ ነገር መጠኑ ቀነሰ እንጂ ሊጠፋ አልቻለም ነበር፡፡

ደርጉ ‹‹መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡›› ባለ ማግስት በወቅቱ የሚያራምደውን እግዚአብሔር የለሽ ሶሻሊስታዊ ሥርዓት በመደገፍ ረገድ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች እንዳሻው ለማሽከርክር በፈለገበት ወቅት፣ የአንተ ወሰን እስከዚህ ድረስ ነው በሚል በተነሳ አለመግባባት የተነሣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለተኛ ፓትሪያሪክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ለእስር፣ ለአንግልትና ለሞት እንዲዳረጉ ሆነዋል፡፡

ይህ ለሺህ ዘመናት ቤተ ክህነቱና ቤተ መንግሥቱ የተቆራኙበት ታሪካዊ እትብት በአንድ ጀምበር ቆርጦ በመጣል ወደፊት ለመራመድ የማይቻል መሆኑን የእዚህ የደረግ ድፍረት የተሞላበት እርምጃ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በተጨማሪም በሕዝቡ ፖለቲካዊ ስነ ልቦና ላይ የራስዋ የሆነ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ አሻራ ያላትን ቤተ ክርስቲያን ከዳር አውጥቶ መንግስትን መምራት አዳጋች መሆኑን ይህ የደርጉ አብዮታዊ እርምጃ በግልፅ እውነታውን የሳየ እንደሆነ አስባለሁ፡፡

በሕዝብ የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ስነ ልቦና ውስጥ የራሷ የሆነ ትልቅ ተጽእኖ ያላትን ይህችን ተቋም በተዘዋዋሪ መንገድ በእጁ ለማስገባት ደርግ ፈርጣማ ክንዱን ቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ አሳረፈ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን በመቆጣጠር በእርሷም በኩል ሕዝቡን ተገዢው ለማድረግ መሪዋን አሰረ፣ ገደለ፡፡ ውጤቱም ዘግናኝ የሆነ የትውልድ እልቂትና ፍጅትን ነበር ያስከተለው፡፡

ይህ የደርጉ እርምጃ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊው መልኩ የቆየው የቤተ መንግሥቱና የቤተ ክህነቱ የግንኙነት ሰንሰለት  በቀላሉ በአንድ ጀምበር ሊቆረጥ አለመቻሉን ሊያሳዩን ከሚችሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ አንዱና ተጠቃሹ ነው፡፡

የቤተ መንግሥቱና የቤተ ክህነቱ ተቋማት እርስ በርሳቸው እንደ ተቃራኒ የማግኔት ዋልታዎች የሚሳሳቡበት ምክንያቱ ቤተ ክርስቲያኒቱ በኢትዮጵያ ታሪክ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ ሕይወትና ፖለቲካ ውስጥ ከነበራትና አሁንም ካላት ተጽእኖ የተነሳ እንደሆነ ብዙዎች የቤ/ቱ ምሁራንና ታሪክ አጢኚዎች ይስማማሉ፡፡

በዚህና በአያሌ ተዛማጅ ምክንያቶች ቤተ ክርስቲያኒቱ በአገሪቱ የሚከሰቱ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ ተጽእኖ እንዳላት ሁሉ እርሷም ከተለያዩ አቅጣጫዎችና ከመንግሥት በሚመጡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ኩነቶች ተጽእኖ ስር መሆኗ ግን አልቀረም፡፡ እናም መንግሥትና የቤተ ክህነት ግንኙነት አዎንታዊና አሉታዊ ውጤቱን እያስመዘገበ ዘመናትን ተሻግሮ  አሁን የሚገኝበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክ የሚያጠኑ የታሪክ ምሁርና ተመራማሪ የሆኑ የአንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቋም ባልደረባ እንደሚሉት፣ ‹‹ቤተ ክርስቲያኒቷ ራሷን ቻለች በተባለችባቸው ሃምሳ ዓመታት ከግብፅ ጥገኝነት ብትላቀቅም በመንግሥት ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኛ ወደ መሆን መሸጋገሯን፡፡›› በጥናታቸው ይገልፃሉ፡፡

እኚሁ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር እንደሚያስረዱት የቤተ ክርስቲያኒቱን የሃምሳ ዓመታት እራሷን የመስተዳደር ጉዞ ‹‹ፍፁማዊው ከነበረው የውጭ ጥገኝነት፣ ፍፁማዊው ወደሆነው የውስጥ ጥገኝነት የተሸጋገረበት ነው፡፡›› በማለት በአጭር ቃል ይገልጹታል፡፡

‹‹ቤተ ክርስቲያኒቱ ከግብፃውያን ቅኝ ግዛት ተላቃ በንጉሡም ሆነ በደርግ ዘመነ መንግሥት አንፃራዊ በሆነ መልኩ ውስጣዊ አስተዳደሯን በተመለከተ ራሷን ችላ በነፃነት ማከናወን የምትችልበት ዕድል ማግኘቷን ያሰምሩበታል፡፡ ይህን አንፃራዊ በሆነ መንገድ ራሷን በነፃነት የማስተዳድር ዕድል ከ1983ቱ የመንግሥት ለውጥ ጋራ ሲመጣ ግን ብቻውን አልመጣም፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷ ራሷን ሙሉ በሙሉ የማስተዳደር አቅሟን በሚገባ ሳታዳብርና በቂ ዝግጅት ሳታደርግ ነበር ነፃነቱ የደረሰባት ይላሉ፡፡›› እኚሁ ምሁር፡፡

የታሪክ ተመራማሪው እንደሚሉት በደርግ እጅ የተገደሉት አቡነ ቴዎፍሎስ የጀመሯቸው የተቋማዊ አሰራር ውጥኖች ቢኖሩም ራስን በነፃነትና በውጤታማነት ለማስተዳደር በሚያስችል ደረጃ ሳይዳብሩ ቀርተዋል፡፡

የተቋማዊ አሰራሩ ድክመት ባልተቀረፈበት በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ለረጅም ዓመታት በመንበሩ ላይ የቆዩት ፓትሪያሪክ አቡነ ጳውሎስ ከትምህርታቸውና ከውጭ ዓለም ልምዳቸው በመነሳት ስር ነቀል የሆነ ለውጥ ያመጣሉ ተብለው ቢታሰቡም ከበርካታ በመልካም እርምጃ ከሚጠቀሱባቸው ሥራዎቻቸው ባሻገር የተጠበቁትን ያህል የቤተ ክህነቱን ተቋማዊ አሠራርና አሥተዳደር ከመሠረቱ ለመለወጥ ሳይችሉ ቀርተዋል ሲሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምሁራንና የቅርብ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡

ፓትርያሪኩ ይላሉ የአዲስ አበባው ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር ‹‹ከመንግሥት ጋር አላቸው የሚባለው የጠበቀ ግንኙነት መንግሥት በበኩሉ ጣልቃ እንደማይገባ ለማሳየት የቤተ ክርስቲያኒቱን ውስጣዊ ጉዳዮች በሙሉ ለራሷ የተወ በመምሰል በቅኝ አዙር አገዛዝ ‹አስተዳዳራዊ ድክመት ወደ አስተዳዳራዊ ቀውስ እንዲሸጋገር መንገዱን አመቻችቷል› በማለት ይደመድማሉ፡፡

ኢህአዴግ መንግሥትና ሃይማኖትም የተለያዩ ናቸው፡፡ አንዳቸው በአንዳቸው ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም በሚል በግልፅ በሕገ መንግሥቱ ውስጥ አስፍሯል፡፡ እናም የዘመነ ኢህአዲጓ ኢትዮጵያ ለሁሉም ሃይማኖቶች ክፍት መሆኗን በቃልም በተግባርም ያሳየች አገር ሆና ነው ላለፉት ሃያ ዓመታት የተጓዘችው፡፡

ይሁን እንጂ ይህን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ለመተርጎም ግን ገና ብዙ የሚቀረው ቢሆንም፣ የሃይማኖት ነፃነትን በግልፅ የተቀበለችና መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን በሕገ መንግሥቷ ያጸደቀች አገር ግን አለችን፡፡

የኢፌድሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 11 ላይ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ፣ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንደማይገባ ቢገልፅም አልፎ አልፎ በተግባር እየታየ ያለው እውነታ ግን በተቃራኒው እንደሆነ ታዛቢዎችና በርካታ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ጥናት ያደረጉ የምሁራን የጥናት ወረቀቶች የሚጠቁሙት፡፡

በሕገ መንግስት ደረጃ ሃይማኖትና መንግሥት የተለያዩ ናቸው አንዱ በአንዱ ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ አይገቡም ቢባልም፤ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በተመለከተ ግን የኢህአዴግ መንግሥት ትናትናም ሆነ ዛሬ ነፃ ነኝ የሚልበት ድፍረትና ወኔ  ይኖረዋል ብዬ ለማሰብ ግን ፈፅሜ አልደፍርም፡፡ ለዚህም ሙግቴ አንዳንድ አሳማኝ ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡

ኢህአዴግ በሕገ መንግሥቱ ‹‹ኢትዮጵያ ለሁሉም ሃይማኖቶች እኩል ናት፣ የመንግሥት ሃይማኖት የሚባል ነገር የለም፣ መንግስትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡›› ቢልም ወደ ሥልጣን በመጣ ማግስት ወደ ቤተ ክህነቱ ተቋም በድፍረት ዘልቆ በመግባት ያለፈለገውን አውርዶ ያሻውን ለማስቀምጥ የሄደበት መንገድ በወረቀት ላይ ከደነገገው ሕግ ጋር የሚፃረር እንደሆነ ተደጋግሞ የተነሳ ጉዳይ ነው፡፡

እናም አሁንም ድረስ ለእኔና እኔን ለሚመስሉ ለበርካታዎች ቤተ መንግሥቱና ቤተ ክህነቱ ተለያይተዋል የሚባልበት መሰመሩ የቱ ላይ እንደሆነ በግልጽ ለመጠቆም እየተቸገረን እዚህ ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡

የኢህአዴግ መንግሥት ‹‹ህመምተኛ ነኝ፣ አሁን ባለሁበት ሁኔታ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመምራት አልችልም፣ በገዛ ፈቃዴ ሥልጣኔን ለቅቄያለሁ…፡፡›› ብለዋል በሚል ሰበብ ከመንበራቸው እንዲሰደዱ የተደረጉት አቡነ መርቆሪዮስ በሂደት ይኸው እስከ ዛሬይቱ ቀን ድረስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ውስጥ ትልቅ የታሪክ ስብራትና ጠባሳ የሆነ አሳፋሪ ክስተትን ጥሎ አልፏል፡፡

ይህ ክስተት የወለደው መለያየትና መከፋፈልም የሃይማኖት አባቶችን በአብዛኛው የጥላቻ፣ የጠላትነትና የጽንፈኝነት የፍረጃ ፖለቲካ በሚንጠው የአገራችን ፖለቲካ ጎራ አሰልፎ ከቃላት ጦርነት ባለፈ በግልፅ ፖለቲካዊ አቋም እንዲያራምዱ ትልቅ በርን ከፈተ፡፡

ሰሞኑን በተለያዩ መረቦችና በማኅበራዊ ድረ ገጾች ተለቀው ያየናቸው አንድ በአሜሪካ የሚገኙ የሃይማኖት አባት፣ ‹‹በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ስርዓት፣ ፍትህ፣ የሕግ የበላይነትና ብልጽግና መስፈን አማራጩ መንገድ ጦርነት ነው፣ ሌላ የወንድማማቾች እልቂት፣ ሌላ የአንድ እናት ማኅፀን ልጆች ዳግማዊ ፍጅት ነው፡፡›› ብለው ዱር ቤቴ ካሉ ነፍጥ አንጋች ወገኖቻችንን ጋር በረሃ ድረስ ወርደው የተነሱት ፎቶ የሃይማኖት መሪዎቻችን ላሉበት የአቋም መዋዠቅና ኢ-መንፈሳዊ አካሄድ ትልቅ መሳያ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡

ለፍቅር፣ ለሰላም፣ ለምሕረትና ለእርቅ ይቆማሉ የምንላቸው አባቶቻችን አድራሻቸው የጦር ግንባር፣ የእልቂት አውድማ ከሆነ እንግዲህ ምን እንላለን!?

ለእውነትና ለፍትህ ጠበቃ ይሆናሉ የምንላቸው አባቶች እርሰ በርሳቸው ተለያይተውና ተከፋፍለው በቃላት ጦርነት የሚሞሻለቁ ከሆነ ፍፃሜያቸው ምንድን ነው!?

የምሕረትና የእውነት አደባባይ በተባለች በቤተ ክርስቲያኒቱ ዐውደ ምሕረት ላይ ሐሰት ነግሶ፣ ጥላቻ ድል ነስቶ የሚወጣ ከሆነ ምን ማለት ይቻለን ይሆን!?

ቤተ ክህነቱ አሁን ላለበት ቀውስ ተጠያቂው ማነው፡- ራሱ የቤተ ክህነቱ ተቋምና መሪዎቹ ወይስ…?

ዛሬ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላለችበት ዘርፈ ብዙ አስተዳዳራዊ ቀውሶች፣ ሙስና፣ ዝርፊያ፣ ጎሰኝነት፣ ሥርዓተ አልበኝነት፣ የሞራል ውድቀትና ዝቅጠት፣ የመንፈሳዊነት ሕይወት መጥፋት… ወዘተ ተጠያቂው ማነው? ይህ ጽሑፌ ቤተ ክርስቲያኒቱንና የሚመሯትን አባቶች ክብርና ልእልና ዝቅ ለማድረግ ያለመ አድርገው እንዳያዩብኝ አባቶችን፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ተከታዮችንም ጭምር በትህትና ልገልጽላቸው እወዳለሁ፡፡

የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በቅንነት መንፈስ ቤተ ክርስቲያኒቱ ባሉባት ችግሮች ዙሪያ በቅንነትና በግልፅ ለመወያየት መድረክ ለመክፈት ነው፡፡ በዚህም ከትናንት ታሪካዊ ስህተቶቻችንና ውድቀቶቻችን ተምረን በጋራ ለመፍትሔው ለመመካር እንጂ የማንንም ሰብአዊ ክብርና ማንነት ለመንካት ብዬ አይደለም ይህን ጽሑፍ ያዘጋጀሁት፡፡

ወደ ተነሳሁበት ርዕሰ ጉዳይ ስመለስ የቤተ ክህነቱ ተቋም አሁን ላለበት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ዋናው መንስኤ ራሱ ነው፡፡ መፍትሔውም የሚመነጨው ከራሱ ከቤተ ክህነቱ ተቋምና መሪዎቹ እንደሆነ አጥብቄ አምናለሁ፡፡ እስቲ በቅርብ ዘመን ቤተ ክህነቱና መሪዎች የተፈተኑበትን የታሪክ አጋጣሚዎች ከቅርብ የአገራችንና የቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ በመነሳት ለማሳየት ልሞክር፡፡

ቤተ ክህነቱ የራሱን መንፈሳዊ ክብር፣ ኃይል፣ ሥልጣንና ልእልና በመጠበቅ ረገድ ጉልበቴን ያለበትን በርካታ አጋጣሚዎችን እኔና ትውልዴ በተደጋጋሚ ለመታዘብ የቻልንባቸው ወቅቶች ትናንትና ነበሩ፤ ዛሬም ተደቅነውብን አሉ፡፡

የቤተ ክህነቱ ተቋም የሚመሩ አባቶች ይላሉ እውቁ ምሁርና ጸሐፊ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ክህደት ቁልቁለት በሚለው መጽሐፋቸው፡-«ሥጋቸውንየበደሉ፤ ለነፍሳቸውያደሩ» ናቸው ተብሎ ነው በብዙዎቻችን ምእመናን ዘንድ የሚታመነው፡፡የሃይማኖትመሪዎችለጽድቅማለትለእውነትእንዲሁምለፍትሕናለእኩልነትየቆሙናቸውተብሎይታመናል፡፡ ለሀብትናለሥልጣንግድስለሌላቸውከዚህዓለምጣጣውጭናቸውም ተብለው ነው የሚቆጠሩት፡፡

የሃይማኖት መሪዎች ለፍትህ፣ ለስው ልጆች ነፃነትና እኩልነትም ድምፃቸውን የሚያሰሙ የእውነት ጠበቃዎች ናቸው፡፡ ልዩ ክብር በሚያሰጣቸው በመንፈሳዊ ሰብእናቸውና ሥልጣናቸው የተነሣም በእውነትና በፈትህ ተቃራኒ የሚቆሙ መንግስታትን፣ መሪዎችንና ክፉዎችን ሁሉ የመገሰጽና ፊት ለፊት የመቃወም መለኮታዊ ሥልጣን ከላይ ከአርያም የተቸራቸው እንደሆኑ ነው በአብዛኛው ምእመኖቻቸው ዘንድ የሚታሰበው፣ የሚታመነውም፡፡››

ይሁን እንጂ በቤተ ክህነቱ ተቋምና ቤተ ክህነቱን በሚመሩት አባቶች ዙሪያ በእኔ እና በትውልዴ ዘመን እንኳን የታዘብነው እውነታ ግን ከዚህ ተቃራኒ የሆነ ነበር ወይንም ነው፡፡ ደርግ ወደ ሥልጣን በመጣ ማግስት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪ የነበሩትን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን ሲያግዝና በግፍ ሲያስገድል ድርጊቱን በመቃወም ስለ እውነትና ፍትህ ድምፃቸውን ያሰሙ አባቶች እንደነበሩን አልሰማንም፡፡

እንደውም በተቃራኒው አሁን አሁን እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ስለ ቅዱስነታቸው ከመንበራቸው መወገድና መገደል ‹‹የክብር ፊርማቸውን በማኖር ሙሉ ስምምነታቸውን የገለጹ የሲኖዶሱ አባላት አባቶች እንደነበሩ ነው፡፡››

የግድያ እርምጃው ማንንም ከማንም ያለየበት ደርግ በእግዚአብሔር የለሽ አቋሙ ትውልዱን በኮሚኒሰት ማኒፌስቶ ጸበል እያጠመቀ ከሃዲ ሲያደርገውና አብያተ ክርስቲያናትም እንዲዘጉ ሲያደርግ፣ የሃይማኖት ሰባኪያን ወደ ወህኒ ሲወረወሩና ሲረሸኑ ትንፍሽ ያለ አባት ነበር እንዴ!?

በሀገሪቱ የሺህ ዘመን ታሪክ የደመቀ አሻራ የነበራት ቤተ ክርስቲያን ሀገሪቱ በጥፋት ገደል ጫፍ ላይ ቆማ በነበረችበት ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ድምፃቸው ያለመሰማቱ ጉዳይ ምክንያቱ ምን እንደነበር አባቶቻችን አልነገሩንም፤ እኛም ደፍረን አልጠየቅንም፡፡

በተቃራኒው አባቶቻችን በዘመኑ የፖሊቲካ መሪዎች ጋር እጅና ጓንት በመሆን ከወንጌል እውነት ተቃራኒ ለፍትህ፣ ለእውነት፣ በወንድማማቾች መካከል ፍቅርና ሰላም እንዲሰፍን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያሰማሉ ሲባል ድምፃቸውን አጥፍተው በፍርሃት ድባብ አፋቸው ተሸብቦ ያን የመከራ ዘመን ከሕዝባቸው ጋር ለመቆም አልደፈሩም፡፡

አባቶቻችን የግፍንና የጭቆናን ቀምበር ለመስበር ሕዝቡን ከጎናቸው አሰልፈው ግንባር ቀደም በመሆን ለእርቅ፣ ለፍትህ እና ለሰላም መቆም አለመቻላቸውን ትላንትናም ሆነ ዛሬ አይተናል፣ ታዝበናል፡፡

የአንድ እናት ማኅፀን ልጆች እርስ በርሳቸው ሲተራረዱ፣ በቀይ ሽብርና በነጭ ሽብር የራሺያ የተውሶ አብዮት ምድሪቱ በደም አበላ ተመትታ አኬል ዳማ ስትሆን፣ ወንድማማቾች በርዕዮተ ዓለም ልዩነት አንጃ ፈጥረውና እርስ በርሳቸው ተቧድነው ሲተላለቁ መንግሥትን ተው ያለ፣ ወጣቶቹንስ ከልባቸው እንዲሆኑ የመከረና የዘከረ፣ ስለ ሰላምና እርቅ ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማ የሃይማኖት መሪ ነበር እንዴ!?

ይህን የዘመኑን አሰቃቂ ክስተትና የሃይማኖት አባቶች ዝምታን የመረጡበትን እንቆቅልሽ ‹‹ያለመቻቻል ፖለቲካ ሰማዕትነት፡- መቼም እንዳይደገም›› በሚል ሦስት የአገራችን ምሁራን ባቀረቡት የጥናት መጽሔት ላይ የታሪክ ምሁሩ ፕ/ር ባህሩ ዘውዴ ‹‹ቀይ ሽብር በኢትዮጵያ፡- ታሪካዊ ይዘትና አንድምታ›› በሚል ርዕስ ባቀረቡት ጥናታዊ ወረቀታቸው፡-

‹‹በዘመነ ቀይ ሽብር አገሪቷ አስፈሪ የሆነ የሞት መልአክ ባንዣበባት ወቅት ካህናቱና የሃይማኖት መሪዎች እንደ ጥንቱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ባህል ታቦት ተሸክመውና መስቀል ይዘው በመውጣት ስለ ሰላምና ስለ እርቅ ሊሰብኩ ቀርቶ፣ ለራሳቸው ፈርተው ተሸሽገው ነበር፡፡›› በማለት ትዘብታቸውን በመግለፅ በወቅቱ የነበሩትንና አሁንም ድረስ በሕይወት ያሉትን አንጋፋ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች የዛን ቀውጢ ጊዜ የት እንደነበሩ የጠየቁት፡፡

በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት የሰው ደም በከንቱ ሲፈስ፣ ምርጫ 97ትንተከትሎ እንዲያ አገሪቱ ስትታመስ፣ ሮጠው ያልጠገቡ ሕጻናት በአልሞ ተኳሾች ግንባራቸው በጠራራ ጸሐይ እየተመቱ ሲወድቁ፣ የኢትዮጵያውያን ምስኪን ራሄሎች/እናቶች ዋይታና ፣ ኤሎሄታ፣ የፍርድ ያለህ፣ እያሉ እንባቸውን ወደ ጸባዖት ሲረጩ፣ ስለ ሰላም፣ እርቅና እውነት ይቆሙ ዘንድ የተገባቸው አባቶቻችን ለመሆኑ በዛች ቀውጢ ሰዓት ድምፃቸው ምነዋ አልተሰማ?!

ዛሬ ስለ ፍትህ፣ እውነትና ሰላም ይቆማሉ የምንላቸው አባቶቻችን በተቃራኒው መቆማቸውን ስናይ እኛ መንፈሳዊ ልጆቻቸው በእፍረት እንሸማቀቃለን፡፡ ከዛም አልፎ ዛሬ በግልጽ እያየንና እየሰማን ያለነው የሞራል ውድቀቱ፣ ዘረኝነቱ፣ ሙስናው፣ የመንፈሳዊ ሕይወት መጣቱ ጉዳይ ሌላ ትልቅ ቀውስ ሆነ ብቅ ብሏል፡፡ እናም የነገ የቤተ ክርስቲያኒቱ ህልውና ክብርስ ምን ሊሆን ይችላል በሚል በዋይታና በለቅሶ እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ዓይኖቻችንን ወደ አርያም ለማንሳት እንገደዳለን፡፡

አሁን በመሪነት ያሉ አንዳንድ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች በከፍተኛ የአመራር ስነ ምግባር ብልሹነት ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ መናገር እንደ ዜና እንኳን የሚቆጠርበትን ደረጃ ካለፍን ሰንብቷል፡፡ በእነዚህ የሃይማኖት መሪዎችና አባቶች ነን በሚሉ ሰዎች እየተፈጸመ ያለው ድርጊት የእነርሱን ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የማኅበረሰባችንን የሞራል ድቀት፣ የአመራር ዝቅጠትና ራእይ አልባነት የሚያረጋግጥልን ነው፡፡

እንዲህ ዓይነቶቹን የሃይማኖት መሪዎች ማጋለጥ በአንዳንዶች የዋኻን ዘንድ የሃይማኖቱን ወይም ተቋማቱን እንደ ማዋረድ ተደርጎ ይሰበካል ወይም ይቆጠራል፡፡

በሌላ በኩል ይህን አመለካከት ተቋቁሜ ድርጊቱ እንዲታረም እታገላለሁ የሚል የሃይማኖት አባትም ሆነ ምእመን ቢገኝ እንኳን አቤቱታውን የሚያሰማበት መድረክም ሆነ አካል የለም፡፡ ‹‹የሃይማኖት መሪ ቢያጠፋ እንኳን ልንጸልይለት እንጂ እንደ ሥጋውያን ልንጠይቀው አይገባም፡፡›› የሚል እውነት ቀመስ የሐሰት ምሽጋቸውን ይቆፍራሉ፣ ያስቆፍራሉ፡፡

ታዲያ ይህን መሰል ማኅበረሰባዊ ክብራቸውን የሕገ ወጥነትና የኢ-ሞራላዊነት መደበቂያ ያደረጉ የሃይማኖት አባትና መሪዎች ነን የሚሉ እስከ መቼ እንዲህ ይቀጥላሉ፡፡ በዚህ ሁሉ ድቀት፣ ቀውስና ዝቅጠት ውስጥ ያለችው ቤተ ክርስቲየን በአንፃሩ ደግሞ ለትንሳኤዋ የሚተጉ እንደ ንጉሥ ዳዊት ባለ መንፈሳዊነት ‹‹የቤትህ ቅናት በላኝ›› በሚል መንፈሳዊ እልኽና ቁጭት የሚተጉ አባቶችና መሪዎች እንዳሉም አልዘነጋም፡፡

እንደ ነቢዩ ኤልያስም ስለ ቅዱስ መቅደሱና ስለ አምልኮተ እግዚአብሔር በፍፁም ነፍሳቸው የሚቀኑ፣ ከበዓል ነቢያትና በሃይማኖት ካባ ስር ተሸሽገው ካሉ አስመሳዮች ጋር ፊት ለፊት በመግጠም ስለ እውነትና ፍትህ የሚከራከሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች ትላንትና እንደነበሩና ዛሬም እንዳሉ ቅንጣት ያህል አልጠራጠርም፡፡ እንደ ነቢዩ ኤርምያስም እንባቸውን እያፈሰሱ ‹‹አቤቱ እባክህ የሆነብንን አስብ…!›› የሚሉ አባቶችና ምእመናን በመቅደሱ አደባባይና በጓዳ ውስጥ ዛሬም እንዳልጠፉ አምናለሁ፡፡

የተነሳሁበትን የቤተ ክህነቱን ጉዳይ በአንድ ክፍል ለመጨረስ የሚቻል አልሆነም፡፡ ስለዚህም በቀጣይ ጽሑፌ በተለይ በኢትዮጵያውና በአሜሪካው ሲኖዶስ መካከል ሰላማዊ ድርድሩ ወዴየት ያመራ ይሆን፣ የቀድሞው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው ይመለሱ በሚሉና በፓትርያሪክ ምርጫ ዙሪያ የሚነሱትን አስተያየቶችና ውዝግቦች፣ የመንግስትን ስውር እጅና ጫና በተመለከተ በቤተ ክርስቲያኒቱ የቅርብ ታሪክ ላይ በመንተራስ ለመተንተን የሚሞክረውን ጽሑፌን በቀጣይ ሳምንት ለማቅረብ እሞክራለሁ፡፡

ሰላም! ሻሎም!

ደራርቱ ቱሉ ለወያኔ ስራ ጉዳይ ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ሳይሳካላት ተመለሰች

ማለባበስ ይቅር ፣ ማሰመሰልም  ይቅር፣

ውያኔን ለመጣል እንስራ በፍቅር፡፡

ዘረኝነት ይጥፋ ከመካካላችን፣

በኛተጨንቃለች ኢትዮጵያ ሀገራችን፡፡

በሀገራችኝ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የተኩላዎች ቁጥር ከቀን ወደቀን እየጨመረ መምጣቱ የሚታወቅ ነው ተኩላዎች ወደ ሕብረተሰቡ ሲቀላቀሉ ወይም ሲገቡ በጣም ተወዳጅነት ያለው የሰው መልክ ይዘው ስለሚመጡ የምንቀርባቸውን ሰዎች በደንብ  ማወቅ  አለብን ራስን ለማሳወቅ የዘገየን ሰውን ለማወቅ የፈጠን እንሁን ካለማወቅ መሸወድ ይመጣል  የአንድ ቀን

Derartu Tulu Ethiopian athlete

Derartu Tulu

መሸውድ የዘላለም ጸጸት ያመጣል  በተለይም በስደት ላይ የምንግኝ እህቶች እና ወንድሞች ይህንን በተግባር ማዋል ግድ ይሆንብናል፡፡ በቅርቡ የተከሰት አንድ ነገር  ልገልጽላችሁ  እወዳልሁ ነገሩ እንዲህ ነበር መቼም  ኢትዮጵያዊ ሆኖ ፕሮፌሰር ኢሳቅ ኤፍሬምን  የማያውቅ ይኖራል ብየ አልጠራጠርም ባለፈው  በምርጫ 1997 ዘመን  እኒህ ስመ ጥሩ አባት  አንድ ያስታራቂ  ቡድን  በማማቋቋም  መንግሰትን እና ተቃዋሚዎችን  ለማደራደር ሞክረዋል ፡ ሙከራቸውም ለርሳቸው ግቡን መቶላቸዋል ለኢትዮጵያ ህዝብ ግን ሊንጋለት የነበረውን ብረሀን ያጣበት ወቅት ነበር፡ይህ ሰው የሰላምን ጎህ ካዳፈኑት አንዱ መሆናቸው መዘንጋት የለበትም፣ አሁንም አላፍር ብለው ተኩላዎቻቸውን ከሀገር ውጭ በመላክ  በውጭ ሀገር የሚገኙ ተቃዋሚዎችን  ለማዳከም በመስራት ላይ ይገኛሉ አሁን በቅርቡ ከኖርዊ መንግስት ጋር በመደራደር ይህ ያስታራቂ ቡድን  የሚሺን  ሰራውን ለመስራት ወደ ኖርዊይ ያመራው በታዋቂዋ ብርቅየ የኢትዮጵያ  ልጅ በነበረቺው  ደራርቱ ቱሉ ነበር፡ ደራርቱን ማንም ሰው የዚህ አይንት ወራዳ ስራ ትሰራለች ብሎ  የሚጠረጥር ሰው የለም  ለዝህም ነው መልካም ሰው መስለው ይገባሉ  ብየ በመግቢያው ላይ የገለጽኩት  በኦስሎ ከተማ የሚኖሩ የኦሮሞ ተውላጆች  ደራርቱን እና  አብረው የመጡትን ሰዎች  ለምን ስራ እንደመጡ ስለነቁባቸው እና ለመደራደር የሚቀርቡትን ሰውች በቁጥጥር ስር በማድርግ  ስራውን እንዳይሰራ አስቁመዋቸዋል፡ የመጡበት ስራ ሳይሳካላቸው ተመልሰው እንዲሄዱ ምንም አይንት የመደራደሪያ ቀዳዳ እንዳያገኙ ያደረገውን የኦነግ አባላት በኢትዮጵያ ህዝብ ሰም ክፍ ያለ ምስጋናየን አቀርባለሁ ፡፡ ይህ ነው ከኛየሚፈለገው ደራርቱ  ስኳር ልታልስ መምጣቷን ባለማወቅ ሁሉም ሰው ከፍተኛ  የመረጃ ምንጭ ይሰጣት ነበር  ደና ሰው ሲበላሺ  ቅራሬ የለውም ይሉየለ አበው.ሲተርቱ ዋ፡ደራርቱ. ዋ ኢትዮጵያ ማንይሆንእውነተኛሰው ላንቺ የሚቆም ?

በርቱ እንበርታ እንደዚህ ተባብረን  ከሰራን የነጻነት ቀን ቅርብ ነው ከነጣቂ ተኩላዎች ጌታይጠብቀን፡፡

ወያኔ  የሚሰራውን የአሰራር ስልት  አበሻ  የነደፈው ነው ቢባል ለእኔ ከእውነት የራቀነው  ይህ የአውሮፓዊያን  ቀመር ነው ፡፡  በደንብ ከተከታተላችሁት  የሚያሰልሉን እርስ በርሳችን፣ ለጥቅም አደር ሆዳም የሚያገጉት  ከመካከላችን ነው በዚህ  አካሄድ ከቀጠሉ እርስ በርስ  እንድንጋጭ  የሚያደርግ ስልትም  እንደሚፈጥሩ  እርግጠኛነኝ  እኛም  በጣም መጠንቀቅ ያስፈልገናል ፡ ካለፈው የቅንጅት መበታተን ልንማር ይገባንል  ቅንጅት እንደጅምሩ ቢቀጥል ኖሮ የውያኔ እድሜ  እስከ አሁን  አይቆይም ነበር  በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣ ይባልየለ፡ ለቅንጅት  መበታተን  ዋና ምክናየት የሆ ነው  ይህ  አሁንም  በስራላይ ያለው ያስታራቂ  ቡድን  መሆኖን መርሳት የልብንም  ፡፡
በነግራችን ላይ ቅንጅት ይመራ የነበረው  በጣም፡በሳል እና በሀገሪቱ  አሉ በሚባሉት ሙህራን  ነበር  ከሀገረም አልፈው ለሌሎች ሀገሮች  ነጻነት  የሚከራከሩ ሙህራኖችን  ያካተተ ነብር እንደ ምሳሌ ዶክተር  ያቆብን ብጠቅስ  ለሯዋንዳ ሕዝቦች መብት ሲከራከሩ የነበሩት የህግ ባለሞያ   ናቸው ፡ወያኔ የሰራውን የመሰናክል ሩጫ ግን ማለፍ አልቻሉም  ምክናየቱም  የወያኔው የመብት ተሟጋች  አስታራቂ በመምሰል  መሀላቸው ገብተው  እርስበርስ በማጋጨት እንዲበተን አድርገውታል ወያኔም  እድሜ ለፕሮፌሰር  ኢሳቅ እያለ ብዝበዛውን እንደቀጠለ ይገኛል ለመሆኑ ፕሮፌሰር ኢሳቅ ማናቸው ? ሰማቸው እና ግብራቸው አብሮ  የማይሄድ. ከማንኛው እንመድባተው ? ለውደፈት ማወቅ የሚገባን ነገር ቢኖር  በሀገር ጉዳይ ላይ ሽምግልና  እና የምልጃ ስራ  የማይሰራ መሆኑን ነው ፡፡

ወያኔ ከሚጠቀምባቸው የተሻል  ስልት መጠቀም አለብን ያካልሆነ  ግን ሰላም እንደናፈቀቺን እኛም እናልፋለን  ለመስራት በመጀመሪያ  በውስጣችን ያሉትን  እንደነ ደራርቱ እና ፕሮፊሰር ያሉትን  ነጣቂ ተኩላወች  ለይቶ ማውጣት አለብን ፡፡ ወያኔ የተግባር አስፈሚ የሚጠቀምባቸው አንዳንድ ሆዳም ባለሀብቶችን መጠንቀቅ አለብን ፡እንደ ሼህ አላሙዲ  ያሉ ሰውችን ሀገር ወዳድ  በማስመሰል  ለሲምቦል ሲያቀርቡልን  የቀረበው ማነው ብለን መጠየቅ አለብን  እንድህ አይነት ሰወች  የእትዮጵያን ሕዝብ ሊወክሉ የማይችሉ ናቸው ሀገር በተበጠበጥች ቁትር የግል ባልሀብቶች ቢዝንሳቸውን እንደፈልጉት  እራን  ማድረግ ይችላሉ ምክናየቱም  የሰው ሀይልም ሆነ የገባየ ሁኔታ በርካሺ የማግንት ቻንስ እንዳላቸው ጠንቅቀው ያውቃሉ የሚሰሩትም ከገዡ አካል ጋር ተለጥፈው ነው  ሀብቱ ቢሆን  በነሱ ስም የተመዘበር የሀገሪቱ  ገንዘብ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡ ባሳለፍናቸው 21 ዓመታት ሼህ  አላሙዲ ከየት ወደየት  እንደደረሱ ማየት  ይቻላል ፡ በሀገር ውስጥ የሰላም መጥፋት ያለምንም  ተወዳዳሪ ከሌቦች ጋር በመሻረክ  የሀርገሪቱን  የገባያ ሁኔታ  በቁጥጥር ስር አድርገውት ይታያል.፡ እንደዚ አይነት ሰው በጭራሽ ሀገር ሊወክል አይችልም ፡፡

እንድ መነሻ የፕሮፌሰር ኢሳቅን ሥራ ጠቀስኩ እንጅ ብዙ አይነት የማዳከሚያ ስልቶችን  በትለያዩ ሰውች  እየተጠቀሙ ይገኛሉ ከጥንቱም ሰወቹ በዚህ የማሰለል ስራ ልምድ ያላቸው ናተው ፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ታሪክ ልመልሳችሁ.. ደጃችውቤማናቸው ?   የሰሩትን ስራ ታውቃላችሁ ?

የትግራይ ገዥ የነበሩት ደጃች  ውቤ ስልጣናቸውን ለማስፋፋት ሲሉ የአማራውን ክፍለሀገር ለማጥፋትና በቁጥጥራቸው ሥር  ለማድረግ የአማራ ክፍለሀገር ገዥ የነበሩትን እራስአሊን  በአቡነ  ሰላማ በማሰለል  (በማስወገዝ ) የማዳከም ስራ የተጠኸሙ፡መሆኑ ይታወቃል፡፡

አቡነሰላማ የአማራውን  ገዥ የሆኑትን ራስአሊን በገሀድ  በማውግዝ ቀጥለው  እንዳለ  ደጃች ውቤ  በበኩላቸው  ግዙፍ ሰራዊታቸውን  በመምራት  ወደ በጌምደር  አቀኑ  በወቅቱ በጌምድር የንጉስ ግዛት ብትሆንም  ሙሉ ስልጣን የነበራቸው ራስ አሊ ነበሩ፡፡  የነዚህ ወራሪውች ቅድመ  አባት የሆኑት ተንኩል የተሻረባቸው ደጃች ውቤ ንጉስ ዮሐንስ3ኛ እና ደጃች ጎሹን  በማስተባበር  በበላይ አዛዥነት የካቲት 9  1842 ዓ.ም  በአማራው ሕዝብ ላይ የከፋ ጦር እንዳካሄደ  ታሪክ ያስረዳል፡፡ ሙከራውን  ሞከሩእንጅ  ደጃች ውቤ  አልተሳካላቸውም  በራስአሊ ቁጥጥር ስር ነው የወደቁት፡ ከታርክ እንደምንረዳው በሰሜ በኩል ከጥንትም ጀምሮ ሰላም የለም  በሌላ በኩል የትግራይ ክፍለሀገር ሁኔታውን ስንመለከት ደም አፍሳሽ፡ በሆነው የመሳፍንት ዘመን፡ የጉላሚናነበረው ለማለት እንችላለን እርግጥ ነው የሸዋክፍለሀገር በራስ ገዥነት፡ለበርካታ ዘመናት ለመኖር እንደቻለ ይታወሳል ፡፡

የትግራይ ክፍለሀገር ገዦች ከጎንደር፡አቻወቻቸው ጋር በነበራቸው ትሥስር አንድ ጊዜ  በመካከላቸው ሰላምና መረጋጋትን  ሲያሳልፉ በሌላ ጊዜ  ደግሞ አንዱ በሌላው  ላይ በመዝመት  ሲዋጉ አካባቢያቸውንም የጦርነት  ቀጠና በማድረግ ይታወቁ ነበር ፡፡

በአሁኑ ወቅት እኔ እንደሚመስለኝ  በደጃች ወልደ ስላሴ ከ1784 እስክ 1816 ዓ.ም የደረሰባቸውን የጦረነት በቀል እየተበቀሉን ያሉ ይመስለኛል፡፡ነገሩ እንድህ ከሆነ  እኛም የደጃች  ጉግሳነን ብለን እንነሳ  ፡ደጃች ጉግሳ የትግራይን መሪ ግብ ካስያዙት  የመጀመሪያው ጀግና ተዋጊናቸው  ፡፡  ከእኛ  የሚጠበቀው  ከውስጣችን   አንድ  ድጃች ጉግሳን  መፍጠር ወይም ሆኖ መገኘት ነው ፡፡

እነሱ የሰለላን ስራ ከደጃች ውቤ  ውሸት ና ክደትን ከደጃች ወልደሥላሴ  ይዘው  የመጡ መሁኑን ማወቅ አለብን  ዘር ከልጓም ይጠቅሳል ይሉ የለ አበው ሲተርቱ ፡፡ ለአንድ  ወያኔ  መዋሸትና ዋሾ መባል የመዕረግ ስም መሆነን ልንርዳው ይገባናል ፡  የደጃች ወልደስላሴ ክህደት እንዲህ ነበር የትግራይ ገዥ ደጃች ወልደስላሴ  የኢትዮጵያ ገዥ፡እራሳቸው እንደሆኑ በማስመሰል ከውጭ መንግስታት ጋር ግንኙነት ማድረጋቸው ነበር ፡ በመሆኑም ከእንግሊዝ መንግስት ጋር የፖለቲካና የንግድ ትብብር ውል  መፈራረማቸው ይታውቃል ፡፡
ደጃች ወልደስላሴ  ያወረሱ አቸው የሽፍጠኝነት ውርስ  በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ወያኔ አንደጥሩ ተግባር ሲያስፋፉት ይታያል በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሰለሞናዊ ሥርወ መንግስት እስከ አለን በት ዘመን የተለያዩ የጭቆናና አፋና አገዛዞች  ሲካሄዱ የቆየ መሆኑ ባይካድም  የውያኔን ስርዓት ክሌሎቹ የተለየ  የሚያደርገው፣  .

1 . በዘር ላይ የተመሰረተ መሆኑ ፣

2  .አባገነናዊ  እና ጭካኔ የተሞላበት የሰው ልጆች  የመናገርም ሆነ የመጠየቅ መብት የተነፈጉ በት ስርዓት መሆንኑ ሌሎችም ፡፡
በጣም፡የሚገርመው ካንዳንድ ከድሮ የድርጅቱ  ሰውች የምንሰማው ነገርነው የውያኔ መንግስት  ከበጀመርያው  ሲመሰረት ዋና አላማው ኢትዮጵያ የሚለውን ስም እና አማራን ማትፋት ነበር ሲሉ አቶ ገብረመድን አራያ ገልጸዋል  አቶ መለስ ዜናዊም 1974ዓ.ም አማራን ማጥፋት ቀላልነው ማጥፋት አለብን  ሲሉ በሙሉ ቃል ተናግራዋል  ከጫካ እያለ  ጥፋትን የተመኘልን ሰው ምኞቱ ትሳክቶለት እስክ እለተሞቱ የአማራን ልጆች  እንድባብ ጭፍጭፎ፡የጨረሰ ሰው ነው  ጌታ በቃህ ብሉ እርሱን ብያንሳው  ፡ የማጥፋቱን ስራ  አሁንም  ተተኪወቱቹ  ተያይዘውት ይገኛሉ  ይባስ ብለው  በዓለም ታሪክ በጭካኔው በሚታወቀው በ2ኛ የዓለም ጦርነት ጊዜ ያልተሰራውን ስራ ሲፈጽሙ ይታያሉ. የውስን ልጅ ብልት  በገመድ በማሰር  ለባለቤቱ  አስይዞ  ማስጉተት የሞት ሞት ይህ ነው  ከዚህ በላ ምንያድርጉ ሰው ከነነፍሱ  መቅበር  ነው የቀራቸው  ወያኔ   ለመቶ ዓመት የመግዛት ዓላማ ያለው የመምራት ችሎታ የሌለው፣  በመደራደር ከስልጣን የማይለቅ፣  የስስት ባሂሪ ያለው፣  ክሟጨጨ የማይለቅ ዳሞትራ፣  የሰው ደም የመጠጠ መዥገር ልቡ የማይገኝ፡የእባብ ተምሳሌት በውሸት ላይ የተመሰረት  የሌቦች ጥርቅም ካለጦርነት አይለቅም ልንዋጋው ይገባል ሲሉ ገልጸዋል  አቶ ገብረመድን አራያ እስኪ ሁላችንም  የአቶ ገብረመድንንያክል አስተዋጾ  እናድርግ  ልንዋጋቸው ይገባናል ካልተዋጋናቸ

ግን ፈራንም አልፈራንም፣ ብንወድም፣ ባንወድም ፣ቢዋጥልንም ባይዋጥልንም ደስቢለንም ብናዝንም  ለሆዳሞች  የተመቻቸ የአግዛዝ ሰልት አስፈጻሚ መሆናችን  መዘንጋት የለበትም በመተባበር  ሀላችንን መጠቀም  ያልብን ስዓቱ አሁን ነው  የሰው ዘር ጨርሶ ከኢትዮጵያ መሬት ሳይጠፋ  ወገኔ  እንነሳ  ከግብጽ ና ከቱንዝ ሕዝቦች ያየነውን  እኛም በተግባር ላይ እላውለው ዘረኛው የወያኔ መንግስት  በመደራደር ወይም በሰላም የሚለቅ እንዳልሆነ እያውቅነው  እስከመቸድርስ ታፍነን እንኖራልን ለራሳቸን ነጻነት መታገል ያልብን እኛው እራሳችን እንጅ ሌሎች ህይሎች ሰላምን ሊያመጡልን የማይችሉ መሆነን መረዳት  አለብን፡፡ ድል ለኢትዮጵያ ሕዝቦች ፡፡

ከመለስ ሞት ባሻገር  በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ  እየታመሰች ተገኛለች የጠቅላይ ሚንስተር መለስ መሞት ለኢትዮጵያኖች ምንም  ለውጥ  አላሳየም  ሕዝቡም ለማየት ሲጠባበቀው የነበረው ሰላም የውሀ ሽታሆኖነው የቀረበት፡ ፡ ሕዝብ  ጦጣ ፈርቼ  ዛፍ ብወጣ ነብር ቆየኝ  የሚለው ዘይቤ አዊ አባባል ነው የሆነበት ምክናየቱም የ3ሚኒስተሮች  ከመጀመሪያው  አያያዛቸው ሲታይ  ሕዝቦች  ሀገር ለቀው ተሰደዋል  ብዙ ሰወችም ከስራቸው ተፈናቅለዋል በፐርሰንት  ስናየው ከባለፉት ዓመታት  የግማሽ ዓመት  ተጠቂዎትን  ቁጥር  የሚሸፍን ነው በሩብ ዓመት ውስጥ የግማሽ ዓመት  ካሳየ  ኢትዮጵያ  የቀጣዩ እጣ ፈንታዋ ምንይሆን ?

ይህ ችገረንዳለኦሆኖ  የሚገርመው  በአሁኑ ወቅት ሕዝቦቿን  መግባ ማደር ያልቻለቺው  ሀገራቺን  ለኒውክለር  ተጠቃሚ ለመሆን  በስልጣኔ  ከታውቁ  ሀገሮች ጋር ለመፈራረም

መደራደሯ  ነው ፡፡አድሱ ጠቅላይ ሚንስተር የማንችልበት ምንም ምክናየት የለም  በማለት  ሀሳባቸውን ገልጸዋል  ትለብሰው የላት ትኮናነበው አማራት ይሏች ይህነው፡ . ለመሆኑ  ጠቅላይ ሚንስተሩ የትዮጵያን  ሕዝቦች  የኑሮ ሁኔታ በሚገባ  ያውቁ   ይሆን ፟

ይኖራቸዋል ብሎ መገመት በጣም አስቸጋሪ ነው ፡፡በዓለም ላይ ካሉ ድሀ ከሚባሉ ሀገሮች ውስጥ አንዷ መሆኗን እያወቁ  እየለ  በዓለም  ላይ ከታወቁ  የማዕድን  አምራች ሀገሮች ጋር ሲደራደሩ ትንሽ እፍረት አይሰማቸውም ፡በመጀመሪያ፡የሕዝቦች ነጻነት  ይከበር የኒውክለር ምርት ማምረቱ ቀርቶ ፡፡በጉደፍቻ መልክ በመሸጥ ላይ ያሉት የህጻናት  መብት ይከበር. በአሁኑ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያ ልጆችን በጉደፍቻ በመላክ ያልቀ ስም  አግኝታለች  ልጆቹም ላሳዳጊ የሚሰጡት (የሚስሸጡት )ከወላጆቻቸው  ተስርክቀው መሆኑን  አሁን  ብቅርብ  በደኒማርክ ሀገር የከሰትውን  ጥሩ መርጃ መጥቀስ ይቻላል  ለአቶ ኅይላማሪያም  ደሳልኝ  ኒውክለር ከማምረትወት በፊት  ለዜጎቺወት  ቅድሚያ  ይስጡ፡ስል ሃሳቤን  እቋቻልሁ.፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን  ይጠብቅ  አያና ከበደ ከኖርዊይ

ጽሃፊውን  ማግኘት ከፈለጉ ayanakebede@hotmail.com

ECADF.COM

ሰንበት ምሳ፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ልጆች ደቡብ አፍሪካ ምን አላቸው!?

አቤ ቶኪቻው

ዛሬም “ለአዲስ ታይምስ” (ፍትህ) አዲሳባ ተልካ የነበረችቱን ወግ ለሰንበት ምሳ እዚህ ተለጥፋለች፤ ይቋደሱልኝ እውነት ግን የደቡብ ኢትዮጵያ ልጆች ደቡብ አፍሪካ ምን አላቸው!?

ሰላም ወዳጄ እንዴት ሰነበቱ…ሰንበት ምሳ፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ልጆች ደቡብ አፍሪካ ምን አላቸው!?

የመንገድ ቁፋሮው ነገር እንዴት አድርጎታል? በአሁኑ ሰዓት አዲሳባ ውስጥ ትራንስፖርት ከማግኘት “ፖርት” ማግኘት ይቀላል ሲሉ የሚያሽሟጥጡ ሰዎች መበራከታቸውን እየሰማን ነው።

ኧረ “ፖርት” ብል ጊዜ ምን ትዝ አለኝ፤ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ አዲስ ወደብ ግንባታ እያደረገችላት መሆኑን ሰምተን ደስታችን ጨምሯል። እሰይ እንዲህ ነው እንጂ ልግስና! በዚሁ አይነት ፤ ሌሎቹ ጎረቤቶቻችንም እንዳይቀየሙ ብንገነባላቸው ምን አለበት…? ለነ ሱዳን ፤ለነ ሱማሌ ኤርትራዬ እና ኬኒያስ ቢሆኑ ካለኛ ማን አላቸው…? እና ይታሰብበት… “ያስቀኛል ገንፎ ከራቴ ላይ ተርፎ” አሉ አበው!

እና ታድያ የትራንስፖርቱ ነገር እንዴት አደርጎታል? እንደውም እንደሰማሁት ከሆነማ “ፒያሳ መሀሙድጋ ጠብቂኝ” ከሚለው የታላቁ ወዳጃችን መሃመድ ሰልማን መፅሐፍ በኋላ “ቦሌ ፒኮክ ጋ ጠብቂኝ” “መርካቶ ምዕራብ ሆቴል ጋ ጠብቂኝ” የሚሉ ተደጋጋሚ የቀጠሮ ፅሁፎች ሲወጡ የነበረውን ያህል… አሁን በቅርቡ ከወዳጆቻችን እንደ አንዱ የሆነው በሀይሉ ገብረ እግዚአብሔር “የትም አትጠብቂኝ” ብሎ መፃፉን ሰምተናል።

ወዳጃችን ይህንን ሲፅፍ እንደሌሎቹ መቀጣጠሪያ ቦታ አጥቶ ሳይሆን፤ ብቀጥራት በምን ትራንስፖርት ትመጣለች? ብሎ ይመስለኛል። እርግጥ ይሄ የኔ ግምት ነው እንጂ፤ ሙሉ ፅሁፉን ገና አላነበብኩትም። (የት አግኝቼው…)

የምር ግን የትራንስፖርቱ ነገር “የትም አትጠብቂኝ” የሚያስብል መሆኑን ብዙ ወዳጆቼ እያማረሩ ነግረውኛል። እኔ የምለው ግን መንገድ ገንቢው አካል ገንቢ አስተያየቶችን ለምን አይቀበልም? መንገዶቹን እስኪሰሩ ድረስ ወይ አማራጭ መንገድ መስራት ወይ ደግሞ የስራ ማቆም አድማ መጥራት አለበትኮ! አለበለዛ ሰዉ ከአለቃውና ከቀጠራት ጋር እየተጣላ ከተማዋ የድብድብ “ሪንግ” እንዳትሆን ያሰጋል…!

ለማንኛውም ወዳጄ ዛሬም ኬኒያ እንሄዳለን… ሻንጣዎትን መያዝ አይጠበቅብዎም እንደው ደረስ ብለን መለስ ነው የምንለው።

በነገራችን ላይ ከአዲሳባ ኬኒያ አንድ ሰዓት ከሃምሳ ደቂቃ የበረራ ሰዓት ብቻ ነው የሚወስደው። በአሁኑ ሰዓት ከሽሮሜዳ ቦሌ ለመድረስ እንኳ ስንት ሰዓት ይፈጃል? አሁን አሁንማ ምን ሰዓት “ሰው ነው የሚፈጀው እንጂ!” ብለው በጣም አያማሩ…

እንደምንም ብለው ቦሌ ይድረሱ። ከዛም አንድ ሰአት ከሃምሳ ደቂቃ በሰማይ ላይ ተንሳፈው፤ ናይሮቢ ኬኒያ እንኳን ደህና መጡ ብላ ትቀበልዎታለች።

በኬኒያ በተናጠል ከሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን በተጨማሪ በአንድ ጊዜ አርባ ሰላሳ እየሆኑ እየተቧደኑ የሚሰደዱ የደበብ ኢትዮጵያ ልጆችን ማየት በጣም የተለመደ ነገር ነው። እነዚህ “ደቡቤዎች” ኬኒያ የሚመጡት ካናዳ፣ አሜሪካ፣ እና አውሮፓን ናፍቀው አይደለም። ወይ ደግሞ ፖለቲካን ነክተው መንግስት “ንኩት” (ውጡልኝ ከዚህ ቤት) ብሏቸውም አይደለም።

በቃ ከሆነ ጊዜ በኋላ በደቡብ ኢትዮጵያ የመጣ አንድ ፋሽን አለ። አንድ ሰው ጎርመስ ካለ፤ “ደርሷል ይባላል” ለአቅመ አዳም አይደለም። ለአቅመ ስራም አይደለም። ለአቅመ ጉዞ ደበብ አፍሪካ እንጂ…!

አንድ ሰሞን ግራ ገብቶኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ልጆች ደቡብ አፍሪካ ምን አላቸው? ብዬ አንድ ወዳጄን ጠይቄው ነበር።

እርሱም ሲነግረኝ፤ በአንድ ወቅት አንድ የደቡብ ክልል ሰውዬ ስማቸው ጠፋኝ (በቅንፍ እርሳቸውም ጠፍተዋል መሰለኝ። (በሌላ ቅንፍ ዘንድሮ አንደሆነ እግር ኳስ ተጫዋች ሳይሆን እንደወጣ የሚቀረው የመንግስት ባለስልጣን ሆኗል። ሁለቱም ቅንፋችን ዘግተን ስንወጣ))

እናልዎ እኒህ የደቡቤ ባለስልጣን በደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ተደርገው ተሹመው ነበር አሉ። ታድያ ያኔ ሰውዬው በርካታ ዘመዶቻቸውን ከደቡብ ክልል ወደ ደቡብ አፍሪካ ማስወጣት ጀመሩ። ዘመዶቻቸው ደግሞ በ “ሳውዝ” እንደምንም ብለው ተፍጨርጭረው ውጤት ላይ ሲደርሱ ሌላ ዘመዳቸውን መጥራት ጀመሩ። ከዛ እያለ እያለ አሁን አሁን የደቡብ ኢትዮጵያ ልጆች ታላቅ የተስፋ ምድር አድርገው የሚያዩዋት ደቡብ አፍሪካ ሆነች።

ወደዛ ለመድረስ ደግሞ ኬኒያን መርገጥ፤ በኬኒያም መረገጥ ግድ ነው። እንዴት የሚለው ብዙ ነው… ዛሬ እንደው መንደርደሪያውን እንቃመሰውና እንቀጥልበታለን…

አብዛኛዎቹ የደቡቤ ስደተኞች የሚመጡት በግሩፕ ነው ተባብለን የለ! ኬኒያ ድረስ በእግርም በአውቶብስም በምንም በምንም ተብሎ ይገባል። ከዛ በኬኒያ አንድ ቤት ውስጥ ቁጭ ብለው አርባ ወይም ሰላሳ እስኪሞሉ ይጠባበቃሉ። ምክንያቱም ለቀጣዩ የደቡብ አፍሪካ ጉዞ ትራንስፖርታቸውም የትልልቅ መኪና እቃ ማጠራቀሚያ “ኮንቴይነር” ነው። “ኮንቴይነሩ” ከሰላሳ እስከ አርባ የሚሆኑ ሰዎችን በአንዴ ይይዛል። ዋጋውም ከሌሎች መጓጓዣዎች ቀነስ ያደርጋል። ስለዚህ ብዙዎች ይመርጡታል።

በኮንቴይነር ሲጓዙ ታድያ፤ ዋጋው ብቻ ሳይሆን ስቃዩም እርካሽ ነው። ሞቱም በሽ ነው። ምነው እንኳ ባለፈው ኬኒያን አልፈው ታንዛንያ ሲደርሱ ስንት ወጣቶች ናቸው አየር አጥሯቸው በኮንቴይነር ውስጥ የሞቱት…? እረሱት እንዴ፤ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁሉ ዜናውን ሰምተን አልነበር እንዴ! (ወይስ እርስዎ ያኔም ዲሽ ገዝተው ነበር…!? ትንሽ ኢቲቪን ሏሽሟጥ ብዬ እንጂ ዜናው በአለም አቀፍ ማሰራጫዎችም ተሰራጭቶ ነበር። እና በርግጠኝነት ሰምተውታል)

ኬኒያ ቁጭ ካሉ ደግሞ እንደዚህ አይነት ዜና ብርቅ አይደለም። በተለይ ታንዛንያ ላይ በርካታ ወገኖቻችን በታጨቁበት ኮንቴይነር ውስጥ ፍፃሜያቸው ሆኗል።

ነገር ግን እንዲህም ሆኖ ጉዞው አያቋርጥም። መጓጓዣውም አይቀየርም። ኬኒያ ለ12 አመታት የኖረው አዲስ እንደነገረኝ ከሆነ “እነኳን ሌላው ቀርቶ አጠገባቸው ጓደኞቻቸው በኮንቴይነር ውስጥ አየር አጥሯቸው ሞተው በእግዜር ታምር ተርፈው ደቡብ አፍሪካ የገቡ ሰዎች ራሳቸው፤ ሌላ ዘመዳቸውን የሚያስመጡት በኮንቴይነር ነው።” ብሎኛል።

ደቡቤ ወዳጆቻችንም እንትና ሞተ የሚለውን ወሬ ቢሰሙትም ከልባቸው አይፅፉትም። በጣም ያስገረመችኝን አንድ ወሬ ቀጥሎ ልንገርዎትማ፤

በደቡብ ኢትዮጵያ በተለይ ከንባታ እና ሃድያ አካባቢ የተለያዩ ቪዲዮ ቤቶች አሉ። ቪዲዮ ቤቶቹ ፊልም ያሳያሉ። የሚያሳዩት ፊልም የ “ጄኪ ቻን” ካራቴ እንዳይመስልዎ… የ “ጆቴ ጃና ህይወት በደቡብ አፍሪካ” የሚል ነው።

እንግዲህ “ጆቴ” በአካባቢው የሚታወቅ የደቡብ ልጅ ነው አሉ። (ስሙ አፌ ላይ መጥቶ ነው አንጂ ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ያለው እውነተኛው ስም አይደለም) እና ከደቡብ ሲወጣ “ስንጥር ነበር የሚያክለው ቀጫጫ፤ አሁን ወፍሮ ባላባት መስሏል። እቤቱ ሶፋ ላይ ሲቀመጥ፣ በሪሞት ቴሌቪዥኑን ሲያበራ እና ሲያጠፋ፤ የሆነች ነጭ የምታምር መኪና ተደግፎ፣ ደግሞ ሌላ ቀይ መኪና ውስጥ ቁጭ ብሎ “ሾፌር” ሆኖ… ብቻ በጥቅሉ የአካባቢው ወጣቶች በቅርብ የሚያውቁት “ጆቴ ጃና” ሆኗል የሚያስቀና…!

ይህንን ቪዲዮ የአካባቢው ወጣቶች ከፍለው ነው የሚያዩት። ከዛ የስቃይ እና የሞት ወሬ ትዝ አይላቸውም። ቁጭ ብለው ያስባሉ እንደ “ጆቴ ጃና” መሆን የሚቻለው እንዴት ነው? ብዙውን ጊዜ ቪዲዮውን የሚያሳየው ሰውዬ ራሱ አማካሪ ነው። እንደውም ሳስበው ቪዲዮውን ካሳያቸው በኋላ “እንደ ጆቴ ጃና መሆን ይፈልጋሉ… እንግዲያስ መላው ቀላል ነው!” ብሎ ማስታወቂያ ሳይሰራ አይቀርም።

ታድያ የድለላ ስራ ይራና ጠርቀምቀም ያሉ ጎረምሶችን ከመንገድ መሪ ጋር አድርጎ ኬኒያ ያደርሳቸዋል። ከኬኒያ ደግሞ ጠርቀምቀም ሲሉ በኮንቴይነር መኪና ውስጥ ተጭነው በሰላም ከገቡ “ጆቴ ጃና” ደቡብ አፍሪካ ይቀበላቸዋል።

“መሃሉ አይነገርም” እንዲል ሰባኪው መሃሉ ግን ብዙ ጣጣ አለው። በደቡብ ኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ መሃል ካሉት የመሃል ላይ አበሳዎች አንዱ ኬኒያ ውስጥ ያለው አበሳ ነው… በሚቀጥለው ጊዜ ቅንጭብጫቢ አበሳዎችን እናነሳለን!

ለዛሬ ይብቃን…

እስቲ አማን ያሰንብተን!

ECADF.COM

ባዶ ሥልጣን ይዞ ውሸት ለመሳቂያነት

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

Click here for PDF

ፈጽሞ ለማጅ የማያሰኝ ዋሾነት በአቶ ኃይለማርያም ሲተወን አልጀዚራ ላይ ተመልክተናል። እርግጥ ነው እንደ ‘ባለ ራዕዩ’ ጮሌነትና አራዳዊ መገለባበጥ ቢያንሰውም ለመዋሸት Ethiopian PM Hailemariam Desalegn on Al Jazeeraግንባራቸውን እንደማያጥፉ ግን አረጋግጠውልናል። አቶ ኃይለማርያም ምናልባት እየተቆጡ ሲዋሹ፣ እያስፈራሩ ሲቀጥፉ ስለኖሩ እንጂ እንደዚህ በአንድ ጊዜ የላቀ የዋሾነት ሜዳልያ የሚያሰጥ አቅም ሊኖራቸው ባልቻለ ነበር። ብዙ ሰባኪዎችን የተመለከቱ ግን አይመስለኝም። ቢሆን ኖሮ ቴክኒክ ተውሰው ትንሽ እውነት እያስደገፉ ግዙፍ ውሸት በመዋሸት ማደናቆር በቻሉ ነበር እንደ ታምራት ላይኔ። ግን ይዋሻሉ፣ አረ የምን ሰው ምን ይለኛል ነው፣ እግዜር ምን ይለኛልም አይሉም እኮ። አቤት መለስ እንዴት አድርጎ ጠፍጥፎ ሰራቸው እባካችሁ? ግን አላማረባቸውም ምክንያቱም ባዶስልጣን ይዞ ውሸት መሳቂያነት መሆኑን ሊያውቁ በተገባ ነበርና። ለዚህም ነው አስፎጋሪ ውሸት የዋሹት። ስለመሬት ነጠቃው ቀባጠሩ፣ ስለ ታሰሩት ወገኖችም ዋሹ። አዎ ኳስ ጨዋታዋ ላይም ሳቱ። ለመታጠፍ ደግሞ ዘገዩ ኳሱን ተዉትና መለስ እኮ ሃምሳ ጊዜ ኤርትራ እሄዳለሁ ብሎ ነበር አሉና መታጠፍ ጀመሩ። እናቴ ትሙት እጅሽን ልምታ እያለ የሚማጸን ልጅ መሰሉ። አባቱን ድረስልኝ የሚል ልጅ ይመስል ሮጠው መለስ መለስ ሲሉ ያሳዝናሉ። ጋዜጠኛይቱ በሆድዋ ምስኪን የምትል ይመስል ነበር።

ምላስ አጥንት ቢኖረው ታድያ ቀጨ..ጨ..ጨ ሲል በሰማነው ነበር ሲዋሹ። አቤት ባለቤታቸው እንዴት ይሳቀቁ ይሆን? እሳቸውም ከአንድ ውሀ ካልተቀዱ እና ቀዳማይቱን መምሰል ካልፈለጉ ተሳቅቀው ማለቃቸው ነው። ውይ …. የሰው ዐይንስ እንዴት አያለሁ ይሉ ነበር። ደግነቱ ቤተመንግሥት ነው ያሉት ማየትም መስማትም ከማይችሉበት ድብቅ ስፍራ ብለን እንለፈውና ነጥቦቹን እንመልከት። አለዚያማ መጻፋችንስ ምን ዋጋ አለው። ክቡርነትዎ ግን ድንገት ተፈቅዶልዎ ይህንን ካነበቡ የፕሮፌሰር አልማርያምን ምክር አይርሱ። አለም እንደትስቅሎት እየሳቁ ይዋሹ እንጂ አለም እንዲስቅቦት እየሟሸሹ አይዋሹ  ቂ..ቂ….ቂ……

የአስመራ ጉዳይ ላይ የሰጡት አስተያየት ትንሽ ብልጠት ነበረው ምክንያቱም በመጨረሻ የኤርትራ ክሊክ አሸናፊ ሆኖ ኢትዮጵያን ለመጠቅለል መውጣቱን ልብ በማለታቸው ሊሆን ይችላል ብሎ መጠርጠር አስፈላጊ ነው። አለበለዚያም የሳቸው ‘ኤክሰለንሲ’ ያደርጉ እንደነበረው መተጣጠፍ ፈልገው ነበር። ይሁን እንጂ እንኳን በሀገር ጉዳይ ሊወያዩ ስለ ኳስ ጨዋታ እንኳን ያለማወቃቸው አሳፋሪና ከታማኝ ተላላኪም በታች ያደርጋቸዋል።  አቶ ኃይለማርያም እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ መቶ አለቃ ግርማ ሲሆኑ ያሳዝናሉ። እንደዚህ መሳቂያ እናደርግሀለን አርፈህ እንደ እሱ ቁጭ በል የሚሏቸው ይመስላል። ግን እንዲያው ምን አለበት ባያዋርዱዋቸው እሳቸውም እንዲህ ባይወርዱ።

ግን ከዚህ በላይ ዋሽተዋል መዋሸት አይደለም አቶ ኃይለማርያም ደመኛችን ናቸው። አቶ ኃይለማርያም መዋሸት ከጀመሩ ቆይተዋል። አታስታውሱም ብዬ አልልም ከወይዘሮ ገነት ዘውዴ ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለህንዶች ሲደልሉ ኖረዋል፡ አሻሽጠዋል እየዋሹ ሕዝብ አስለቅሰዋል። ይህንን ስትመለከቱ ሰውየው እንደ መግቢያ ያጠኑት ትንሽ አረፍተ ነገር እንዳለና እንደ ትወና በዚያችው እንደሚንደረደሩ ማየት ትችላላችሁ http://www.youtube.com/watch?v=zJ9Lnm7ODjE ይህ ቃልምልልስ ሕንድ አገር ሄደው የሰጡት ነው። ‘Savana land’ ላይ አበሻ አይኖርም ወባ ስለሚፈሩ እዚያ ሰዎች የሉም ይላሉ የአራተኛ ክፍል ጂኦግራፊ እያስታወሱ፣ ሁለት አመት ቆይተውም የተሻለ መከራከሪያ ይዘው አይመጡም አሁንም ‘Savana land’ ውሀው እንደልብ ነው መሬቱ ባዶ ነው ስለዚህ ለውጭ ንግድ የተመቸ ነው ይሉታል ለጠያቂው። ሰው እንዴት እንደዚህ ፈዛዛ ይሆናል ስንት ጽሁፎች ፊልሞች ተሰርተው ከተበተኑ በሁዋላ እንኳን ትንሽ ውሸታቸውን አይቀባቡትም እንዴ? ምንም የተፈናቀለ ሰው የለም ከሚሉ መሰረታዊ ልማት አሟልተን ዘመናዊ የገጠር ቴክኖሎጂ አቅርበን ድሀ ገበሬዎች መካከለኛ ገቢ እንዲያገኙ ጅምራችንን አጠናክረናል አይሉም ነበር? አቤት መሌ ቢሆን ያልገባው ነገር ሲሆን አንጠልጥሎ ነበር የሚሸውደው አንዳንዶች እንደዚህ ሌሎች ደግሞ እንደዚህ ሊሉ ይችላሉ እኛ ግን አማራጫችንን በጊዜው እንወስዳለን ያንን ደግሞ አሁን መናገር አስፈላጊ አይደለም ይሉና ኳስ ከጎላቸው ራቅ ያደርጋሉ ቂ ቂ ቂ ቂ። አቶ ኃይለማርያም ግን እንዲህ እያሉ ይቀጥላሉ…..

የመሬት ነጠቃ የሚባለው ነገር ኢትዮጵያን አይመለከትም ምክንያቱም የምንሰጠው አገልግሎት ላይ ያልዋለ ባዶ መሬት ነው። በሀገር ውስጥ የፖለቲካ ቀውስ ያስከትላል የሚባለው ውሸት ነው። ይሄ የዳያስፖራው ግፊት እንጂ በሀገር ውስጥ ችግር የለብንም ይሉታል ለጠያቂያቸው ለቪክራም ባሂ። ባልደረባቸው ወይዘሮ ገነትም ለዚህ ጋዜጠኛ እንዲህ ነበር ያሉት። “… Our government is giving land to investors with almost negligible price for about 25 to 50 years…” ይላሉ ፈገግ ብለው ። እድሜአቸው እንዲህ ከብዶ ሀሳባቸው እንዲህ መቅለሉ ያሳፍራል። እዚህ ላይ ያገኙዋቸዋል http://www.youtube.com/watch?v=gsFyIeVD108

መቼም ወያኔ በአንድ ነገር ጎበዝ ነው። ከሀዲና ውሸታሞች ፈልፍሎ ያገኛል። እኒህ ሴት እንደተማረ ሰው ሳይሆን የወሬ ወሬ ሰምቶ የሚያወሩ ነው የሚመስለው። እናም እንዲህ አሉ አገራችን ድርቅ ያጠቃታል እናም በረሀብ ትታወቃለች ሕንዶች ደግሞ ጥጥ ይዘራሉ፣ የዘይት እህሎችን ያመርታሉ ስንዴና ሩዝም። ስለዚህ በምግብ ራስን እንድንችል ያደርጉናል ይላሉ። የጥጥ ፍሬ እንኳን ገበሬው ይተርፈው ይመስል። የአነጋገራቸው መንቀርፈፍና የእውቀታቸው አናሳነት ጎልቶ እንደሚታይ ያውቁት ይሆን? ግን ማን ይነግራቸዋል? እስቲ የትኛው ምርት ነው ለአገር ውስጥ ገበያ የዋለው ብሎስ ማን ይጠይቃቸዋል?

አቶ ኃይለማርያም የፖለቲካ እስረኛ በሀገራችን ውስጥ የለም ይላሉ። ያሉት አሸባሪዎች ናቸው እነሱንም ህግ ይዳኛቸዋል አሉ። ትንሽ መለሳለስና አንዳንድ ችግሮችም ካሉ በጥንቃቄ በመመልከት መፍትሄ እንፈልጋለን፣ ታዳጊ ዲሞክራሲ ስለሆነ እየወደቁ መነሳት ያለ ነው የታሰሩት አሸባሪዎች ናቸው ይሁን እንጂ በምክር፣ በመለስተኛ ቅጣትና በማስጠንቀቂያ ውደ ልማታዊነት እንዲመጡ የማድረግ ሂደትም አለ እያሉ ትንሽ ቢያለሰልሱት የፖለቲካ ሀ ሁ ቆጥርዋል ያሰኛቸው ነበር። ግን በጣም ጭፍንና ደካማ ግን ታማኝና ታዛዥ በመሆን ብቻ ነበርና መለስ አጠገብ መሆን የሚቻለውና ደህና ሰነበቱ። ጠቅላይ አስለቃሹ ሲሰናበቱ ሳያስቡት ስልጣን ላይ ራሳቸውን አግኝተዋል ብሎ ማለፍ ይሻላል። ግን እንጠብቃቸው ለሚሉት ምንም ነገር ከርሳቸው መጠበቅ ሞኝነትም መሆኑን ማሳሰብ አስፈላጊ ነው።

ምንም እንኳን አቶ ኃይለማርያም ዳይቨርሲቲ እያሉ የሚደጋግሟት ነገር ብትኖርም ለርሳቸው አኝዋኮች ዳይቨርሲቲ ውስጥ አይገቡም? አፋሮች ሰዎች አይደሉም፣ የተፈናቀሉት አማራዎች የውጭ ዜጎች ናቸው። የራሳቸው ሚዲያ ላይ እንኳን መሰረተ ልማት ምናምን የሚሉትን ለምን አያነቡም። ውሸት አገርቤት ውስጥ እንጃልህ እያሉ እንደሚደነፉት ይመስላቸዋል እንዴ? ወይ ፋታ እንስጣቸው ብሎ ነገር? በሉ ፋታ ወደ ድንፋታ ዞሮ የመከራ ዘመን ሳይበዛ ጠንከር ብላችሁ ታገሉ። ሰውየው ለራሳቸውም ፋታ አላገኙም። ያለው የትግራይ ተገንጣይ ቡድን ነው። አዘናጊ አስተያየት ይቅርና ሕዝቡ ለነፃነቱ ይታገል።

biyadegelgne@hotmail.com

ECADF.COM

ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የድምጻችን ይሰማ ትግላቸውን አንደኛ አመት በቶሮንቶ አከበሩ

ተክለሚካኤል አበበ

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሀይማኖት ነጻነታቸውን ለማስከበር ትግል የጀመሩበትን 1ኛ አመት ቶሮንቶ በሚገኘው ሳላህዲን እስላማዊ ማእከል ትናንት እሁድ ታህሳስ 21 ቀን አከበሩ።Ethiopian muslims held public meeting in Toronto, Canada

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አለማቀፍ ምክርቤታ የቶሮንቶ ቅርንጫፍ ባዘጋጀው በዚህ አንደኛ አመት መታሰቢያ በዓል ላይ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያዊያን ተገኝተዋል።

በአንደኛ አመት መታሰቢያ ዝግጅቱ ላይ፤ ከጀርመን ተጉዘው የመጡትና፤ በአጼ ሀይለስላሴ ዘመን ህዝብ እንደራሴዎች ምክርቤት አባል የነበሩት ታዋቂው ሙስሊም ሀጂ መሀመድ አህመድ ልጅ፤ አቶ መሀመድ ሀሰን ስለሙስሊሞች ትግል ውጣውረድ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።

ካለፉት ሁለት አመት ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ለማዳከም የተለያዩ ሴራዎችን እንዳቀደ የሚያሳይ ሰነድ ከእጃቸው እንደገባ የተናገሩት አቶ መሀመድ ሀሰን፤ ላለፉት 12 ወራት መንግስት በሙስሊሞች ላይ የሚያደርገው አፈና በዚህ ምስጢራዊ ሰነድ ውስጥ እንደተካተተ ተናግረዋል።

አተ መሀመድ ሀሰን የሙስሊሞችን የአንድ አመት ትግል ሂደት የሚያሳዩና ለትግሉ የተደረገውን አለማቀፍ ድጋፍ የሚያሳዩ የምስል ማስረጃዎችን ለተሰብሳቢዎች ያቀረቡ ሲሆን፤ ተሰብሳቢዎቹ አቶ መሀመድ ባቀረቡት ሀሳብ ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዚህ የአንደኛ አመት መታሰቢያ ዝግጅት ላይ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የህገመንግስቱ አንቀጽ 27 እንዲከበር ጥሪ ያደረጉ ሲሆን፤ “ድምጻችን ይሰማ፤ ሰላም አጣን ባገራችን፤ መንግስት የለም ወይ” የሚሉ መፈክሮችንም አሰምተዋል።

በዝግጅቱ ላይ  በቶሮንቶ የሚገኙ አገር ወዳድ የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያንም ተገኝተዋል።

ፓትሪያርክ መርቆሬዎስ ቡራኬ ሰጡ፤ ሊቀካህናት ምሳሌ እንግዳ ታሪካዊ ስህተት እንዳይሰራ አስጠነቀቁ

ተክለሚካኤል አበበ

Abuna Merkorios (Patriarch and Catholicos of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church)

ትናንት እሁድ ታህሳስ 21 ቀን በቶሮንቶ በተከበረው አመታዊው የታህሳስ ገብርኤል በዓለ ንግስ ላይ ፓትሪያርክ መርቆሬዎስ ለህዝቡ ቡራኬ የሰጡ ሲሆን፤ ሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ ከሰላምና አንድነት ሂደቱ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ አሳዛኝ አቅጣጫ እየያዘ መሆኑን ገልጸው፤ ታሪካዊ ስህተት እንዳይሰራ ህዝቡ በንቃት እንዲጠባበቅ አሳስበዋል።

በትናንትናው እለት በተከበረውን የታህሳስ ገብርኤል በኣል ላይ ለህዝቡ ባሰሙት አጭር የመግቢያ ንግግር፤ የውጪው ሲኖዶስ አባላት የቤተክርስቲያን አንድነት እንዲከበር ጥረት ቢያደርጉም፤ ከሰላምና አንድነት ጉባኤው አዘጋጆቹ አንዱና የኢትዮጵያውን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊያናግሩ ሄደው የነበሩት ሊቀካህናት ሀይለስላሴ አለማየሁ ከቤታቸው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተጠርተው በአጃቢ ወደአሜሪካ በግድ እንዲመለሱ እንደተደረጉ ተናግረዋል።

ሌላኛው ሸምጋይ ዲያቆን አንዱአለም የደረሰበት እንደማይታወቅም ተናግረው ዝርዝሩን በመጪው ሳምንት ለህዝቡ እንደሚገልጹና ህዝቡም በንቃት እንዲከታተል አሳስበዋል።
በስደት የሚገኘው ሲኖዶስ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆኑት ሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ በዚህ ሳምንት የጉዳዩን መጨረሻ ተመልከተው ስለሰላምና አንድነት ሂደቱና በሸምጋዮቹ ላይ ስለደረሰው ችግር መግለጫ እንደሚሰጡም ጠቁመዋል።

በትናንትናው እለት በተከበረው በዓል ላይ ባለፈው ወር የቶሮንቶ ቅድስት ማርያም ካቴድራልን መርቀው የከፈቱት ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትሪያርክ ርእሰ ልቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የተገኙ ሲሆን፤ የአቋቀም ሊቅ የሆኑት ፓትሪያርክ በእለቱ በቅዳሴና በዝማሬ፤ በብርቱ መንፈስ ሲያገለግሉ ውለዋል።
የፓትሪያርኩ ጤናም በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ታውቋል።

Abuna Merkorios (Patriarch and Catholicos of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church) 2012

Abuna Merkorios Patriarch and of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church)

Abuna Merkorios Patriarch of the Ethiopian Orthodox Church

ECADF.COM

ተስፋ መቁረጥ የወለደው እርምጃ – መስጊድ ነጠቃ!

ድምፃችን ይሰማ

ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መሠረታዊ የእምነት ነፃነት መብታችን ተጥሶ ለተቃውሞ አደባባይ ከወጣን ድፍን አንድ አመት ሞላን፡፡ ይህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን አንድ ላይ ያስተሳሰረ ተቃውሞ መነሻውም ሆነ መድረሻው የመንግስት በሐይማኖታችን ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች በይፋ መጣሳቸው ነው፡፡ አሕባሽ የተሰኘውን አንጃ ከሊባኖስ በማስመጣት በሙስሊም ዜጎች ላይ በኃይል ለመጫን የተደረገው ሙከራ ለዚህ የከፋ ድርጊት ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ተስፋ መቁረጥ የወለደው እርምጃ - መስጊድ ነጠቃ!

አሕባሽ በከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ታጅቦ በመንግስት ጋባዥነት ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ሊፈፅማቸው ያሰባቸው በርካታ ፕሮጀክቶች ነበሩት፡፡ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ የአህባሽ የግዳጅ ጠመቃ ላይ በወጣው ባለ 15 ነጥብ የአቋም መግለጫ መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረግ ማንኛውም የሙስሊሞች እንቅስቃሴ በአህባሽ የመጅሊስ አስተዳደር ጥብቅ ቁጥጥር ስር እንዲውል፣ ማንኛውም የመስጂድ ኢማምም ሆነ ዳዒ ይህንን የአሕባሽን ስልጠና እንዲሳተፍ፣ የአሕባሽን ስልጠና ያልወሰደ ማንኛውም ኢማም ማሰገድ እንደማይችልና ስልጠናውን ያልወሰደ ኢማም ቦታም ስልጠናውን በወሰደ ሌላ ሰው እንደሚተካ፣ የአህባሽን ስልጠና ያልወሰደ እና ከአህባሽ የመጅሊሱ አስተዳደር ሰርተፊኬት ያልተሰጠው ማንኛውም ዳዒ በየትኛውም መድረክ የኃይማኖት ትምህርት እንዳይሰጥ፣ በሕብረተሰቡ ጉልበት፣ ሀብትና ጥረት የተገነቡ ማንኛውም ኢስላማዊ ተቋማት ለአሕባሽ እንዲሰጡ… አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡

ይህ አዋጅና በከፍተኛ የመንግስት ሁለንተናዊ እገዛ የተደረገው የአሕባሾች እንቅስቃሴ የህዝብን ቁጣ ቀስቅሶ እነሆ መብረጃ ወዳልተገኘለት ቀውስ ውሰጥ ገብቶ ይገኛል፡፡ ሕዝበ ሙስሊሙ በወሰዳቸው ቆራጥ የተቃውሞ እርምጃዎች የአሕባሽ ፕሮጀክቶች አንድ ባንድ ተንኮታከተዋል፡፡ ዛሬ ስለ አህባሽና አደገኛ ሴራው ያልተረዳ እና ራሱንም ቤተሰቡንም ከአደጋው ያልጠበቀ ሙስሊም ግልሰብ ማግኘት አዳጋች ነው፡፡ ይሁንና መንግስት በዚህ ተፀፅቶ እርምት ሊወስድ ሲገባው አላስፈላጊ እልህ ውስጥ በመግባት እነሆ የብዙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች እጣ ፋንታ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት የአህባሽ ፕሮጀክት የመጨረሻ ተግባራትን የፖለቲካ ኃይሉን ተገን አድርጎ ለማስፈፀም እየተጋ ይገኛል፡፡

መንግስት ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ያደራጃቸውን ቡድኖች ስትራቴጂካዊ ቅርጫ በማድረግ ነባሩን የአሕባሽ አመራር በሌላ የአሕባሽ አመራር አካላት ተክቷል፡፡ ይህም ለቀጣይ የመጨረሻ የአህባሽ ፕሮጀክት አፈፃፀም እንደሚረዳው በመተማመን እነሆ በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ድፍረት የተሞላበትን እርምጃ መውሰድ ጀመሯል፡፡ በሕዝብ ንፁህ ሀብት፣ ጉልበት፣ ደምና መስዋዕትነት የተገነቡ ኢስላማዊ ተቋማትም ሆኑ መስጂዶች ለሙስሊሙ ሕዝብ ትርጉማቸው ከ‹‹ግንብ›› ከ‹‹ሕን›› በላይ ነው፡፡ አይደለም ዛሬ የመጣበትን አደጋ ለመከላከል እጅ ለእጅ ተሳስሮ አንድነቱን ይፋ ባደረገበት ወሳኝ ጊዜ ላይ ይቅርና ያኔም በቀደመው ጊዜ በነኚህ ሀብቶቹ ላይ የመጣውን አካል ያለምንም ማቅማማት ሲጋፈጥ ቆይቷል – በዚህ ጉዳይ ተደራድሮም አያውቅም፡፡

ሰሞኑን በአንዳንድ አካባቢዎች በተለይም እዚህ በመዲናችን አዲስ አበባ እና ደሴ ከተማ እየተደረገ ያለው አደገኛ አካሄድ አፀፋ ከማውገዝም በላይ ሊሆን እንደሚችል ማንም ጤነኛ አእምሮ ላለው ሰው የሚጠፋው አይደለም፡፡ ህዝብ ጥሮ ግሮ ያፈራቸውና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን መስጂዶች በፖሊስና በወታደር ኃይል በማስፈራራት፣ በመከብበብና በማገት ለመንጠቅና እና ለአሕባሾች አሳልፎ ለመስጠት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በተለይም በደሴ ከተማ እየተስተዋለ ያለው ሁኔታ ትእግስትን የሚፈታተን ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡ የዚህ የመንግስት አካሄድም ተልዕኮውም ግልፅ ነው፤ ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳት እልቂትና ፍጅትን መጋበዝ ነው፡፡ መስጂዶቻችንን መንጠቅ፣ ኢማሞቻችንን በማባረር በአሕባሾች መተካት በየትኛውም ሐይማኖት ተከታዮች ላይ ታስቦ እንኳን የማይታወቅ ድፍረት ነው፤ የዚህን ድርጊት መቀጠል ተከትሎ ለሚከሰተው ማንኛውም ጥፋት መንግስት ራሱ ተጠያቂ እንደሚሆን ቀድሞ ሊያምንበት ይገባል፡፡ መስጂዶቻችን የህልውናችን ጉዳዮች ናቸው፡፡

አሕባሾን ከማደራጀትና በሌላው ላይ በግድ ከመጫን ያልተቆጠበው መንግስት የህዝብ ንብረት በሆኑት መስጂዶቻችን ላይ ወረራ ከማካሄድ የራሳቸውን መስጂድ ሊገነባላቸው ይችላል፡፡ ከዚህ ቀደም በከሸፉት የአሕባሽ ፕሮጀክቶች፤ በተለይም ሕብረተሰቡ በአንድ ድምጽ የአሕባሽን አስተሳሰብ ከእውቀት በመነሳት አንቅሮ በመትፋቱ በመበሳጨትና በተስፋ መቁረጥ ስሜት ተውጦ ያለ የሌለ ሃይልን በመጠቀም በተጨባጭ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ መዘዙ የከፋ እና የአገራችንንም ገፅታ እስከመጨረሻው ድረስ ሊያበላሽ እንደሚችል ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙም መቼም ቢሆን መስጂዶቹን አሳልፎ እንደማይሰጥ ቢታወቅም በተዘጋጀለት ወጥመድም ላይ እንደማይወድቅም ሊታወቅ ይገባል፡፡

አላሁ አክበር!

ECADF.COM

“ያም ሲያማ፣ ያም ሲያማ – ወገኔ ለኔ ብለህ ስማ!”

ከይነጋል በላቸው
yinegal@gmail.com

ይህን ከዚህ በታች የምታገኙትን ዜና የወሰድኩት ከኢትዮጵያን ሪቪው ድረ ገፅ ነው – ዛሬ ማለዳ ነሐሴ 10 ቀን 2005ዓ.ም፡፡ ለሀገራችን አንዳች ጠቃሚ ነገር ይኖረው ከሆነ ብዬRebels seeking to topple Syria President Bashar Assad  እንደገባኝ ተርጉሜ ልኬዋለሁና እንደመላችሁ አድርጉት፡፡ የእንግሊዝኛው ከግርጌ አለላችሁ፡፡ በአንዳንድ ነጥቦች ዙሪያ ከኛዋ ከርታታ ሀገር የነገሮች መገጣጠም ጋር እያወራረስኩ ጥቂት መናገር እያማረኝ በዩሮኒውስ ቲቪ የ‹nocomment› የእንደወረደ አቀራረብ ሥልት ሆን ብዬ ለአንባቢ ትቼዋለሁ – ጥቂት ቦታዎች ላይ ብቻ ግን – እንዲያው ሳት ብሎኝ – አፅንዖት (emphasis) ብቻ በመስጠት ‹ተናግሬያለሁ›፡፡ ደብተራ የጻፈው አሸንክታብ አስመሰልኩባችሁ ይሆን?

አሳድ በአላዋይቶች ጎሣ የትውልድ ከተማ ‹እስከ መጨረሻዋ ህቅታ ድረስ ሊዋጋ› መዘጋጀቱ ተገለጸ – ሪፖርት

በዚህ ሣምንት ‹ዘ ሰንደይ ታይምስ› እንደዘገበው የሦርያው ፕሬዚደንት ባሽር አላሳድ ከሀገሪቱ ዋና ከተማ ከደማስቆ በመሸሽ የመጨረሻውን ፍልሚያ ሊያደርግባት ወዳሰበባት የትውልድ መንደሩ ሊሄድ ማቀዱን ለመረዳት ተችሏል፡፡

አንድ የራሽያን ዲፕሎማት በምንጭነት ጠቅሶ ይህ የዜና ማዕከል እንደዘገበው 22 ወራትን ባስቆጠረው የገዛ ሕዝቡ አመጽ ሳቢያ ከፍተኛ የነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ውጥረት ውስጥ የገባው የሦሪያው ፕሬዚደንት የማይቀርለት ለሚመስለው የመጨረሻ የአልሞት ባይ ተጋዳይ ግብግብ እየተዘጋጀ ነው፡፡

ይሄው ጋዜጣ ያልተረጋገጠ የዜና ዘገባ ጠቅሶ እንዳሠፈረው ፕሬዚደንት አሳድ  “ ምናልባት የተወሰነ የቤተሰቡን አባላት በአላዊት ጎሣ ምርጥ ኃይሎች ጥበቃ ሥር ወደምትገኘውና ቃርዳ(ሃ) ወደምትባለው የአያት ቅድመ አያቶቹ መኖሪያ ከተማ ቀድሞውን አሽሽቶ ሊሆን ይችላል፡፡”

“አሳድ እስከመጨረሻዋ ጥይት ሊዋጋ ዐቅዷል” ሲል ለ‹ዘ ታይምስ› የገለጸው የራሽያው ዲፕሎማት በማስከተልም የአሳድ መንግሥት ቢያንስ ሰባት የሚደርሱ በአብዛኛው ከአላዊት ጎሣ የተዋቀሩ የልዩ ኮማንዶ ባታሊዮን ጦርና ከአንድ የማያንስ     የተወንጫፊና ተምዘግዛጊ ሚሳይል ባታሊዮን በዚሁ የአላዊቶች ጎሣ መኖሪያ በሆነችው ከተማ በዚህ ወር መጀመሪያ አካባቢ ማሸመቁን የመካከለኛውን ምሥራቅ የደኅንነትና የፀጥታ ምንጮች በመጥቀስ ገልጧል፡፡

የዜና ምንጮቹ “የአሳድ ኃይሎች የአላዊቶችን ከተማ ከማንኛውም የተቃዋሚዎች ጥቃት ለመከላከል ዙሪያዋንና ከሌሎች ቦታዎች የሚያገናኟትን መንገዶች በሚቀበሩ ፈንጅዎች አጥረዋል፤ ልዩ የጦር ኃይልም ተሠማርቶ ቅኝትና ጥበቃ ያደርግላታል” ካሉ በኋላ አክለው እንደገለጹት የተወንጫፊ ሚሳኤሎቹ ባታሊዮን ጅምላ ጨራሽ የሆነ የኬሚካል ማሣሪያ መታጠቁንም ጠቁመዋል፡፡

ከዚሁ በተያያዘ አላዊቶች ከተደቀነባቸው አደጋ በማምለጥ ጥበቃና ከለላ ሊያገኙ ወደሚችሉባቸው ሥፍራዎች ወደ ሊባኖስና ቱርክ የጋራ ድንበር የሜዲትራኒያን የባህር ዳርቻ አካባቢ ሲጎርፉ መታየታቸው የሁኔታዎችን እየተባባሰ መሄድ እንደሚጠቁም ዘገባዎች አውስተዋል፡፡

በብዛታቸው ከሦርያ ሕዝብ 12 በመቶ (ብቻ) የሚሆኑት አላዊቶች በአብዛኛው የአሳድ ደጋፊና ታማኞች ሆነው ዘልቀዋል፡፡ ከነዚህም አብዛኞቹ በአሳድ መንግሥት ውስጥ ቁልፍ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችንና የጦርና የፀጥታ ተቋማትን አመራር መያዛቸው የሚታወቅ ነው፡፡       

የዜና ምንጩ እንደጠቀሰው አላዊቱ አሳድ ጦርነቱን (በእልህ) ለመግፋት ወስኖ በዚያች በጎሣው ከተማ ከመሸገና ጦርነቱን ከቀጠለ ከራሱ ጎሣ የመሠረተው ታማኝ ጦር ለአሳድ ከሚሰስትለት የአካባቢው የአላዊት ሕዝብ ጋር በመተባበር ጦርነቱን ለወራት መቀጠል እንደሚችል የታመነ መሆኑን ጠቅሷል፡፡

በተያያዘ ዜና ይህ ራሽያዊ ዲፕሎማት የዜና ምንጭ የሦርያው ሕዝባዊ ዐመፅ ከተጀመረ ከማርች 2011 ወዲህ ለበርካታ ጊዜያት ከፕሬዚደንት አሳድ ጋር እንደተገናኘ ለመረዳት ተችሏል፡፡

የአሳድ መንግሥት በሲቭሉ ማኅበረሰብ ላይ የሚያካሂደውን ጭፍጨፋ የአሜሪካን መንግሥት (በዲፕሎማሲ ደረጃ) የሚቃወመው መሆኑን በማስታከክ “አላዊቶች በጦር ከፍተኛ ሥልጠናና ዘመናዊ መሣሪያም እስካፍንጫቸው የታጠቁ መሆናቸውን፣ ያላቸው ብቸኛ ምርጫም እስከመጨረሻዋ የደም ጠብታ መፋለም መሆኑን አሜሪካዎች ያውቃሉ፡፡” በማለት  የዜና ምንጩ ተጠሪ በአፅንዖት ገልጦኣል፡፡

ጋዜጣው አክሎ እንደዘገበው ይህ ሀገሩን ወክሎ በሦርያ ጉዳይ ከአሜሪካዎች ጋር ይደራደር የነበረው ራሽያዊ ዲፕሎማት ባለፈው ሣምንት አሜሪካ የሦርያውያንን የተቃውሞ ኃይላት የጋራ ግንባር (SNC – Syrian National Coalition) ለሦርያ ብቸኛው ሕጋዊ ወኪል አድርጋ መቀበሏና ዕውቅና መስጠቷ እንዳላስደሰተው ጠቁሟል፡፡

በዚህ የራሽያ ዲፕሎማትና በአሳድ መካከል በተደረገ አንድ የቅርብ ጊዜ ውይይት“ሆስኒ ሙባረክ ከሥልጣን ቢወገድም ግብጽ ግን አለች፡፡ ነገር ግን እኔ ከሥልጣን ብወገድ ሦርያ የምትባል ሀገር ከናካቴው አትኖርም፡፡” በማለት አሳድ ማስጠንቀቁና ማስፈራራቱ ተዘግቧል፡፡

በእስካሁኑ የሦርያ የመንግሥት ይለወጥልን ሕዝባዊ ዐመፅና የርስ በርስ ግጭት በትንሹ ዐርባ ሺህ ሕዝብ ማለቁና ካለቀውም ሕዝብ አብዛኛው በአላዊቶች ግዛት አቅራቢያ በትሬሜሽ፣ በራስታንና በሁላ በሚገኙ የሱኒዎች መንደሮች የሚገኙ ሱኒ ነዋሪዎች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ምንጭ፡- ኢትዮጰያን ሪቪው ዌብሳይት

The Last stand, As Assad prepares to ‘fight to his last bullet’ in Alawite hometown – Report

Syria’s President Bashar al-Assad is reportedly planning an escape from Damascus, preparing for a last stand in his home town, The Sunday Times reported this week.

The embattled leader, facing a lingering 22-month-old uprising against his rule, is preparing for the “worst case scenario,” according to a Russian source who spoke to the newspaper.

The story cites unconfirmed report suggesting Assad “may already have moved members of his family to the town of Qardaha, the family’s ancestral home, where they were being guarded by loyal Alawite special forces.”

Assad plans to “fight to his last bullet” the Russian source told The Times, which highlighted that at least seven largely Alawite commando battalions and up to one ballistic missile battalion had been redeployed to the Alawite territory earlier this month, says Middle East intelligence sources.

They add the missile battalion was equipped with chemical munitions, noting “Assad’s forces mined roads along the border and moved Elite Special Forces to monitor the area,” the newspaper said.

This reflects on recent reports that a flood of Alawites were fleeing to a sanctuary along the Mediterranean coast between Lebanon and Turkey.

Alawites, who make up about 12 percent of the Syrian population, have largely stayed loyal to President Assad. Many occupy key positions in the government and security forces.

If Assad were to take his last battle to his home town, the Russian source told the paper that Assad’s army could “fight on for months with the help of … a sympathetic local population.”

The source is reported to have met with Assad several times since the start of the Syrian uprising, which erupted in March 2011.

“The Americans know that the Alawites are well trained and well equipped and that they have no choice but to fight to the bitter end,” he emphasized, in reference to continued U.S. condemnation of the deadly Syrian army attacks on the civilian population.

The newspaper says the source, who has also been involved in talks with U.S. officials, was disappointed by last week’s American decision to recognize a coalition of opposition forces as the legitimate representative of the Syrian people.

In a meeting between him and Assad, the Syrian leader reportedly said: “Mubarak may have gone but Egypt remains. But if I go, none of Syria remains.”

At least 40,000 people have been killed in violence across the country since the outbreak of an anti-regime revolt, with major attacks reported in Sunni villages, including Tremesh, Rastan and Houla – all of which lie on the eastern edge of Alawite territory.

Source: ethiopianreview.com

 ECADF.COM